Get Mystery Box with random crypto!

ኑ እናንብብ

የቴሌግራም ቻናል አርማ nuenanbib — ኑ እናንብብ
የቴሌግራም ቻናል አርማ nuenanbib — ኑ እናንብብ
የሰርጥ አድራሻ: @nuenanbib
ምድቦች: ሳይኮሎጂ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.11K
የሰርጥ መግለጫ

ማንበብ የስብዕና ልህቀትን ያጎናፅፋል!!
ማንበብ ምክንያታዊ እና የሰላ አእምሮን ያንፃል!!
በዚህ ቻናል
👉የስነ ልቦና ምክሮች
👉ግጥሞችና ወጎች
👉ሳይንስና ፍልስፍና
በብዛት ይቀርባሉ።
ወዳጆዎን የዚህ የንባብ ማዕድ ተካፋይ እንዲሆኑ በመጋበዝ ቻናሉን ይደግፋ።
ማንኛውም አስተያየት @NuEnanbib_bot ላይ ይላኩልን

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2022-08-27 08:14:36 እናየው ይሆን ይህን ቀን አልፈን?!

(በእውቀቱ ስዩም)

በጦር መርታት ነው፤  የሁሉም ተስፋው
የሰላም ዋጋ  መቸ  ታሰበ?
አብሮ ለመኖር መላው የጠፋው
አብሮ ለመሞት ተሰባሰበ::

እንዳውሬ መኖር ፤እንደ ሰው ለብሶ
እብዱን ስንፈራው ፤ ጭምቱ ብሶ
“ውረድ እንውረድ”  የሁሉም ዘፈን
እናየው ይሆን ፤ ይሕን ቀን አልፈን   ?


የሞት ፈረስ ነው፥ አንደኛው ላንዱ
የሁሉም ክንዱ-
-ለማነቅ ተግቶ ፤ ለማቀፍ ዛለ
“ አንተኛው ታገስ፤ አንተም ተመለስ “
የሚል የታለ?
እንደ ጥጥ ሸክም ፤ ሽበት ቀለለ
መስቀል ጨረቃው አልተከበረ
ማርጀት ነው እንጂ መሸምገል ቀረ : :
1.1K views05:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 08:25:26 አስተሳሰቦችና ፍልስፍናዎች
@Zephilosophy

«ፍቅር ቤቱን የሠራበት ልብ እንዴት የታደለ ነው? ምክንያቱም ከዓለም ጭንቀት ሁሉ መዳኛው ፍቅር ነውና። ፍቅር ትዕግስትና ማመዛዘንን ወደ ምንምነት የሚቀይራቸው የነጐድጓድ ኃይል ነው። አፍቃሪ ስለራሱ ደህንነት ማሰብ አያውቅበትም፤ የትችት ተራራ ለእሱ ከገለባ ክምር የቀለለ ነው። እንዲያውም ትችት የፍቅሩን ኃያልነት የሚጨምርለት ጉልበቱ ይሆናል።»

ሱፊስቶች

«ዓለም በሙሉ ዕብድ ነው ይለኛል። በእርግጥም ዕብድ ነኝ። አናንተም ደግሞ ዕብድ ናችሁ። ዓለም በሙሉ ዕብድ ነው። ለመሆኑ ዕብድ ያልሆነስ ማን ነው? ይሁንና እነዚህ ዕብዶች ደግሞ እኔን ዕብድ በማለት ይጠሩኛል። ከእነሱ አንዳንዶቹ ለስማቸውና ለክብራቸው ያበዱ ናቸው። አንዳንዶቹ ገንዘብ በመከተል አብደዋል። ሌሎቹ ደግሞ ሥጋን ውበትን እየተከተሉ ያብዳሉ። እሱ ፈጣሪውን ተከትሎ ያበደ ግን በእርግጥም የተባረከ ነው። እኔ እንዲህ ዓይነቱ ዕብድ ነኝ።»

ባንግ አቫድሁት

"የሰው ልጅ ምኞት ገደብ የለሽ ነው። ምኞት በጥም የተቃጠለ ሰው የሚጠጣው ጨዋማ ውሃ ነው፤ ጨዋማ ውሃ የውሃ ጥምን አለማርካት ብቻ ሳይሆን ጥሙ እየጨመረ እንዲሄድ ማድረጉ የማይቀር ነውና። ስለዚህም የሰው ልጅ የእርካታ ምንጩ ከውስጡ ነው፤ በምኞቱ ግን አለመርካታ ብቻ ሳይሆን ስቃዩም እየጨመረ ይሄዳል። እናም ለምኞትህ ገደብ አበጅለት"

ሃይዲገር

"ስለሦስተኛው የዓለም ጦርነት አላውቅም፧ ስለአራተኛው ግን ልነግራችሁ እችላለሁ አራተኛው የዓለም ጦርነት ብሎ ነገር የለም፤ ምክንያቱም ሦስተኛው ሁሉን ነገር ይጨርስዋልና!"

አልበር አንስታይን

"ሰው የሚያፈቅረውን ነገር ይሆናል። ድንጋይ ካፈቀረ ድንጋይ ይሆናል፤ የሰውን ልጅ ካፈቀረ ደግሞ ሰው ይሆናል፤ ፈጣሪን ካፈቀረ ደግሞ... ከዚህ በላይ እንኳን ማተት የለብኝም... አለበለዚያ በድንጋይ ልትወግሩኝ ትችላላችሁ።"

ኦውግስቲን

"በሰዎች ክፉ ተግባርም ሆነ ምግባር ለመፍረድ ስንነሳ የእኛም ክፉነት እየተገለጠ ይሄዳል። ለማንኛውም የሰው ልጅ የምግባር በሽታ ጠንካራው መድኃኒት ፍቅር ብቻ ነው»

ራማያና

"የሰው ልጅ የፈጣሪውን ማንነት ተረድቶ በእሱ ማንነት በምድር ላይ ለመመላለስና የእሱንም ዘላለማዊነት ለመልበስ ዋስትና የሚሆነው ሃይማኖቱ ሳይሆን የተሰጠውን ተፈጥሮአዊ ብቃት ለመግለጥ በፈጣሪ መንገድ ላይ መገስገስ ብቻ ነው።።"

ሂንዱይዝም

«ራስን አለማወቅ ይጎዳል፤ ራስን አለማወቅ ሕይወትን በሙሉ ትርጉም አልባ ያደርገዋል። ሁሉን ነገር ልታውቁ ብትችሉ እንኳ ራሳችሁን ግን አላወቃችሁም፤ የሚገርመው ግን ከእውቀታችሁ በፊት ልታውቁት የሚገባው ራሳችሁን ነበር።"

ኦሾ

«አብዛኛው የሰው ልጅ የሚከተላቸው እምነቶችና በእምነቱ ውስጥ የሚፈፅማቸው ድርጊቶች መነሻቸው ልማድ ነው። እምነት በዕውቀት መገለጥን ካልያዘ የሚጠይቀውም ሆነ ምላሽ የሚያገኝለት ጥያቄ ስለማይኖር ሌሎች ስለሚያደርጉት ብቻ የሚደረግ ከንቱ ተግባር ሆኖ ይቀራል።»

ዜኖች

"የሰው ልጅ ሊኖር የሚገባው ዛሬን ነው፤ ስለነገ እያሰቡ ዛሬን መኖር ዛሬ ልንጨብጠው የምንችለውን ነገር ለነገ አሳልፎ የመስጠት ተግባር ይሆናል። ብዙዎች እምነታቸውን በነገ ላይ በማንጠልጠላቸው ምክንያት ዛሬ እምነታቸው ሊሰጣቸው የሚችለውን በረከት እያጡት ይገኛሉ። "

ዜኖች

"ቀላል፣ የተዋበ፣ ፀጥታ የሞላበት፣ ተደሳችና የተባረከ ሕይወት መኖር የምትሻ ከሆነ የአእምሮን ስግብግብ ጥያቄዎች ጣላቸውና በምትካቸው የልብህ መልሶች ተካባቸው። የአእምሮ ጠቢብነት ነገሮችን እያወሳሰበ ዕለት ተዕለት ጥያቄን መከመር ነውና የሕይወትህ ጌታ ልብህን አድርገው። "

ኦሾ

"ፍቅር በውስጥህ ቦታን ሲያገኝ የውበት መገለጫው ትሆናለህ። ፍቅር የያዘው ሰው ውበት የሚንፀባረቅበት መስተዋት ነው። ምክንያቱም ውበትም ሆነ ነፀብራቁ መነሻቸው ፍቅር ነውና... የሁለቱም ምንጭ ፍቅር ነው።"

ሱፊስቶች

#Abel
@Zephilosophy
@Zephilosophy
2.4K views05:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 20:01:19 ራስን ማታለል (Bad Faith)

በሕይወትህ ለምን ያህል ጊዜ ለውድቀትህ ሌሎች ሰዎችን ወይም ሁነቶችን ወቅሰህ ታውቃለህ? እንዲህ ባይሆን ኖሮ እንዲህ እሆን ነበር' ብለህስ ታውቃለህ? አለቃህ፣ መምህራኖችህ፣ ወላጆችህ የሆነ ነገር እንድታደርግ አስገድደውህ ያውቃሉ?

የሃያኛው ክ/ዘመን ፈላስፋ የሆነው ዣን ፖል ሳርት እነዚህን ሃሳቦች በአንድ ሰብስቦ “bad faith' ብሎ ይጠራቸዋል። ይህም ራስን ማታለልን ያመላክታል። ብዙውን ጊዜ በሕይወት ላይ አማራጭ እንደሌለን ለራሳችን እናሳምነዋለን፡፡ ይህን ያደርግነው እንዲህ ስለሆነ ነው የሚል ምክንያትም ከድርጊቶቻችን ጀርባ እናስቀምጣለን። አሁን ላለንበት ደረጃ ያበቁንን አስገዳጅ ምክንያቶች እና ሰበቦች እንደረድራለን፡፡ ራስን ማታለል በዙሪያችን እስር ቤት የመገንባት ያህል ነው።

ማህበረሰቡ ባስቀመጠልን አስገዳጅ ህጎች አልያም ልማዶች ራሳችንን ወስነን በነጻነት ከመምረጥ እንገደባለን፡፡ ለምሳሌ ሜሴጅ እንደላከልሽ ወዲያውኑ አትመልሽለት” አይነት ተራ ሕጎች ጀምሮ እስከ በዳኛ የተደነገጉ ሕጎች ድረስ - የመምረጥ ነጻነታችን ይገደባል።

እናም ራስን ማታለል (bad faith) የሚጀምረው ለውድቀታችን እነዚህን ህጎች ተጠያቂ ስናደርግና በእነርሱ ውስጥ ስንሸሸግ ነው::

እናም ከማህበረሰቡ ተውስን የምንወስዳቸው ብዙ ጭንብሎች አሉን፡፡ በብዙ የሕይወት ክፍሎቻችን ላይ እንዲህ መሆን አለብህ ስለተባልን ልክ እንደ ተዋናይ ሆነን እንተውናለን፡፡
ነገር ግን ይለናል ሳርት፤ ህግ፣ ደንብ፣ ባህል እና ወዘተ... ከመምረጥ አያግዱንም፡፡ ምርጫዎችን የመምረጥ እና የመወሰን ፈቃዱም በእኛ እጅ ላይ ነው ያለው፡፡

በእያንዳንዷ ቅጽበት፣ በእያንዳንዱ ቀን ምርጫዎች አሉን። በእያንዳንዱ ሰከንድም የወደድነውን የመምረጥ ነጻነት አለን። ይህንን ነፃነት ምንም አይነት ነገር ከእኛ ሊቀማን አይችልም፡፡ ነጻ ለመሆንም የተገባን ነን።

በዚሁ ልክም ለእያንዳንዱ ምርጫዎቻችን ውጤት የምንጠየቀው እኛ ብቻ ነን። ቀድሞውኑ በሚገባ አመዛዝነን ካልወሰንን እና መንገዳችን ወደ መጥፎ መዳረሻ ካደረሰን፣ ከእኛ ውጪ ልንከሰው የሚገባ አካል አይኖርም፡፡ ጥፋታችንንም ከማመን ውጪ ማንም ላይ ማላከክ የለብንም፡፡

ነጻ ነህ ... ነጻነትህን ተጠቅመህ መንገድህን ምረጥ...

ምንጭ-ፍልስፍና ከዘርዓ ያዕቆብ እስከ ሶቅራጠስ
ዝግጅት-ፍሉይ አለም

@Zephilosophy
@Zephilosophy
1.9K views17:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-24 18:31:07 ደራሲ - አዳም ረታ ፣ ስብሀት ገ/እግዚአብሄር ፣ ዳኛቸው ወርቁ ፣ ሰርቅ.ዳ ፣ በዐሉ ግርማ ፣ ባሴ ሀብቴና ሌሎችም በህብረት
4.0K viewsedited  15:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 21:56:02 ቃል
ሮፍናን
@Human_Intelligence
4.5K views18:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-20 21:54:38 Rophnan ft Julian marley
Merkeb
(አርምሞ)


የልቦናን መቅረፅ አብርቶ
የሚጓዝ መች ይሰምጣል ከቶ
ወደ ውስጥ ላየ ለገባው
መርከቡ ሰፊ ነው ከውሀው


ሰው ራሱን ካዳመጠ ከራስ ከታረቀ
የመኖርን ሚስጢር እውነት አወቀ
ልብ ላይ ሁሌም ድምፅ አለ እሱን ተከተለህ
በሶስተኛው በሙሉ አይንህ ታያለህ


@Zephilosophy
@Zephilosophy
4.3K views18:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-05 21:12:04 ጭፍን እምነትን አውልቃችሁ ጣሉ

ምንጭ ፦ የፍልስፍና ሀሁ
ፀሀፊ ፦ በላይ ደስታ

መሪር ሀሳቦችን ለማንሳትና ለመወያየት ካልደፈራችሁ? ሗላ ቀር የሆነውና ከቤተሰቦቻችን የወረስናቸው ልማዶችና አስተሳሰቦች እርስ በእርስ አባልተው ይጨርሱናል፡፡ ስለእውነት ነው የምላችሁ፣ እንደሰው ተፈጥረን እንደድመት የምናልፍ ከንቱዎች እንሆናለን። በየጎጡ ጎራ እየሰራን እንለያያለን:: እምነታችን ሁሉንም የዓለም ህዝብ ካልቀየረ ብለን አክራሪነት ውስጥ ተቻኩለን እንወተፋለን። በንቁ ሀሳባችን ካልተመራን፣ ያው መሪያችን ልማድ ሆኖ መቅረቱ ግልጽ ነው፡፡

በሀሳብ፣ ልማድና እምነት መካከል ሰፊ ርቀት አለ፡፡ በሀሳቡ የሚያምን ሰው ይልቃል። በእምነቱ የሚያምን ግን አዲስ ሀሳብ አይፈጥርም፡፡ ቀድሞ የተፈጠረውን ስርዓት ተቀብሎ ወደ ልጁ ሰፈር ያደርሳል። እንደዱላ ቅብብል ማለት ነው። የዱላ ቅብብል ተወዳዳሪ ስለዱላው ምንም የሚያስበው የለም፡፡ ዱላው ብረት ይሆን እንጨት አያስብም። የሱ ስራ፣ ከኋለኛው አጋሩ የተቀበለውን ዱላ ይዞ ወደ ፊት መሸምጠጥ ብቻ ነው። ከዚያ ከፊቱ ለሚጠብቀው ሯጭ እስኪያቀብል ሳያባራ ይሮጣል፡፡

በእምነትና በባህላዊ ስርዓት ውስጥ የሚኖሩ ህዝቦችም እንዲሁ ናቸው። ከአባቶች የወረሱትን እምነትና ትዉፊት የሙጥኝ ብለው ወደፊት ይሮጣሉ። ለቀጣዩ ትዉልድ እስኪያስረክቡና ህይወታቸው እስኪያልፍ የሚያስቡት አዲስ መንገድ አይኖርም፡፡ አእምሯቸው በጥልቀት እንዲያስብ ፈቃድ አይሰጡትም፡፡ ለዚህ ነው፣ ብዙ እምነት ውስጥ የሚኖሩ ህዝቦች ስልጣኔን የሚሸሹት።

እምነትን ብቻ የሁሉ ነገር ምንጭና መንገድ አድርጎ የሚቆጥር ህዝብ ያየለበት ማህበረሰብ ወይም ሀገር፣ ኋላቀርነቱ እዚያው ኋላ እንደቀረ የሚኖር ይሆናል። ትልቁ ፈተና ደግሞ፣ እምነት ውስጥ የተኛ ህዝብ ኋላ ቀርነቱን እንደጸጋ ማየቱ ነው፡፡ የትኛውም የኑሮ ገጠመኝ ማለትም ድህነት፣ አለመማር፣ አለማወቅ፣ የበታች መሆን፣ ስደት፣ በሽታ፣ ጦርነትና መሰል እልፍ ወረርሽኞች እግር ተወርች አስረውት ጭምር አያዝንም፡፡ እልህ ውስጥ አይገባም፡፡ ለምን እንዲህ ተፈተንኩ ማለትን አይፈልግም፡፡

"የፈጣሪ ፈቃድ ነው ብለን ዝም አልን” በሚል የተለመደ ዋሻ ውስጥ ይደበቃል፡፡ ይህን ለማረጋገጥ፣ ዛሬም ወደ ራሳችን ማየት ነው፡፡ እየወደቅንም ፈጣሪ የምንለውን ሀይል አመስጋኞች ነን። ብንራብ፣ ብንጠማ፣ ፈተናዎች ቢደራረቡብን፤ ጦርነት ውስጥ ብንናጥ ሁሌ እያመሰገንን እናልፋለን፡፡ ለምን በዚህ ሁኔታ ውስጥ ገባን? እንዴትስ መውጣት እንችላለን? ብለን አንጠይቅም። ምክንያቱም "ሁሉም ነገር የፈጣሪ ፈቃድ ነው” በሚለው ራሳችንን እናታልላለንና።

መፍትሔ የምንጠብቀው ከጸሎትና ከፈጣሪ ነው። እጆቻችንን ወደ መሬት አዙረን መዶሻና አካፋ አንይዝም፡፡ ምንም ሳንይዝ አየሩ ላይ ወደ ሰማይ አንጋጠን እንለምናለን። በዛ ጥፋታችን ለፈረሰ ቤት ጥገና የምንጠይቀው ፈጣሪን ነው:: ይህ መንገድ ለሁሉም ነገር መፍትሄ አይሆንም፡፡

ፍጹም አማኝ ሆኖ የተሰባሰበ ህዝብ ስልጣኔ የማይሰራው ለምን እንደሆነ ግልጽ ነው። የተሰባሰበው ሰማያዊ መንግስትን እያሰበ እንጂ፣ በእጁ የጨበጠውን የምድር ህይወት ከግምት አያስገባም፡፡ እየኖረ በመሆኑ ግን፣ የግድ መንግስት ይፈጥራል። የሚፈጥረው የመንግስት አይነት ግን ምድር ላይ ያለውን እውነት ያማከለ አይሆንም፡፡ የተዘበራረቁ መልኮች ይኖሩታል፡፡

የራሱን የህይወት መንገድ እንዲፈጥር ነጻነትን ያልተማረ ህዝብ፣ ጥያቄ አይጠይቅም፤ የተለየ ሀሳብም አያስብም፡፡ ሀሳብ የሚያድገው ደግሞ በፍልስፍና ነው ! በፍልስፍና አስተሳሰብ ያልተገራ ህዝብ በነጻነት ውስጥ ሆኖ የእውቀት ልዩነት የሚፈጥር የሀገር ቅርጽ አይወልድም፡፡ በጥንት ልማድና አሁን ባለው የሀገር ቅርጽ መሃል የተለየ ማንነት አይኖርም።

በልማድና በእምነት ውስጥ ብቻ የሚኖር ህዝብ አንደኛው ችግር ይኼው ነው፡፡ ከዘመን መለወጥ ጋር የሚያድግ ርዕዮት አይፈጥርም፡፡ የእርሱ ጉዳይ ዶግማዎችን እንዳሉ ማስቀጠል ነው፡፡ የባህል ዱላ ቅብብል ላይ የተገደበ ስርዓት ነው የሚፈጥረው፡፡ ባህል ግን ብቻውን ስልጣኔ አይሆንም ፤ ስልጣኔንም አያመጣም፡፡ ባህል የቡድን ባህሪ እንጅ የግለሰብ አስተሳሰብ አይደለም፡፡ የሳይንስ ወይም የፍልስፍና ተግባር ደግሞ ዶግማዎችን ብቻ ማስቀጠል አይደለም።

ኢትዮጵያ ዘመናትን ያስቆጠሩ ሥነቃላዊና የፅሁፍ ፍልስፍናዎች ባለቤት ናት። ከአስራ ሰባተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በፊት፣ ከሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች በተለየ መልኩ በርከት ያሉ የፍልስፍና ስራዎችን በመስራት በቀዳሚነት የምትጠቀሰው በጥንታዊው የግእዝ ቋንቋ ከተጻፉት የፍልስፍና ስራዎቿ መካከል ከፊሎቹን በትውልድ ካናዳዊ፣ በምርጫ ደግሞ ኢትዮጵያዊ የሆነው ፕሮፌሰር ክላውድ ሰምነር ወደ እንግሊዝኛ ቋንቋ በመተርጎም፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲታወቁ እድርጓል። ሌሎች በርካታ በግዕዝና በአረብኛ ቋንቋዎች የተፃፋ የጽሁፍ ስራዎች በጥንታዊ ቤተእምነቶችና ቤተመዛግብት ውስጥ ተቀምጦ አንስቶ የሚመረምራቸውን የሀገራቸውን ጠቢብ በመጠባበቅ ላይ ናቸው።

ፍልስፍና በጥቅሉ የተጻፉትንና በቃል ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፋትን የማህበረሰብ ወጎች፣ ልማዶች፣ ጥበቦች፣ የእውቀት ዘርፎችንና አስተሳሰቦችን፤ በግለሰብ ፈላስፋዎች፣ በአንድ ዘመን ተሰርተው በጽሁፍ የተላለፉትን ስራዎች የሚመለከት ምጡቅ የጥበብ ዘርፍ ነው። በቃል ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፉ ማኅበረሰባዊ ፍልስፍናዎች፤ በተረትና ምሳሌ፣ በምሳሌያዊ አነጋገሮች፣ በዘይቤዎች፣ በቅኔዎችና በወጎች ሊገለጡ ይችላሉ።

ሀገራችን ኢትዮጵያ፣ ገና ያልተጠኑ የበርካታ ጥንታዊ ስነ ጽሁፎች ባለቤት ናት፤ ማጥናትና መመርመር አቅቶን ሌሎች አጥንተው የቅጂ መብቱን ከመውሰዳቸውና የታሪክ ክፍትት ተፈጥሮ በመጪው ትውልድ ተወቃሾች ከመሆናችን ሰፊት፣ ከትምህርት ቤት ጀምሮ፣ በወጣቶች አዕምሮ ውስጥ የምርምር ሀሳቦችን በማንሳትና የዘርፉ ምሁራንም ተገቢውን ጥናትና ምርምር በማካሄድ፣ በየደረጃው ያሉ የትምህርት ተቋማትም፣ የፍልስፍና ጥበብን በትምህርትና በምርምር ስራቸው ውስጥ በማስገባት፣ ወጣቶች ከተለመደው አስተሳሰብ ወጥተው፣ በተለያዩ የፈጠራ አስተሳሰቦች ውስጥ እንዲመሰጡ ማበረታት ወቅቱ የሚጠይቀው አቢይ ስራ ነው፡፡

እየኖርን ባለነውም ሆነ ወደፊት በምንኖረው ዘመን፣ ለአንድ ሃገር አስፈላጊና ወሳኝ ነገሮች ናቸው ተብለው ከሚታመንባቸው ጉዳዮች መካከል፤ ለዘመኑ የሚመጥን የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂና የፈጠራ ውጤት ሊያመነጭ የሚችል ተመራማሪ ትውልድ ማፍራት መቻል ነው፡፡ አዳዲስ የሳይንስ ግኝቶችንና የተራቀቁ የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ሊያመነጩ የሚችሉ ጠይቂ አዕምሮዎች እንዲፈጠሩ ደግሞ፣ በነባሩ ባህላዊ አስተሳሰብ ውስጥ ያሉ ዜጎች፣ አዲሱ ትውልድ፣ የምርምር ሀሳቡን በሚያምንበት መንገድ ያለገደብ፣ እንዲያራምድና እንዲያዳብር መፍቀድ መቻል አለባቸው።

@Zephilosophy
@Zephilosophy
1.6K views18:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 21:29:10 መጥፊያችን ደርሷል

ደራሲ እንዳለጌታ ከደራሲ አለማየሁ ገላጋይ ጋር ያደረገው እጅግ አስገራሚ ቆይታ

ክፍል-1
@Zephilosophy
@Zephilosophy
2.8K views18:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-28 21:28:45
አወዛጋቢው መፅሀፍ በገበያ ላይ ነው!! ገዝታችሁ እንድታነቡት ጋብዣለሁ!!

የተጠላው እንዳልተጠላ
ደራሲ አለማየሁ ገላጋይ

@Zephilosophy
@Zephilosophy
2.3K views18:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ