Get Mystery Box with random crypto!

ISLAMIC SCHOOL

የቴሌግራም ቻናል አርማ islam_and_science — ISLAMIC SCHOOL I
የቴሌግራም ቻናል አርማ islam_and_science — ISLAMIC SCHOOL
የሰርጥ አድራሻ: @islam_and_science
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 18.51K
የሰርጥ መግለጫ

✍ ጅልከሆንክ ጅል ተከታይ ጀንትል ከሆንክ አስከታይ ትሆናለህ..!
ጅልም ጀንትልም ካልሆንክ ደግሞ አርፈህ በራስህ ዓለም ትኖራለህ..! አንባቢ እንሁን፡፡ለውጥ ከራስ ቢጀመር ...የቸገረን ጥሩ መካሪ ሳይሆን፤
የሰማነውን መተግበር ነው ያቃተን!ጅህልና በሽታ ነዉ፡፡
🎖For any comment T.me/Aisuu_bot
💠Another channal
@IslamisUniverstiy_public_group

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 23

2021-01-17 06:06:13 መራራ እዉነት
ክፍል

....... ሰሚራ ሽኩር

ለናቴ ብነግራት አትፈቅድልኝም ሳልናገር ወደ አንድ እየተሰራ ወዳለ ፎቅ ተሸካሚ እንኳን ቢቀጥሩኝ ብየ አመራሁ

ፎቁን በኩንትራት የያዘዉ ሰዉየ ጆርጂ ይባላል በናቱ አሜሪካዊ ሲሆን በአባቱ ቻይናዊ ነዉ ጥሩ ፀባይ አለዉ አማረኛ በደንብ ይሰማል ለማዉራት ቢከብደዉም እየተንተባተበ ትንሽ ትንሽ ያቃል ለመግባባት አይቸገርም።
....እኔም በፍራት የቤተሰቤን ችግር ነገሬዉ እዚህ ጂብሰም፤ሲሚንቶ፤ኮርኔስ የመሳሰሉ ነገሮችን...... በመሸከም እንዳመላልስላቸዉና የተወሰነች ብር ብትከፍለኝ ብየ አናገርኩት ጆርጂም "አንተኮ ገና ህፃን ነህ አትችልም" ብሎ እንቢ አለኝ እኔም ተስፋ በመቁረጥ እግሬን ዘርግቸ ቁጭ ብየ ማልቀስ ጀመርኩ ጆርጂ በኔ ሁኔታ ልብ ተንክቶ "በቃ እሽ እኔ ትንሽ ገንዘብ እሰጥሀለሁ አንተ ዝም ብለህ ተማር" አለኝ እኔ ግን አልተስማማሁም የላቤን ገንዘብ ነዉ ለእማየ ማብላት ያለብኝ አልኩት እሱም በንግግሬ ተደንቆ አንተ ህፃን አይደለምህ ትልቅ ነህ የትንሽ ትልቅ አለሽ


.....ከዛ ቀን ጀምሬ ከጥዋት ትምህርቴን ስማር እቆይና ከሰአት ከጆርጂ ጋር አዉላለሁ ምግብም አሱ ጋር እመገባለሁ ጆርጂን በጣም እወደዋለሁ እንዳአባትም ይመክረኛል፤አጋዥ መፅሀፎችን ይገዛልኛል ብቻ ደስ የሚል ፀባይ ያለዉ የዋህ ሰዉ ነዉ።

እማየ ሁሌም ከሰአት ቁርአን ቤት ቁርአን ስቀራ የምዉል ይመስላታል ካፏ የማይለየዉ የሁል ጊዜም ምክሯ ሰላትና ቁርአንህን አደራ!!!ነዉ
...እኔም ሰላቴን በሰአቱ እሰግዳለሁ ቁርአኔን ደግሞ እሁድ እሁድ ስራም ትምህርትም ስለማይኖር እቀራለሁ
አንዳንዴ ስራ ስዉል ድክም ሲለኝ ሱቢህ ሲሰገድ እየሰማሁ ለመነሳት ይከብደኛል የዛኔ እማየ በጆክ ዉሀ ይዛ ትመጣና "ትናሳለህ አትነሳም" ስትለኝ አምስት ደቂቃ አልቆይም ስነሳ"
...... ልጆችን ስናሳድግ በኢማናቸዉ ጠንካራ አድርገን ቁርአን እንዲቀሩ፤ሰላት እንዲሰግዱ ካላደረግናቸዉ ተለቀዉ እንደፈለጉ ካደጉ ቡኋላ ሲያድጉ ይስተካከላሉ ማለት ከዝንብ ማር እንደመጠበቅ ነዉ።



ኢማም አሕመድ ኢብኑ ሐንበል በእናታቸው እጅ እንዴት እንዳደጉ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ
“እናቴ ገና በ10 ዓመቴ ነው ቁርኣንን በቃሌ እንድሐፍዝ ያደረገችኝ፡፡ የሱብሒ ሰላት ሳይደርስ በፊት ትቀስቅሰኝ ነበር፡፡ በዚያ እጅግ ቀዝቃዛ በሆነው የባግዳድ ከተማ በለሊት ተነስታ ለዉዱእ የሚሆን ዉሃ አሙቃ ታቀርብልኛለች፡፡ ልብሴን ታለብሰኝና በጉፍታዋና ነሒጃቧ በሚገባ ከተሸፋፈነች በኋላ መስጂዱ ከኛ አካባቢ ራቅ ስለሚልና ጨለማም ስለሆነ እጄን ይዛ መስጂድ አድርሳኝ ትመለሣለች”
እሳቸውም አላሳፈሯትም
ዝሆን እንኳ ቢገረፍ አቋሙን ሊቀይር የሚችልበትን ግርፊያ በስተርጅና ተገርፈው በዓላማቸው ፀንተዋል።
ገራፊያቸው የአንድ ቀኑን ትዝታ እንዲህ ይተርከው ይዟል:- "ከዕለታት አንድ ቀን ቁርአን የአላህ ቃል አይደለም እንዲሉ ተገደው ራሳቸውን በተደጋጋሚ ስተው እስኪወድቁ ድረስ ብዙ እንግልትና ግርፋት ደረስባቸው ጀርባቸው ቀልቶ ሰንበር አውጥቶ ተዝለፍልፈው ሲወድቁ ስመለከት አዝኜ አንድ ኩባያ ውሀ አቀበልኳቸው ቀና ብለው በትኩረት ተመለከቱኝና ዛሬ ፆመኛ ነኝ በማለት መለሱልኝ። አያቹህ የናታቸዉ አስተዳደግ ጠንካራ ኢማን እንዲኖራቸዉ እንዴት እንዳረገ....

ወደ አማኔ ታሪክ ስንመለስ
"እናቴ ለኔ እናት ብቻ አልነበረችም ሁሉ ነገሬ ነበረች ሲያመኝ ከኔ በላይ ታማ ሲጨንቀኝ ተጨንቃ ፤ሳትበላ አብልታ....ነዉ ያሳደገችኝ ዉለታዋን በምን ይሆን የምክሳት ሁሌም አስባለሁ
የናት ዉለታዋ

ቃላት ቢደረደር በብዙ ጋጋታ
መቸ ይገልፀዋል የናትን ዉለታ
የናትን ዉለታ እንዴት ችየ ላዉራዉ
የሁሉም ተምሳሌት መሆኖን አቃለሁ
ሀዘኖን አርቀህ ደስታዋን አብዛላት ብየ እየተማፀንኩ
ከዛ ከጭንቁ ቀን ከዉልደቷ ጀመርኩ
ስትወልድ ያለዉ ስቃይ እንዴት ይገለፃል
ከሀሊቁ በቀር ማንስ ያቅላታል
ያየችዉስ ስቃይ በምንስ ይተካል
ከወለደች በላይ ጭንቀቱ ይብሳል
ከመዉለዷ በፊት ካለዉም ይለያል
እሷ ሳትበላ ልጇን ታበላለች
አልበላም ሲላትም በጣም ታስባለች
ለምን ይሆን ብላ ከባዱን ታዝናለች
ከታመመ ደግሞ እንቅልፏን ታጣለች
በሀሳብ ተጠምዳ ብትሰለሰላለች
እስከሚያድጉ ድረስ በጭንቀት ታያለች

እሰይ አደጉልኝ ነፍስም አወቁልኝ
ስራ ስለያዙ ሀሳቤን አረፍኩኝ
ብላ ሳትጨርስ ምነዉ አመሸብኝ
ምን ነክቶብኝ ይሆን ልጀ የቀረብኝ..
.
.
ከመዉለዷ በፊት የጀመረ ስቃይ
ማብቂያዉ ቢሆን እንጂ እዱንያን ስትለይ
ሌላም ማብቂያ የለዉ
አላህ ያሳምረዉ
ደርቦ ደራርቦ ጀዘዋን ይክፈለዉ!
..... ሰሚራ ሽኩር

....አንድ ቀን ጆርጂ የሚሰጠኝን ገንዘብ ለእማየ ሰጠኋት እማም ከየት አመጣኋዉ ስትል አፋጠጠችብኝ እኔም ሁሉንም ነገርኳት እማየ በኔ ትደሰትብኛለች ብየ አይን አይኖን ሳይ የእማየ አይኖች በእንባ ሞልተዋል ደነገጥኩ እማ ምነዉ እኔ ልጂሽኮ በሀላል እንጂ በሀራም አይደለም ገንዘቡን ያመጣሁት አልኳት እማም እንባዎች እየወረዱ "አቃለሁ የኔ ልጂ ሳሳድግህም ሀላልን እንጂ ሀራምን እንዳትነካ አድርጌ ነዉ" አለችኝ እሽ እማ ምን ያስለቅስሻል ስላት "እኔ የሚያስለቅሰኝ ሁለት ልጆቸን ማሳደግ አለመቻሌ ነዉ አንተን በዚህ በጨቅላ እድሜህ ከሀቅምህ በላይ ስራ ለመስራት ተገደድክ"

......እንባየን መቆጣጠር አልቻልኩም ተይይዘን አለቀስን እማ ለትንሽ ቀን ነዉ ይሄ ሁሉ ስቃይ ያልፋል ብየ ወደ ጆርጂ አመራሁ ጆርጂን ስራ ቦታ አጠሁት ወዴት ሂዶ ይሆን ብየ ስፈልገዉ አማኔ ብሎ አንገቴን ከኋላየ አቀፈኝ በጣም ተግባብተናል የእማየን ሁኔታም አስረድቸዋለሁ

አንድ ቀን ጆርጂ እናትህን አስተዋዉቀኝ ብሎኝ እማየን ላሳየዉ ይዤዉ ወደ ቤታችን አቀናሁ.....

በአላህ ፍቃድ ይቀጥላል

Join
t.me/Islam_and_Science
t.me/Islam_and_Science
8.4K views03:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-16 06:25:43 መራራ እዉነት
ክፍል
....... ሰሚራ ሽኩር

.......ለማወቅ በጓጓ አንደበት የዚህን አላልህም እዚህማ አብረንህ ነበርን እኔ ያልኩኝ እዚህ ሳትመጣ በፊት ቤተሰቦችህ የትና እንዴት ናቸዉ? አንተስ ምን ሁኔታ ላይ ነበርክ?ስል ጠየቁት አማኔም አይኑን ወደ መሬት ወርዉሮ ባዘነ ፊት"ምን ያደርግልሻል የኔ ታሪክ
..... እኔኮ የሚነገር ታሪክ የለኝም በቃ ታሪክ የለኝም! ብሎ ማልቀስ ጀመረ
አባቢ "አንች ልጂ ምን መሆንሽ ነዉ ለምን የሚያስጨንቀዉን ማስታወስ የማይፈልገዉን የትናንት ሂወቱን ትጠይቂዋለሽ ትናንትኮ ታሪክ ሁኖ አልፏል በቃ ሙቷል ላይመለስ አምልጧል ትናንት ጥሩም ሆነ መጥፎ ላይደገም ለዛሬና ለነገ ሂወታችን ትምህርት ሁኖን አልፏል።
የትናንት ሂወቱን እያስታወሰ ባለፈ ነገር የሚያለቅስ ሞኝ ነዉ ትናንት የሆነዉ ሁሉ መሆን ስላለበት ነዉ የምሆነዉም መሆን ያለበት ነዉ! አላህ ከመወለዳችን በፊት ሁሉንም ፅፎታል የተፃፈዉም ተግባራዊ ይሆናል ከኛ የሚጠበቀዉ ሰበብ ማድረስ ብቻ ነዉ።
.... ግን ሀናኔ እንዲህ የሚያስጨንቀዉን ጥያቄ ስጠይቂዉ ሁለተኛ እንዳልሰማሽ ሁለተኛ!" ብሎ ተቆጣኝ እህ አባቢ ምን አጠፋሁ እያልኩ ወደ ክላሴ ገባሁ እማኔና ሪሀና ተከትለዉኝ መጡና አማኔ ይቅርታ አለኝ እኔም ይቅርታ ማለት ያለብኝ እኔ ነኝ ይቅርታ አልኩት "አይ እኔ ነኝ ይቅርታ መጠየቅ ያለብኝ አስቆጣሁሽ አይለል በአላህ ይቅርታ አለኝ እኔም ጣጣ የለዉም ይቅርታ አድርጌልሀለሁ አንተም ይቅርታ አድርግልኝ አልኩት አደረገልኝ ግን ዉዶቸ ተበድላቹህ ይቅርታ አድርጋቹህ ታዉቃላቹህ? ወይም እናንተ ሌላዉን በድሏቹህ ይቅርታ ጠይቃቹህ ታዉቃላቹህ?
ሁሌም አዉቀንም ሆነ ሳናቅ የምንናገረዉ ፤የምንሰረዉ ስራ የማንን ልብ እንደሚሰብር ማንን እንደሚያስቀይም አናቅም ይቅርታ እናድርግ ጣአሙን አድርገን እንጂ አናቀዉም
በአንድ ሰዉ ተበድላቹህ ወይም ተከድታቹህ ይቅርታ ማድረግ እንኳን ማሰብም ሊከብድ ይችላል ነገር ግን
ቂም፤ምሬት፤ህመም...... በዉስጣችን ስንይዝ ራሳችንን እንጎዳለን። ስለዚህ ለሁሉም ነገር ይቅርታ አድርገን መርሳት ጥሩ መፍትሄ ነዉ።


ዉዶቸ ዓለም በአዎንታዊና አሉታዊ ነገሮች የተሞላች ናት፡፡ ከአንድ መልካም ነገር ጎን ሌላ መጥፎ ነገር አለ፡፡ በአንድ መጥፎ ነገር ውስጥም ሌላ መልካም ነገር ይገኛል፡፡ ከዚህም የተነሣ በሌሎች ሰዎች መገፋታችን ወይም እኛ ሰዎችን መግፋታችን አይቀርም፡፡ ይህ አውቀነውም ሆነ ሳናውቀው በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ መከሰቱ የማይቀር ጉዳይ ነው፡፡ ምክንያቱም ሕይወታችን ከሌሎች ጋር የተቋጠረና የተነካካ ነው፡፡ እኛነታችን ሌሎችን ይፈልጋል፡፡ እኛም ለሌሎች እናስፈልጋለን ፡፡ ሁሉም ሰው ከሌሎች የሚቀበለው ነገር አለው፡፡ ለሌሎች ሰጪም ነው፡፡

መሳሳት የሰው ልጅ ባህሪ ነው፡፡ ዳሩ ግን መሳሳት የጥንካሬ እንጂ የድክመት ምልክት አይደለም፡፡ ስህተት የእንቅስቃሴና የሕይወት ምልክት ነው፡፡ ሰለዚህም መሳሳት በየትኛውም የሕይወት ገጽ ላይ ሊከሰት የሚችለው ፡፡ በአንድ ዓይነት ሁኔታ ላይ በተደጋጋሚ መንገድ መሳሳትና ማጥፋት አስቀያሚ ድክመት ነው፡፡ ከተሳሳትን ይቅርታ እንጠይቅ ፡፡ ከተገፋንም በይቅርታ እንለፍ፡፡ ይህ የአእምሮ ብስለትና የመንፈስ ጥንካሬ ማሳያ ነው፡፡

ይቅርታ ማድረግ ጥሩ ነው ጨርሶ መርሳት ደግሞ እጅግ በጣም ጥሩ ነው፡፡



ሰዎች በቀልን ትተው ይቅርታ ማድረግን የማይመርጡበት ምክንያት ዋጋው ስለሚወደድባቸውና የነርሱ ትንሽነትም ስለማይመጥነው ነው፡፡

አማኔ ጋር ይቅርታ ተበብለን አማኔ "ይቅርታሽ ከዉስጥ አይመስለኝም" አለኝ
ሪሀና "አወ ከዉስጧ አይደለም ታሪክህን ለማወቅ ሁላችንም ጓጉተን ነበር"

.....አማኔም "እሽ የኔ ታሪኩ ቢመራቹህም ለወደፊት ሂወታቹህ ትምህርት ይሆናቹሀልና ማወቁ ደስ ካሰኛቹህ ታሪኬን እናግራቹሀለሁ " ብሎ ታሪኩን እንዲህ መናገር ጀመረ

.....አባቴን አላቀዉም እናቴ ታናሽ ወንድሜን እርጉዝ እንደሆነች ነዉ የሞተ።
እናቴ ናት ብቸዋን ጪኗ እስከሚደማ ድረስ ጥጥ እየፈተለች እስከ አስር አመቴ ድረስ ያሳደገችኝ አንድ ታናሽ ወንድም አለኝ ሌላ እህትም ሆነ ወንድም የለኝም
በትምህርቴ በጣም ጎበዝ ስለነበርኩ እናቴን ለማገዝ ትምህርቴን ላቋርጠዉ ብላት እናቴ አይቻልም እኔ የምለፋዉ አንተን ጥሩ ደረጃ ለማድረስ ነዉ ደሞ ኢንሻአላህ ነገ ዶ.ር ሁነህልኝ ባንተ ያልፋልኛል።
....የኔ ልጂ የዛሬን ችግር አትይ ነገ ያልፋል ብቻ አንተ ጠንክረህ ተማርልኝ ትለኝ ነበር እኔ ግን የሷን ልፋት እያየሁ ተቀምጨ መማር ከበደኝ አንድ ቀን ለምን ከጠዋት እየተማርኩ ከሰአት የተለያዩ የጉልበት ስራዎችን እየሰራሁ እናቴን አላሳርፋትም ብየ አሰብኩ ለናቴ ብነግራት አትፈቅድልኝም ሳልናገር ወደ አንድ እየተሰራ ወዳለ ፎቅ ተሸካሚ እንኳን ቢቀጥሩኝ ብየ አመራሁ

ኢንሻአላህ ይቀጥላል

Join
t.me/Islam_and_Science
t.me/Islam_and_Science
8.0K viewsedited  03:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-15 06:23:08 መራራ እዉነት

ክፍል

....... ሰሚራ ሽኩር

አባቢ ጓደኛዉ የሰጠዉን ግማሹን ገንዘብ ይዞ የአማኔን መድሀኒት ለመግዛት በዛዉም አማኔን ቸክ ሊያስደርግ ወደ አዲስ አበባ ይዞት ሄደ

እኛም አላህ በሰላም ይመልሳቹህ እያልን ሸኘናቸዉ ግን ህክምናዉ ቀላል አልነበረም ወደ ስድስት ወር ሀኪም ቤት ክትትል ያስፈልገዉ ነበር ስድስት ወር ቆዩ እኛም ስድስት ወር ሙሉ በዱአ ጠንክረን፤ በናፍቆት አልቀን....... ጠበቅናቸዉ ረዥም ጊዜ ያአላህ! በስድስት ወር ዉስጥ ስንቱን ስቃይ አየንበት እኔ ትምህርቴን ለማቆረጥ ተገድጀ ነበር እማየ ግን አይቻልም አታቋርጭም ብላ እሷ በየሰዉ ቤቱ እንጀራ ጋጋሪነት ተቀጥራ የኔን የትምህርት ቤት ክፍያ መክፈል ጀመረች አባቢ አያቅም ሚስጥር ነዉ በዛ ላይ ጤፍ፤በርበሬ.....አልቆ ደረቅ ቂጣ እየበላን ኧረረረረ ያችን ስድስት ወር ማስታወስ አልፈልግም!

አማኔን አባቢ በስድስተኛ ወሩ ይዦት ሲመጣ አማኔ መሆኑን እስከምንጠራጠር ድረስ ዘንጦ ኢትዮጵያዊ መሆኑ እስከሚያጠራጥረን ድረስ ቀይ ዉብ ፤ ሲያዩት የሚያስደነግጥ ሁኖ በደንብ እያወራ ነበር የመጣ ።




.......ማመን አቃተን ሁላችንም ወደ አማኔ ተጠግተን አማኔ እኔን አስታወስከኝ ሀናን እህትህ ሀናን ነኝ መፀሀፍ ሳነብልህ የነበርኩት ሀናን አስታወስከኝ ስል ሪሀና ደግሞ አማኔ እኔ ሪሀና እህትህ የዛኔ ስተዉን ስትስቅብኝ የነበርኩት እህትህ ሪሀና አለች እማየም አማኔ እኔን መቸም አትረሳኝም እናትህ ስመክርና ስንከባከብህ የነበርኩት አለችዉ.........


አማንም እየሳቀና እያለቀሰ እንዴት እረሳቹሀለሁ ለኔ ብላቹህ መኪናቹህን ሸጣቹህ፤ለኔ ብላቹህ ከሞቀዉን ቤታቹህ ወጣቹህ፤ለኔ ብላቹህ የምትወዱትን ነገር አሳልፋቹህ ሰጣቹህ፤ለኔ ብላቹህ ተሰደባቹህ ለኔ ብላቹህ ያልሆናቹህትን ሆናቹህ .... ሁሉንም አባቢ ነግሮኛል እኔም አስታዉሳለሁ ብሎ ሰብስቦ አቀፈን እኛም እያለቀስን በደስታ ቀወጥነዉ

.....ወድያዉ ጓረቢቶቻችን ተሰብስበሙ የምን ጩኸት ነዉ ብለዉ መጡ እማየም "ልጆች ከደስታ ብዛት እየጫሁ ነዉ ለአላህ ምን ይዋልለታል ልጀ ዳና አማኔ ተሻለዉ ኑ ግቡ አዩት" ብላ ይዛቸዉ ገባች አማኔም ሰላም ካላቸዉ ቡሀላ አንተ አማን ነህ ሲሉ ጠየቁት ያዩቱን ማመን ከብዷቸዉ አማንም በነዛ ደስ በሚሉ ጥርሶቹ ፈገግ እያለ አወ አማን ነኝ ምነዉ ተቀየርኩባቹህ እንዴ አለ እነሱም አይ ......የሚሉት ጠፋባቸዉ ያኔ እብድ ሲሉ አእምሮን የሚነካ ነገር ሲናገሩ እንዳልነበረ ዛሬ ሁሉም አለፈ አልሀምዱሊላህ ምስጋና ለአለማቱ ጌታ የተገባ ይሁን! እያልኩ የአላህ ስራ እየገረመኝ አማኔን በትኩረት መመልከት ጀመርኩ በሀሳቤ እናቱ 4 አመት እሱን ፍለጋ ስትሰቃን ታየችኝ አባቱ በሱ ናፍቆት ሲንገበገብ ሳልኩት እህት ወንድሞቹ ተስፋቸዉ ተሞጦ ሙቷል ሲሉ ሳልኳቸዉ የአላህ ቤተሰባቹ እንዴት ሁነዉ ይሆን ስል አሰብኩ ለስድስት ወር አባቢና አማኔ ከቤት ቢጠፉ የሀዘን ቤት ነበር የመሰለ በዛ ላይ ናፍቆቱ ለአመታት ከቤተሰብ ርቆ እያልኩ ሳስብ አማኔ



..... ፈገግ ብሎ "ሀናኔ ምን ፊቴጋ የሚታይ ነገር አለ አፈጠጥሽብኝ" አለና ሁለት እጆቹን ፊቱጋ አድርጎ ፊቱን ሸፈነዉ
....ሀሀሀ ናፍቀኸኝ ስለነበር ነዉ አታፍጥጭ ካልከኝ እሽ አላፈጥም ብየ ፊቴን አዞሮ ጠቀመጥኩ አማኔ
"እንዴ ሀናኔ እየቀለድኩ ነዉ ይሄዉ እንደፈለግሽ እይኝ" ብሎ ወደኔ ተጠጋ እኔ ግን አኩርፌሀለሁ አልኩት
..."እሽ ምን ላርግ"
አንድ ጥያቄ ጠይቄህ ከመለስክልኝ እዞራለሁ
"እሽ የፈለግሽዉን ጠይቂ የምችል ከሆነ እመልሳለሁ"
እርግጠኛ ነህ ስል ደጋግሜ ጠየኩት እሱም አወ አለኝ ልጠይቀዉ ያሰብኩ ስለቤተሰቡ ሁኔታ የት እንዳሉ ነበር ግን ፈራሁ በቃ ጥያቄዉን ለሌላ ጊዜ እጠይቀሀለሁ ለዛሬ ይለፍህ ስል አባቢ እየሰማ ነበር "ኧረ አንች ልጂ ከምንገድኮ ነዉ የመጣን እሱንም በወሬ አታድክሚዉ ይረፍ ምግብም አልበላንም አቅርቢልን" ብሎን ምግብ ላቀርብ ተነሳሁ


......ብከፋፍት የሚበላ ነገር የለም ለካ እማየ አባየ የሰጣትን ብር ጨርሰዋለች ጤፍ መግዣ አጣ አልገዛችም ለዛ ነበር ደረቅ ቂጣ ለሳምንት ስትሰጠን የነበረ የአላህ መቸ ይሆን ይሄ ችግር የሚያበቃ ስል አማየ ሁለት እንጀራ ከሱቅ በዱቤ ይዛ መጣችና ትንሽየ ወጥ ነበረ አቀረበችላቸዉ አባየ ነይ አብረሽን ብይ አላት


እማየም በቅርብ እንደበላች ነገረቻቸዉ እኔም ቢርበኝም አሁን በላሁ አልኩኝ ሪሀና "አባቢ አዉቀዉ ነዉ ትናንት ምሳ የደረቀ ቂጣ እንደበሉ ናቸዉ ጤፉ ካለቀ ቆይቶል እማየም መግዣ አጣ አልገዛችም ለብዙ ቀን ቂጣ ነዉ እየመረረን የበላን"አለች አይ ህፃን መሆን ሁሉ ነገራቸዉ ግልፅ ነዉ

.....አባቢም "ለምን አልነገርሽኝም"አለ
እማየም ብር ይቸግርሀል ብየ ምናልባት ብናግርህና ብሩን ብትልክልኝ አንተም ሆንክ አማኔ በብር እጥረት የምትጉላሉ መሰለኝ ከዛ የቀረችዉን ዱቄት በርበሬዉ ዘይቱም ሲያልቅ እየጋገርኩ በደረቁ መመገብ ጀመርን ለመሆኑ ብር ተረፈህ እንዴ ስትል ጠየቀችዉ
አባቢም እዝን ብሎ "እንኳን ብር ሊተርፈን ለትራንስፖርት እንኳን አጠን ዳክተሮቹ ናቸዉ የሰጡን" አለ አየህ እኔም እንደማይበቃቹህ ገምቸ ነዉ ብር ላክልኝ ያላልኩህ አለች።

አባቢም "ዉዴ የኔ ባትሆኑ ይቆጨኝ ነበር ይሄ አስተሳሰብሽኮ ነዉ እንድወድሽ ሁሌም እንድናፍቅሽ የሚያደርገኝ" ......አልጨረሰም አማን "ዉይ ፍቅራቹህ ያስቀናል በሉ እኛንም የሚያካትት ወሬ አምጡ" አለ እኔ ከመሀል አማን ግን የድሮዉን ሁሉንም ነገር ታስታዉሳለህ ስል ጠየቁት
አማኔም አወ እዚህ ምን እንዳደረኩ አባቢ ነግሮኛል እኔም አስታዉሳለሁ ልንገርሽ አለኝ ለማወቅ በጓጓ አንደበት የዚህን አላልኩህም እዚህማ አብረንህ ነበርን እኔ ያልኩኝ እዚህ ሳትመጣ በፊት ቤተሰቦቹህ የትና እንዴት ናቸዉ? አንተስ ምን ሁኔታ ላይ ነበርክ? ስል ጠየኩት አማኔም......

በአላህ ፍቃድ ይቀጥላል


Join
t.me/Islam_and_Science
t.me/Islam_and_Science
8.3K viewsedited  03:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-14 06:16:36 መራራ እዉነት
ክፍል

......ሰሚራ ሽኩር

ጓደኛዉ ጊዜ ሳያባክን መጣና ተፈራርመዉ ቤቱን ገዛዉ እኛም እቃችንን ጠቅልለን የኪራይ ቤት ማፈላለግ ጀመርን ከሸጥነዉ ቤት ራቅ ብሎ ሶስት ክፍያ ያለዉ ቤት በጥሩ ዋጋ ተከራየን የሰዉ ወሬ ግን አላስቀምጥ አለን ሁሌም"እንደዉ ይች ሞኝ ባሏ ከየትም ያመጣዉን ልጁን ለማሳከም ቤቱን ሲሸጥ ዝም ትላለች አይ"እያሉ እማየን ማስቀየም ጀመሩ እማየም ሰምታ ባልሰማ ታሳልፋቸዋለች

.....እማየንና አባቢን ለማጣላት ያልፈነቀሉት ድንጋይ የለም እማየና አባቢ ግን የሰዉ ወሬ ስለማይሰዉ በጣም ይተማመኑና ይዋደዱ ስለነበረ እነሱ ምንም ቢያወሩ አልሰማ አሏቸዉ እንደዉም እነሱ ለማጣላት በሚያደርጉት ሩጫ የአባቢና የእማየ ፍቅር ቀን ከቀን እየጨመረ ነበር የመጣ።


.......የአባቢ ጓደኛ ግማሽ ክፍያ ሰጠዉና ግማሹን አሁን የለኝም በሌላ ጊዜ ብሎ ገገመ አባቢ ሰጠኝ ብሎ ቢለምነዉም ጓደኛዉ "ምን የሚገዛህ አጠህ በገዛሁህ ላይ" እያለ ያሾፋል።
... አባየም ለሱ ባልሸጥለት ነሮ ያረብ! ምን አጠፋሁ ምን በደልኩህ....እያለ አምርሮ አነባ!





እኔም አባቢን ለማፅናናት አባቢ ለሱ ባልሸጥለት ነሮ እያልክ አትፀፀት አላህ በተከበረዉ ቁዱስ ቁርአኑ ላይ እንዲህ ይላል ስል ሊያረጋጉት የሚችሉትን ተናገርኩ
" በምድርም በነፍሶቻችሁም መከራ በማንም ላይ አትደርስም ሳንፈጥራት በፊት በመፅሀፉ የተመዘገበች ብትሆን እንጅ ።" የሚከሰቱት ነገሮች ሁሉ ቀድመው ተፅፈዋል ። ብዕሩ ደርቋል ፤ ወረቀቶቹ ተነስተዋል ።

ﻗُﻞ ﻟَّﻦ ﻳُﺼِﻴﺒَﻨَﺎ ﺇِﻻَّ ﻣَﺎ ﻛَﺘَﺐَ اﻟﻠَّﻪُ ﻟَﻨَﺎ

«አላህ ለኛ የጻፈልን (ጥቅም) እንጂ ሌላ አይነካንም፡፡ » በላቸው፡፡
(አት-ተውባህ 51)

የደረሰብህ ነገር ሁሉ ሊዘልህ አይችልም ነበር ፤ የዘለለህ ነገር ሁሉም ሊደርስብህ አይችልም ነበር ። ይህ አስተሳሰብ በልብህ ውስጥ ጠልቆ መግባት አለበት ። ሁሉም መከራና ችግሮች ቀላል ይሆኑልህ ዘንድ ።

ነብዩ ሶለሏሁ አለይሂ ወሠላም " አሏህ የሚወደውን ሰው /በችግር / ይፈትነዋል " ብለዋል ። አባቢ አንተንም በትንሹ የሞከረህ ስለወደደህ ይሆናል

በመሆኑም ቢያምህ ፣ ልጅህ ቢሞት ፣ ንብረትህ ቢወድም፤ጎደኛህ ቢከዳህ አምርረህ አትዘን ። አሏህ እነዚህን ነገሮች እንድከሰቱ አስቀድሞ አዟል ። ውሳኔውም የእርሱና የእርሱ ብቻ ነው ። በዚህ ካመንን ጥሩ ምንዳ እናገኛለን ። ኃጢዓታችንም ይሰረዝልናል ።

እናንተ ችግር የደረሰባችሁ ሰወች መልካም ዜና ይጠብቃችኋል ። ስለዚህ ትዕግስተኞችና በጌታችሁ ደስተኞች ሁኑ ።

ﻻَ ﻳُﺴْﺄَﻝُ ﻋَﻤَّﺎ ﻳَﻔْﻌَﻞُ ﻭَﻫُﻢْ ﻳُﺴْﺄَﻟُﻮﻥَ

ከሚሠራው ሁሉ አይጠየቅም፡፡ እነርሱ (ፍጥረቶቹ) ግን ይጠየቃሉ፡፡
(አል-አንቢያዕ 23)

አሏህ ነገሮችን ሁሉ ቀድሞ እንደወሰነ በፅኑ ካላመንክ ችግሮችን እንደቀላል ማሳለፍ አትችልም ። ባንተ ላይ የሚደርሰው ነገር ሁሉ የተፃፈበት ብዕር ደርቋል ። ስለዚህ በአንተ እጅ ባልሆነና መቀየር በማትችለው ነገር ላይ ለምን የፀፀት ስሜት ይሰማሀል ? ብርጭቆውን ከመሰበር ፣ አጥሩን ከመውደቅ ፣ ጎርፉን ከመፍሰስ ፣ ነፋሱን ከመንፈስ ማዳን እችል ነበር ብለህ ታስባለህ ?! ወደድክም ጠላህም እነዚህን ነገሮች ማስቀረት አትችልም ። ቀድሞ የተፃፈ ሁሉ ይፈፀማል ።
ﻓَﻤَﻦ ﺷَﺎءَ ﻓَﻠْﻴُﺆْﻣِﻦ ﻭَﻣَﻦ ﺷَﺎءَ ﻓَﻠْﻴَﻜْﻔُﺮْ

« የሻም ሰው ይመን፤ የሻም ሰው ይካድ» ፡፡
(አል-ከህፍ 29)

እጅህን ስጥ ፦ ስሜትህን በፀፀትና በቁጭት ከመጉዳቱ በፊት በቀደር እመን ። የምትችለውን ሁሉ ካደረግክ እና እንዳይደርስ የደከምክለት ነገር ከተከሰተ ያ ነገር የማይቀር እንደነበር እመን ። ይህን ባደርግ ኖሮ ይህ ይሆን ነበር አትበል ። ይልቁንም " ይህ የአሏህ ትዕዛዝ ነው ፤ እርሱ የሻውን ሰሪ ነው" በል ።

በእርግጥም ከችግር ጋር እፎይታ አለ ።
ﺇِﻥَّ ﻣَﻊَ اﻟْﻌُﺴْﺮِ ﻳُﺴْﺮًا

ከችግር ጋር በእርግጥ ምቾት አልለ፡፡
(አል-ሸርህ 6)

ከረሀብ በኋላ ጥጋብ ፣ ከጥማት በኋላ መጠጥ ፣ ከድካም በኋላ እንቅልፍ ፣ ከህመም በኋላ ጤና ፤ ከማጣት ቡኋላ ማግኘት ....አለ ። የጠፉት መንገዳቸውን ያገኛሉ ፤ የተቸገረው ችግሩ ያልፋል ፤ ጨለማው በብርሀን ይተካል ።

ﻓَﻌَﺴَﻰ اﻟﻠَّﻪُ ﺃَﻥ ﻳَﺄْﺗِﻲَ ﺑِﺎﻟْﻔَﺘْﺢِ ﺃَﻭْ ﺃَﻣْﺮٍ ﻣِّﻦْ ﻋِﻨﺪِﻩِ ﻓَﻴُﺼْﺒِﺤُﻮا ﻋَﻠَﻰٰ ﻣَﺎ ﺃَﺳَﺮُّﻭا ﻓِﻲ ﺃَﻧﻔُﺴِﻬِﻢْ ﻧَﺎﺩِﻣِﻴﻦَ

አላህም ድል መንሳትን ወይም ከእርሱ ዘንድ የኾነን ነገር (ማጋለጥን) ሊያመጣ በነፍሶቻቸው ውስጥ በደበቁትም ነገር ተጸጻቾች ሲሆኑ ተረጋገጠ፡፡
(አል-ማዒዳህ 52)

በርካታ ማይል የሚያካልለውን ሀሩር በረሃ ካየህ ከእሱ ቀጥሎ ሰፊ ጥላ ያለው ማራኪ አረንጓዴ መስክ መኖሩን ልብ በል ። እንባ በሳቅ ፣ ፍርሀት በመፅናናት ፣ መረበሽ በመረጋጋት ይተካል ። ነብዩሏህ ኢብራሂም አለይሂ ሠላም ሠወች እሳት ውስጥ ሲከቷቸው በአሏህ እርዳታ ሙቀቱ አልተሰማቸውም ነበር ።

ﻗُﻠْﻨَﺎ ﻳَﺎ ﻧَﺎﺭُ ﻛُﻮﻧِﻲ ﺑَﺮْﺩًا ﻭَﺳَﻼَﻣًﺎ ﻋَﻠَﻰٰ ﺇِﺑْﺮَاﻫِﻴﻢَ

«እሳት ሆይ! በኢብራሂም ላይ ቀዝቃዛ፤ ሰላምም ሁኚ» አልን፡፡
(አል-ኢብራሂም 69)

ነብዩሏህ ሙሳ አለይሂ ሠላም በልበ ሙሉነት ፣ በጥንካሬና በፅኑ እምነት ፥
ﻗَﺎﻝَ ﻛَﻼَّ ۖ ﺇِﻥَّ ﻣَﻌِﻲَ ﺭَﺑِّﻲ ﺳَﻴَﻬْﺪِﻳﻦِ

(ሙሳ) «ተዉዉ! ጌታዬ ከእኔ ጋር ነው፡፡ በእርግጥ ይመራኛል» አለ፡፡
(አል-ሹዐራዕ 62)

ነብዩ ሶለሏሁ አለይሂ ወሠላም ከአቡበክር ሲድቅ ረድየሏሁ አንሁ ወአርዷህ ጋር ዋሻ ውስጥ ተደብቀው በነበሩበት ጊዜ ለአቡበክር አይዞህ አሏህ ከእኛ ጋር ነው አሏቸው ። ከዚያም ሰላምና ጥበቃ አገኙ ።

አንዳንድ ሰወች የሚታይባቸው ችግርና መከራ ብቻ ነው ። ይህ የሆነበት ምክንያት ከመኖሪያቸው በርና ግድግዳ ወዲህ ያለውን ነገር ብቻ ስለሚመለከቱ ነው ። ነገር ግን ከነዚያ መጋረጃዎች ባሻገር ያለውን ነገር መመልከት ያስፈልጋል ።

አትረበሽ!ነገሮች ባሉበት መቀጠል አይችሉም ። ቀናትና አመታች ይሽከረከራሉ ። መጭው አይታይም ። አንተ ልታውቅ ባትችልም በየቀኑ አሏህ ያዘዛቸው አዳድስ ነገሮች ይከሰታሉ ። በእርግጥም ከችግር ጋር ምቾት አለ!


አባቢ ጓደኛዉ የሰጠዉን ግማሹን ገንዘብ ይዞ የአማኔን መድሀኒት ለመግዛት በዛዉም አማኔን ቸክ ሊያስደርግ ወደ አዲስ አበባ ይዞት ሄደ

በአላህ ፍቃድ ይቀጥላል

Join
t.me/Islam_and_Science
t.me/Islam_and_Science
8.5K viewsedited  03:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2021-01-13 05:59:16 መራራ እዉነት
ክፍል

....... ሰሚራ ሽኩር

....."አይዞህ እኛ ሁሌም ከጎንህ ነን ይሄን ወርቅ ሽጥና የአማኔን መድሀኒት ግዛ"አለችዉ አባቢ ግን አይቻልም አለ

....እማየም እኔም አባቢ ወርቁ መሸጥ አለበት የግድ የአማን መድሀኒት በዚህ ሳምንት ዉስጥ መገዛት አለበት አልን አባቢ "እና ለመሸጥ ወሰናቹህ" አለን እኛም አወ መከፈል ያለበትን ሁሉ ለመክፈል ዝግጁ ነን አልነዉ አባቢ በፍቅር አይኑ እየተመለከተኝ "ሀናኔ አንች እንኳን በጣም የምትወጂዉን በጣም የምትሳሽለትን ወርቅ ልትሸጪ ተስማማሽ" አለኝ እኔም አብሽር አባቢ አላህ አንድን ነገር አይወስድም ከዛ የተሻለ ሊሰጠን ቢሆን እንጂ አልኩ
.....አባቢም ቡዙ ካቅማማ ቡኋላ አማራጭ ስላልነበረዉ እሽ ብሎ ሊሸጠዉ ሄደ እማየ ከመሄዱ በፊት "ተጠንቅቀህ ሌቦች በዝተዋል እንዳይሰርቁህ" ብላ በተደጋጋሚ ነገረዋለች እባቢም ችግር የለዉም ብሏት ወርቁን ሊሸጠዉ ሄደ እኛም ስንት ይሸጥ ይሆን እያል አባቢን በጉጉት ስንጠብቀዉ ቀረብን ለብዙ ሰአት ጠበቅነዉ አልመጣም ስንደዉል ስልኩ ዝግ ነዉ ሰአቱ እየሮጠ ጊዜዉ እየመሸ ሄደ አባቢ አልመጣም እማየ ምን ሁኖ ይሆን እያለች መጨነቅ ጀመረች


....... እኔም በጣም ተጨነኩ ከመሀል በሩ ተንኳኳ እየሮጥኩ ስከፍተዉ አባቢ ነዉ አልሀምዱሊላህ ደህና መጣህ ደሞ እስካሁን የቆየህ ታክሲ አጠህ ነዉ አልኩት አባቢ ዝም ብሎ እቤት ገባ።

.... እንባ እያነቀዉ አዉፍ በሉኝ ሌቦች ወርቁን ከእጀ መንትፈዉኝ ሮጡ ተከተልኩ ተከተልኩ.... መጨረሻ ላይ ስሮጥ ቆይቸ እነሱም ጠፉኝ እኔም ፖሊስ ጣቢያ ሂጀ ሁኔታዉን ነግሬቸዉ መጣሁ እያለ ማልቀስ ጀመረ
......እማየ ሀዘንናፍቅር ከፊቷ እየተነበበ "ዉዴ!አይዞህ ለኸይር ነዉ ሌባች ይያዛሉ ወርቁም ይገኛል" ስትል አበረታታችዉ አባቢም እንዳልሽዉ ያድርግልኝ አለ እኔም ኧረ አባቢ ለዚህ ደግሞ ታዝናለህ እንዴ ይሄኮ ተራ ነገር ነዉ ሰዉ እንኳን ቁስ ነገር ሂወቱን ያጣ የለ አብሽር አልኩ ዉስጤ ግን እዉነት ለመናገር ከፍቶኛል ያአላህ ካልተገኘስ መድሀኒቱ የኛ የትምህርት ቤት ክፍያ በምን ገንዘብ ሊከፈል ነዉ ስል አሰብኩ ማሰቡ ሲደክመኝ በቃ ለኸይሩ ነዉ አልኩ።

......ነግቶ አባቢ ሌቦቹ ተይዘዉ እንደሆነ እስኪ አዲስ ነገር ካለ ብሎ ወደ ፓሊስ ጣቢያ አቀና እኔም ወደ ትምህርት ቤት ሊሄድ ስዘጋጂ የትምህርት ቤት ጓደኞቸ ተሰብስበዉ ሊጠይቁን መጡ ደነገጥኩ ችግሬን እንኳን ለአላህ እንጂ ለሰዉ ተናግሬ አላቅም ምክንያቱም ችግር ፈቺ አላህ እንጂ ሰዉ አይደለም።
.... ማታ ከመተኛቴ በፊት ያረብ ቢያንስ ለአማኔ መድሀኒት መግዣ የሚሆን ገንዘብ እናግኝ አባቢም ወርቁን አግኝቶ ከጭንቀቱ ይገላገል ስል ነበር .......... ብቻ አላህ ዱአየን ተቀብሎኝ የተወሰነ ብር አዋጠዉ ብርና ፍራፍሬ ይዘዉ መጠዉ አማኔን አይተዉት ሄዱ እንዴት መታመሙን አወቁ ስል ሪሀናን ጠየቋት ሪሀናም እኔ እስር ቤት እንደገበሁ ሲደዉሉ ወንድሟን አሞባት ብያቸዉ ነበረ።
.... ዛሬ ለመጠየቅ መጡ አለች
.... ይዘዉት የመጡት ብር ለመድሀኒት መግዣ ባይበቃም ለመጨመሪያ ይሆናል አልሀምዱሊላህ እያልን ከእማየ ጋር ስንመካከር አባቢ ምንም አዲስ ነገር የለም ብሎ በአዘነ አንደበቱ ነገረን በቃ ቤቱ መሸጥ እንዳለበት ተስማማንና ይሸጣል የሚል ፁህፍ የግቢዉ በር ላይ ለጠፍንበት ለአንድ ለሁለት ቀን ጠያቂ የለም በሶስተኛዉ ቀን አንዱ አኔ እገዘዋለሁ ብሎ መጣ እኛም ሊሸጥ ነዉ በሚል በደስታና በሀዘን ስንጠብቅ በዋጋ አልስማማ ብለዉ ቀረ የአማኔ መድሀኒት በሳምንት ዉስጥ መገዛት አለበት ሳምንት ሊሆን ሶስት ቀን ብቻ ነዉ የቀረን በፍጥነት መገዛት አለበት እያለ አባቢ የሚገዛ ቢጠባበቅ የሚገዛ ጠፋ በአራተኛዉ ቀን ያ ..ይወደዉ የነበረዉ የአባቢ ጓደኛ በርካሽ ዋጋ ልግዛህ አለዉ አባቢም አይቻልም በዚህ ዋጋ አልሸጥም አለ

ብድሩን የለኝም አልከፍልህም ሲል እንዳልነበር አሁን ቤት ሊገዛ ብቅ ማለቱ ገረመኝ እማየም አባቢም ሁላችንም እጃችንን ወደ ላይ ዘርግተን ያረብ ማለት ጀመርን የአማኔ መድሀኒት ለመግዛት ሁለት ቀን ብቻ ቀረን በዚህ ቀን ካልተገዛ ወደ ጤናዉ በፍጥነት እንደማይመለስ ዶክተሩ ተናግሯል ምን እናርግ ወደ አላህ ፊታችንን አዞርን በርግጥም የኛ ጌታ ዱአን ይሰማል ለምኑኝ እስጣለሁ አይደል ያለ በቃ ነገ የሚገዛ ይመጣል ስንል እርስ በርሳችን ተነጋገርን ነገር ግን በነጋታዉ ገዢ ብንጠብቅ ብንጠብቅ የለም አባቢ ተስፋ ሲቆርጥ ለጎደኛዉ ና ባልከዉ ዋጋ ግዘዉ ብሎ በኔ ስልክ ደወለለት የሱንማ ከወርቁ ጋር አብረዉ ወስደዉበታል


ጓደኛዉም ጊዜ ሳያባክን መጣና ተፈራርወዉ ቤቱን ገዛዉ እኛም እቃችንን ጠቀላለን የክራይ ቤት ማፈላለግ ጀመርን


በአላህ ፍቃድ ይቀጥላል

Join
t.me/Islam_and_Science
t.me/Islam_and_Science
8.6K viewsedited  02:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ