ከአሰልቺው ሰማይ ስር ( Abi.G ) ሰባኪው እንዳለው ፣ የሰው ትርፉ ድካም የእድሜያችን ርዝመት ፣ በእርምጃ አይለካም ቢለካስ ምን ሊኮን? ምኞቱ ሳይሞላ ፣ የሞላ ወንዝ ወስዶት ባጭሩ የቀረ ፣ ህልሙን ውሀ በልቶት ወይ ከናቱ ማህፀን ፣ ማለም ሳይችል ገና በውርጃ መኪና መገጨት የሆነ ፣ የህይወት ፍፃሜው ሳይራመድ ሟቹ ፣ ስንት ይሆናል እድሜው? እግዞ! የተራመደውም ፣ ተጉዞ ተጉዞ መንገድ መርጦ ኑሮ ፣ ፍጥረት ሁሉ እንዳሻው አለመጓዝ ሲሆን ፣ ጉዞው መጨረሻው ስለምን ይጓዛል ? ብልህ ለምን ለፍቶ ፣ ከንቱነት ይገዛል ? እንጃ! ግን በህይወት ፍርጃ ጠንቋይ ቢጠነቁል ፣ የህይወትን ፍጥም መሞቻውን አውቆ ፣ ከሞቱ አያመልጥም ህይወት ርእስ ናት ፣ ሞት ለሚለው ግጥም! ይሁና! ይሄን ያሳብ መና ተፈጥሮም አታጣም ፣ የሚችል ሊያፅናና እድል እጣ ፈንታ ጎኔን እየመታ ወደ ምንምነት ፣ ቢችልም ሊያደርሰኝ ምንምነት ራሱ ምንም ነው ሚሆነው ፣ ከንፈርሽ ሲደርሰኝ!! .. 405 views04:05