ነግሬሽ ነበረ ሴት ክብሯን ረስታ ፣ ጭኗን እንዳታምነው ሁሉን ያጣል ብዬ ፣ የሁሉም የሆነው!!! ነግሬሽ ነበረ ውበት ደም ግባትሽ ፣ ሁሉን እንደሚስብ የወንድ ልጅን ዐይን.. ከተበተነበት ፣ እንደሚሰበስብ ነግሬሽ ነበረ... ትንሽ ስትዘነጊኝ ፣ ብዙ እንደማስብ!!! ነግሬሽ ነበረ... ባትሰሚኝም እንኳ ሳሙና ነው ብዬ ፣ የቆንጆ ሴት መልኳ እድፋም ስሜቶችን... አሽታ ስታነፃ ፣ ያበቃል ታሪኳ!!! ነግሬሽ ነበረ ሴት ልጅ ስታማርጥ ፣ ለራሷ ምራጭ ናት በክብር ነው እንጂ... በመውለድ አይደለም ፣ የሚኮነው እናት፡፡ ክብረ ቢስ ህይወቶች ፣ ጣፍጠው አይቀጥሉም የወለዱ ሁሉ እናቶች አይደሉም ነግሬሽ ነበረ እናትነት ስሟ ከክብሯ ነው እንጂ ፣ ከልጇ እንዳልመጣ ወልዳም ምንም ነች ፣ ሴት ክብሯን ስታጣ። ነግሬሽ ነበረ... ሴት ክብሯን ስትጥል ፣ እድሜዋ ይሔዳል የወንድ ልጅ ቤቱ... የሴትልጅ ውበት ነው ፣ ካየበት ይለምዳል፡፡ ነግሬሽ ነበረ... ጭንሽ ሴትነትን ፣ ከቶ እንደማይበልጠው ቁንጅናም ይረክሳል! ብቻውን እንዲቀር ፣ ሁሉም ከመረጠው! ብነግርሽ ብነግርሽ ፣ ባትሰሚኝም ቅሉ "ሰደበኝ" በማለት ፣ ታወሪያለሽ አሉ ልክ ነሽ አንዳንዴ እውነቶች ውሸት ፊት ፣ ስድብ ይመሥላሉ። ሞኝ ሰው ሲመክሩት ሞኝ ሰው ሲነግሩት የቀኑበት መስሎት ፣ በከንቱ ቢታበይ ግን እነግርሻለሁ! ነግሪያት ነበር ስል ቀንቶ ተናገረኝ ፣ ወይም ሰደበኝ በይ። ግን እነግርሻለሁ ግን እመክርሻለሁ ሴት ልጅ ክብሯ ሲጎድል ፣ ውበቷ አይመችም ሁሉም ይመኟታል ፣ ከአንዱም ልብ የለችም!!! በላይ በቀለ ወያ እንደፃፈው @NuEnanbib 6.0K viewsedited 05:04