# የሟቹ_ኑዛዜ ፡ የምንዱቡን ትንፋሽ ፥ ሞት በግፍ ቢነጥቅም ሟች ቀኑን ያጣ ቀን ፥ ገዳዩ አይታወቅም ፤ ፡ አፋኙ ጣረ ሞት አንደበቱን ይዞ ፥ ነፍሱን የነጠቀው በምን ይናገራል ፥ ገዳዩንስ ቢያውቀው ፤ ፡ ብቻ ጀምበር ዕድሜው በመአልቱ ጽልመት ፥ ማልዶ የታገተ እስከ ሽበት ደርሶም ፥ አፍ ሳይፈታ ሞተ ፤ ፡ ምናልባት ምናልባት ፥ እንደ መልካም ዕጣ ድንገት በለስ ቀንቶት ፥ የኔም ቀን ከመጣ ሚጠይቁም ካሉ ያሟሟቱ ነገር ፥ እንዲህ ነበር በሉ . ሲለው መሶብ መስሎ ፥ ጎድሎ እንዳጎደለው ሲሻውም ቀን ሆኖ ፥ ከፍቶ እንደበደለው እድሜውን በልቶ ነው ፥ ዘመን የገደለው" ------------------------//----------------------- ፡ ( ኢዛና መስፍን Ezana Mesfin ) ("የዜማ ናፍቆት" የግጥም ስብስብ፣2010 ዓም) @NuEnanbib 1.0K views21:46