Get Mystery Box with random crypto!

ኑ እናንብብ

የቴሌግራም ቻናል አርማ nuenanbib — ኑ እናንብብ
የቴሌግራም ቻናል አርማ nuenanbib — ኑ እናንብብ
የሰርጥ አድራሻ: @nuenanbib
ምድቦች: ሳይኮሎጂ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.11K
የሰርጥ መግለጫ

ማንበብ የስብዕና ልህቀትን ያጎናፅፋል!!
ማንበብ ምክንያታዊ እና የሰላ አእምሮን ያንፃል!!
በዚህ ቻናል
👉የስነ ልቦና ምክሮች
👉ግጥሞችና ወጎች
👉ሳይንስና ፍልስፍና
በብዛት ይቀርባሉ።
ወዳጆዎን የዚህ የንባብ ማዕድ ተካፋይ እንዲሆኑ በመጋበዝ ቻናሉን ይደግፋ።
ማንኛውም አስተያየት @NuEnanbib_bot ላይ ይላኩልን

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2022-03-21 19:45:51
#ከድንጋይ_ፈላጩ_ተማር

በስተመጨረሻ የእምቅ ችሎታ ጉብታህን ስታልፍ ሰዎች ስኬትህን የአንድ ቀን ስኬት ብለው ይጠሩታል፡፡ የውጪው ዓለም ሁሉንም የለውጥ ደረጃዎችህን አያይም፡፡ ሰዎች ማየት የሚችሉት ድራማዊ የሆነውን የለውጡን ፍሬ መገለጫ ብቻ ነው። አንተ ግን ለዚህ ያበቁህ ምንም ለውጥ እያሳየህ በማይመስል ሰዓት ሁሉ የሰራሀቸው ጠንካራ ስራዎች መሆናቸውን ታውቃለህ፡፡ በአንድ ነገር ላይ ለመንገስ ትዕግስት የግድ አስፈላጊ ነገር ነው።

ከውጤታማዎቹ የኤን ቢ ኤ ቡድኖች መካከል ተጠቃሽ የሆነው ሳን አንቶኒዮ ስፐርስ ከማህበራዊ ቀራፂው ከጃኮብ ሪስ ወስዶ በተጨዋቾቹ ሎከር ላይ የሰቀለው አንድ ጥቅስ አለ፡፡ ጥቅሱ እንዲህ ይላል፤ ሁሉ ነገር ምንም ለውጥ የማያመጣ በሚመስለኝ ጊዜ ሄጄ የማየው አንድ ድንጋይ ፈላጭ አለ፡፡ ይህ ፈላጭ ድንጋዩን በድንጋይ መፍለጫው መቶ ጊዜ ይመታዋል፡፡ በዚህ ሁሉ ድካም ውስጥ ግን ምንም የመሰንጠቅ ምልክት ድንጋዩ ላይ አይታይም፡፡ በመቶ አንደኛው ምት ግን ድንጋዩ ለሁለት ይሰነጠቃል፡፡ እኔ ግን ድንጋዩን የሰነጠቀችው 101ኛዋ ምት ብቻዋን ሳትሆን መቶ አንዱም ምቶች በአጠቃላይ ተደማምረው እንደሆነ አውቃለሁ፡፡”

ከልማድ ኃይል መጽሐፍ የተወሰደ

@Human_Intelligence
@Human_Intelligence
5.3K viewsedited  16:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-12 20:10:18 ከሞት በፊት

አንዲት ትንፋሽ ብቻ ቀርታኝ
በጣዕረ ሞት ተከብቤ
መኖር ይሉት የምድር ሸክም
ሲንሸራተት ካጠገቤ
ህይወት ሳስታ ቀኗ አብቅቶ
የጤፍ ያህል ምን ብታንስም
ሞትን ቀድሜው አልሞትም

እግር ጥሏችሁ በደጄ
በዚያች ሰዓት የምታልፋ
ዜማዬን ነው የምትሰሙት
ለቅሶ የለኝም አትልፉ

ገጣሚ-ሩሚ
ተርጓሚ-ፍስሃ ጌትነት


@NuEnanbib
5.4K viewsedited  17:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-03-08 20:53:11
አፍሪካ በሙስና ብቻ ወደ 150 ቢልዮን ዶላር በዓመት ታጣለች ::

20 % የሚሆነው የአፍሪካ ህዝብ በጠኔ ምክንያት የሞት አፋፍ ላይ ነው ::

31 % የሚሆኑ ከሠሃራ በታች የሚገኙ ህፃናት የተመጣጠነ ምግብ አጥተው ቀንጭረዋል ::

ግማሽ ቢልዮን የሚሆነው የአፍሪካ ህዝብ አሁንም በመብራት እጦት ዳፈና ውስጥ ይኳትናል ::

50% የሚሆነው አፍሪካዊ በኮሌራ እና ተቅማጥ የመያዝ እድሉ ሰፊ ነው ።

አንዲት አፍሪካዊ ሴት ከአሜሪካዊት ሴት ጋር ስትነፃፀር 231 እጥፍ በወሊድ ወቅት የመሞት እድል አላት ::

25 ሚልዮኑ አፍሪካዊ የ "HIV" ታማሚ ነው። 600 ሚልዮኑ አፍሪካዊ ማንበብ እና መጻፍ የማይችል መሃይም ነው።

እኛ አፍሪካውያን ያልተረዳነው ዋናውና ዋናው ነገር አፍሪካ ወደከፍታ የምትሻገረው በእርዳታና በሌሎች ችሮታ ሳይሆን በጠንካራ የሥራ ባህል በቴክኖሎጂ ፈጠራ እና በካፒታል ነው።

ቻይና 850 ሚልዮን ህዝቧን ከደህነት አረንቋ ያወጣችው በእርዳታ ሳይሆን በራሷ ስራ ነው!

በእርዳታ ያደገ ወይም የበለፀገ አህጉር አይደለም ሃገር እንኳን የለችም :: የሚገርመው አሜሪካ ከቻይና ገንዘብ ትበደራለች :: ከዛ የተበደረችውን ደግሞ ለአፍሪካ በእርዳታ መልክ ትሰጣለች! አሜሪካ ምን ያህል ብታስብልን ይሆን !?

ምንም ጥርጥር የለውም የአፍሪካ ሃብት የሚመዘበረው በእርዳታ መጋረጃ ነው።

Dead Aid
Dr. Dambisa Moyo

ሽያጭ ላይ ነን ::
ጃዕፈር መጻሕፍት !!
6.0K views17:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-27 16:24:55 ኮኮብ ቆጣሪዎችንና አፈጮሌ ፖለቲከኞችን አትመኗቸው!!!
ፎረር ኢፌክት (Forer Effect)

አንባቢዬ ሆይ ሊያስደነግጥህ ይችላል ግን እኔ በግል አውቅሃለሁ። አንተንም እንዲህ እገልፅሃለሁ፡፡ ‹‹ሌሎች እንዲወዱህና እንዲያደንቁህ በጣም ትፈልጋለህ፡፡ ለራስህም ምክንያታዊና አስተዋይ ለመሆን ትፈልጋለህ፡፡ ያልተጠቀምክበትና ሁሌ የሚቆጭህ እምቅ ችሎታ አለህ፡፡ የተወሰኑ ድክመቶች ቢኖሩብህም የምታስተካክላቸው አይነት ናቸው፡፡ ፆታዊ ግንኙነትህ የተወሰኑ ችግሮችን ፈጥሮብሃል፡፡ ከውጭ ለሚያይህ ስነ ስርዓትህን የጠበቅህ እና ራስህን የምትቆጣጠር ብትመስልም ውስጥህ ግን ይጨነቃል፤ ይፈራል፡፡

‹‹የወሰንከውን ውሳኔዎች ትክክለኛነት ወደኋላ እየተመለስክ የምትጠይቅባቸው ጊዜያት አሉ፡፡ ብዙ አማራጮችንና ለውጦችን ትፈልጋለህ፡፡ ይህንን የሚያደናቅፉብህ ነገሮች ሲበዙም ትበሳጫለህ፡፡ ራስህን እንደገለልተኛና ነጻ አሳቢ ስለምታይ ትኮራለህ፡፡ የማንንም ሀሳብ ሳታረጋግጥ አትቀበልም፡፡ ለሌሎች ራስህን ሙሉ በሙሉ ግልጽ ማድረግ ተገቢ እንዳልሆነ ታውቃለህ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ተግባቢ፣ ትሁት ፣ተጫዋች ትሆናለህ ፤ አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ዝምተኛ እና ሰው የማታምን ትሆናለህ፡፡ አንዳንዶቹ ፍላጎቶችህ ፈጽሞ መሆን የማይችሉ ይመስላሉ አንተ ግን እንደምታደርጋቸው ታምናለህ ፡፡››

ራስህ ታውቀዋለህ? ምን ያህል ገልጬሃለሁ? እስኪ ከ 1 (በጣም ደካማ) እስከ 5 (በጣም ጥሩ) ማርክ ስጠኝ፡፡

የስነ ልቦና ባለሞያው በርትራም ፎረር በ1948 አሁን ከላይ ያቀረብኩትን ጽሁፍ ራሱ አዘጋጅቶ ነበር፡፡ ከዚያም ሁሉም ተማሪዎች እንዲያነቡት ሰጣቸው፡፡ እያንዳንዳቸውም በየግል እንደተጠኑና ጽሁፉም የባህሪያቸው ገላጭ የጥናት ውጤት መሆኑም ተነገራቸው። ካነበቡ በኋላም ከ 1-5 ውጤት እንዲሰጡት ጠየቃችው፡፡ ተማሪዎቹም በአማካይ 4.3/5 ሰጡት፡፡ በዚህም 86% ትክክል ነህ አሉት፡፡ ይህ ምርምር በቀጣዮቹ አስርት አመታት ለብዙ ጊዜ በተለያዩ ሰዎች ላይ ተደጋግሞ ተሰርቷል፤ ውጤቱም ተመሳሳይ ነበር።

አንተም ቢሆን ከ 4 ነጥብ በታች እንዳልሰጠኸኝ አምናለሁ፡፡ ሰዎች ራሳቸውን ለመለየት የሚሞክሩት እንዲህ ባሉ አለም አቀፋዊ መገለጫዎች ነው፡፡ ሳይንስ ይህንን አሳሳች ዝንባሌ ፎረር አፌክት ወይም (Barnum effect) ይለዋል፡፡ ይህ ዘርፍ እነዚህ የተሳሳቱ ሳይንሶች ለምን በትክክል እንደሚሰሩ ያወራል። አስትሮሎጂ(ኮኮብ ቆጣሪዎች) የእጅ ጽሁፍ ምርምር፣ መዳፍ ማንበብና የሙት ማናገር ጥበብ ወዘተን አስታውስ፡፡

ከፎረር ኢፎክት ጀርባ ያለው ምንድን ነው? #በመጀመሪያ ደረጃ በፎረር ጽሁፍ ውስጥ ዓረፍተ ነገሮቹ በጣም ጠቅላላና ለሁሉም ሰው የሚሆኑ ናቸው፡፡ #ሁለተኛ አንዳንድ እኛን የማይገልጹንን ነገር ግን ደስ የሚሉንን ዓረፍተ ነገሮች የመቀበል አባዜ አለብን፡፡ ለምሳሌ «በራስህ የምታስብ በመሆንህ ትኮራለህ» የሚለውን ሀሳብ ተመልከት፡፡ ምንም ጭንቅላት የሌለው፣ ማንንም እየተከተለ የሚኖር መሆን ማን ይፈልጋል? እውነታው ግን ያ ላይሆን ይችላል። #ሶስተኛ ‹‹የአሉታ ተጽዕኖ›› የሚባለው ነገር ሚናውን ይጫወታል። የተዘረዘሩት ዓረፍተ ነገሮች በሙሉ አዎንታዊ ሃሳቦች ብቻ የያዙ ናቸው፡፡ #አራተኛ የስህተቶች ሁሉ አባት የሆነ ነው የማረጋገጥ መድሎዕ (confirmation bias) አለ፡፡ ሳናስበው የሚስማማንና የሚመስለንን ነገር ሁሉ እየተቀበልን ሌላውን እንተዋለን ወይም ደግሞ እውነትም ውሸትም ለማለት የሚከብዱ ሀሳቦችን በመጠቀም ሰዎች እውነት የሚመስለውን እንዲመርጡ የማድረግ ጥበብ ነው።


የጠ/ሚኒስትራችንን ንግግሮችና ፁሁፎች ልብ ካላችሁት በእንደዚህ አይነት ጥበብ (Forer Effect) የተካኑ ናቸው።በህዝብ ዘንድ ተወዳጅነት ካገኙትበት ምክንያትም አንዱ በforer effect የበለፀጉ ንግግሮቻቸው ነው። ንግግሮቹ ከላይ የተጠቀሱት አራቱም ባህሪዎች ይንፀባረቁበታል። ለዚህም ነው ንግግሮቹ ሁሉን የሚያስደስቱና ሁሉንም ህዝብ የሚገልፁ የሆኑት ነገር ግን የጠ/ሚኒስትሩንም ሆነ የፓሪቲያቸውን ግልፅ አቋም አያሳዩም።አጨቃጫቂ እውነታዎችን አድበስብሰው ያልፋሉ፤ እናም ሁልጊዜም ሁሉንም የሚያስደስት ቀጭን መንገድ ይፈልጋሉ።ለጊዜው ሁሉንም ሳይስከፉ ቢያልፋም አቋማቸው በተግባር ሲገለፅ ግን ብዙ ተቃውሞ ይገጥማቸዋል። ምክንያቱም ሁሉንም ማስደሰት የማይቻል ነገር ነውና ሁሉንም ለማስደሰት የሚያደርጉት ጥረትም አቋም የለሽ እንዲሆኑ አርጓቸዋል። አንዳንድ ጊዜ ንግግሮቻቸውና ተግባራቸው ፍፁም የማይገናኙ ይሆናሉ።ይህም ንግግሮቻቸው እውነተኛውን አቋማቸውን ስለማይገልፁ ነው። ታዲያ እንደዚህ አይነት መሪዎችን ከንግግሮቻቸው ይልቅ ተግባራቸውን በማየት ብቻ ነው አቋማቸውን ማወቅ የሚቻለው።

መነሻ ሀሳብ
(The Art of clearly thinking)
ሮልፍ ዶብሊ

#አቤል
የስብዕና ልህቀት
@Human_intelligence
@Human_intelligence
5.8K views13:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-19 17:19:02 ሕይወት የምትጀምረው መቼ ነው?

ሁለት ሰዎች በአንድ ጉዳይ ላይ ይከራከሩ ነበር፡፡ አንዱ፣ “ሕይወት የምትጀምረው ልክ አንድ ጽንስ በተጸነሰበት ቅጽፈት ነው” በማለት ያንን እምነቱን በግለት ያስተጋባል፡፡

ሌላኛው ደግሞ፣ “አይደለም! ሕይወት የምትጀምረው የተጸነሰው ልጅ የመጀመሪያውን ትንፋሽ ወደመተንፈስ ደረጃ ሲደርስ ነው” በማለት የተጋጋለ ምላሹን ይናገራል፡፡

ይህንን ሃሳብ ሳይለቁ ለሰዓታት ሲከራከሩ የተመለከተ አንድ ሰው እያዋዛ አንድን ትምህርት ትቶላቸው አለፈ፣ “ሁለታችሁም ተሳስታችኋል፤ ሕይወት የምትጀምረው ሰው የተፈጠረለትን ዓላማውን ሲያውቅና ያንን መከተል ሲጀምር ነው”!!!

ዓላማችንን እንወቅ! በግለት እንከታተለው! እንኑረው!


የስብዕና ልህቀት
@Human_intelligence
@Human_intelligence
5.6K views14:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-17 08:04:13 ነግሬሽ ነበረ

ሴት ክብሯን ረስታ ፣ ጭኗን እንዳታምነው
ሁሉን ያጣል ብዬ ፣ የሁሉም የሆነው!!!

ነግሬሽ ነበረ
ውበት ደም ግባትሽ ፣ ሁሉን እንደሚስብ
የወንድ ልጅን ዐይን..
ከተበተነበት ፣ እንደሚሰበስብ
ነግሬሽ ነበረ...
ትንሽ ስትዘነጊኝ ፣ ብዙ እንደማስብ!!!

ነግሬሽ ነበረ... ባትሰሚኝም እንኳ
ሳሙና ነው ብዬ ፣ የቆንጆ ሴት መልኳ
እድፋም ስሜቶችን...
አሽታ ስታነፃ ፣ ያበቃል ታሪኳ!!!

ነግሬሽ ነበረ
ሴት ልጅ ስታማርጥ ፣ ለራሷ ምራጭ ናት
በክብር ነው እንጂ...
በመውለድ አይደለም ፣ የሚኮነው እናት፡፡
ክብረ ቢስ ህይወቶች ፣ ጣፍጠው አይቀጥሉም
የወለዱ ሁሉ እናቶች አይደሉም
ነግሬሽ ነበረ
እናትነት ስሟ
ከክብሯ ነው እንጂ ፣ ከልጇ እንዳልመጣ
ወልዳም ምንም ነች ፣ ሴት ክብሯን ስታጣ።

ነግሬሽ ነበረ...
ሴት ክብሯን ስትጥል ፣ እድሜዋ ይሔዳል
የወንድ ልጅ ቤቱ...
የሴትልጅ ውበት ነው ፣ ካየበት ይለምዳል፡፡

ነግሬሽ ነበረ...
ጭንሽ ሴትነትን ፣ ከቶ እንደማይበልጠው
ቁንጅናም ይረክሳል!
ብቻውን እንዲቀር ፣ ሁሉም ከመረጠው!
ብነግርሽ ብነግርሽ ፣ ባትሰሚኝም ቅሉ
"ሰደበኝ" በማለት ፣ ታወሪያለሽ አሉ
ልክ ነሽ አንዳንዴ
እውነቶች ውሸት ፊት ፣ ስድብ ይመሥላሉ።

ሞኝ ሰው ሲመክሩት
ሞኝ ሰው ሲነግሩት
የቀኑበት መስሎት ፣ በከንቱ ቢታበይ
ግን እነግርሻለሁ!
ነግሪያት ነበር ስል
ቀንቶ ተናገረኝ ፣ ወይም ሰደበኝ በይ።

ግን እነግርሻለሁ
ግን እመክርሻለሁ
ሴት ልጅ ክብሯ ሲጎድል ፣ ውበቷ አይመችም
ሁሉም ይመኟታል ፣ ከአንዱም ልብ የለችም!!!

በላይ በቀለ ወያ እንደፃፈው


@NuEnanbib
6.0K viewsedited  05:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-02-12 20:11:40 ,,,,,የታለች,,,,,

ሄዋን ወዴት አለች
በተፈጥሮ ውበት
ኮርታ የደመቀች፣
ፀጉሯ አልበቃ ብሏት
ሂውማን ያልቀጠለች፡፡

አምሮ ለመታየት
በሜካፕ ያለወዛች፣
ጣቶቿን ሞርዳ
ጥፍር ያልሰካካች::

ቅርፃዋን ለማሳመር
በስንፖንጅ ያልተመካች፣
በመሰልጠን ሰበብ
እርቃንዋን ያልወጣች::

ክቡሩን ገላዋንን
በወግ የሸፈነች
ማንነትዋን ሳትክድ
እራሳዋን የሆነች፣
ያቺ ልባም ሄዋን
ንገሩኝ የታለች?!

ሰብለወንጌል

@getem
@NuEnanbib
6.1K viewsedited  17:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ