2021-10-25 14:19:49
አረቦች አልሰባህ ረባህ (ከንጋት ትርፍ አለዉ) ይላሉ
ከትናንትናዉ እልህ አስጨራሽ ጦርነት ዛሬ ትንሽ የደሴ ከተማ ህዝብ እፎይ ብሏል
ነብዩ ሰዐወ ጦርነትን በጭራሽ አትመኙ ብለዋል ሀቢቡና ሙሀመድ ሰዐወ ከ1400 አመት በፊት የነገሩንን ከሁሉም ያለዉ ወገን ቢሰማ ይሄ ሁሉ ጉድ ባልመጣብን
ዉድና የተከበራችሁ የቻናሌ ቤተሰቦች ጭንቀታችን አሳስቧችሁ የጠየቃችሁኝ ደሴ እንዴት ሆነ ?? ላላችሁ
አልሀምዱሊላህ ሰላም ነን ትናንት የህዝብ መንጋ ሁነዉ መጥተዉ ነበር ግን እስከ አሁን አልገቡም
በጀግኖቻችን መከላከያዉ የአማራ ልዩ ሀይል ፋኖዉ የደሴ ከተማ ወጣት ስንቅ ዉሀ በማቀበል በአንድ ላይ በመተባበር እየመከተ ይገኛል...ጥላትም አፈግፍጓል ግን ገና ይቀራል
የአይጥ እድሜዋ ስንት ነዉ?ተብሎ ቢጠየቅ እንደ ድመቱ ጥንካሬ ይወሰናል አለዉ ይባላል
እናም የወሎ ህዝብ ሆይ እንተባበር!!!
አንዳንድ አክቲቪስቶች እንደ Esat ጋዘጠኛ
ሲሳይ አጌና በወሎ ህዝብ የሚቀልዱ አይነት የተለያዩ ማህበረሰቦች የደሴ ህዝብ እየሸሸ ነዉ ብለዉ ወሬ ሲያናፍሱ እያየን ነዉ
☞በመጀመሪያ መከላከያ ሰራዊት ከመቀሌ ጀምሮ ስንት ከተማ እየሸሸ መጥቶ አይደል እንዴ ደሴ የደረሱት እናም ሴቶችና ህፃናትን ወደ አዲስ አበባ ማሸሹ ይደንቃል ወይ??
☞የደሴ ልጅ ስናድግ መሳሪያን የምናዉ ከፓሊስና ከወታደር እንጂ በእጃችን ይዘን ተኩሰን አላደግንም ጦርነትም ሰምተን አናቅም እና ይሄ ሁሉ ጦርነት ሲሆን ቢሸሽን የሚተችበት ሞራል አለ??ለምን በፊት ጀምረን አስታጥቁን ብንል የሚሰማን የለም ነበር እና በአማራ ክልል ወሎን ባለማስታጠቅ ዋጋ እያስከፈለን ባለ ጦርነት የደሴ ልጅ መወቀስ አይችልም
ሲጀመር የደሴ ከተማ ወጣት 100% የትም አልሄደም
☞የደሴ ልጅና የደሴ ነዋሪ ለይቷል የደሴ ነዋሪ የነበረ ንበረቱን ይዞ ደሴን ክዶ ወደ ተወለደበት ሀገር ሂዷል እስኪ መጀመሪያ ይረጋጋና የምናያቸዉ ይሆናል፡፡ ግን ወላሂ ብየ ልንገራችሁ የደሴ ተወላጆች የምናቃቸዉ ከአዲስ አበባ ከተለያየ ከተማ መጥተዋል..ከዉጭ ሀገር ከአሜሪካ ድረስ መጥተዉ ህዝቡ ጋር መከላከያዉ ጋር ከጎኑ ሁነዋል
☞ለምሳሌ እኔ ዘመዶቼን ሴቶችና ህፃናትን ወደ አዲስ አበባ ልከናል ለምን በዚህ ጦርነት የከባድ መሳሪያ የመድፍ የዲሽቃ ድምፅ በብዛት ስለሚሰማ ሴቶችና ህፃናት ይረበሻሉ ..ህፃናት ሴቶች ሲረበሹ ሲጨነቁ ከማየት ሴትና ህፃናትን ልከን ወንዱ ግን ጦር ግንባር ድረስ እየሄድን ነዉ
የሸገር ሰዉ ሆይ ባይሆን እናንተ መጥታችህ ወሎን ማገዛችህ ቢቀር የወሎ ሴትን ለዘር ጥሩ ነዉ ብላችሁ እንዳታስቀሩብን አደራ
☞ዛሬ በተደረገዉ ስብሰባ ማንኛዉም ነዋሪ በደሴ ዙሪያ ጫካ ቢገኝ ያዉ ወደ አኼራ ይሸኛል ለምን በጫካ እየሄዱ መረጃ የሚሰጡ ሰርጎ ገቦች እየተያዙ ስለሆነ
☞በከተማዉ ዉስጥ አልፎ አልፎ ተኩስ ይሰማል ይሄ ደግሞ ትናንት በኩታበር በተደረገዉ እልክ አስጨራሽ ጦርነት ዉስጥ ብዙ የተደመሰሱ ሲሆን ግን ሰርጎ ገቦች ደሴ ስለገቡ እነሱ እየተገኙ እርምጃ እየተወሰደባቸዉ መሆኑን እወቁ
ግን ብዙ ሰዉ በተለይ ከወሎ ዉጭ ያለ ነዋሪ ያልተረዳዉ ነገር አለ እንዴት አድርጌ እንደማስረዳ አላዉቅም ደሴ ከተያዘ ኢትዮጲያ መንግስት የመቀጠል ያለመቀጠል ጉዳይ ነዉ፡፡
ጦርነቱን እኛ ፈልገነዉ አልመጣም..መጡብን እንጂ ወላሂ የወሎ ህዝብ ከትግሬ ሳይቀር ተዋልደናል ነገር ግን ይሄዉ መጡብን ጥላቻም ሳይሆን ይሄ ራስን ቤተሰብን ከተማን የመከላከል ህልዉና ነዉ ፡፡
ከወል ዉጭ ያላችሁ ወላሂ ብየ ልንገራችሁ እነሱ የመጡት እንዴት አድርጌ ላስረዳችሁ አዲስ አበባ ሰልፍ ወይም ድጋፍ ሲኖር መስቀል አደባባይ የሚሰበሰበዉ ህዝብ አለ አይደል..እነሱም የመጡት መስቀል አደባባይ እንየሚሰበሰብ ህዝብ ሁነዉ እየዘረፉ እያሳደዱ ነዉ ታዳ ይሄን እንደ ህዝብ የመጣ ደሴ ላይ ካልተመከተ ነገ ከነገ ወዳ አዲስ አበባ እንደማይገቡ ምን ማረጋገጫ አለ
ለማንኛዉም የደሴ የኮምቦልቻ ወጣት ሆይ !!!!
ወደ ጦር ግንባር በመሄድ ዉሀ ስንቅ ማቀበል አንዘንጋ...ወላሂ የሚዋጉትን ወታደሮች በጣም ነዉ የሚያሳዝኑት ..ወራሪዉ ሀይል እየዘረፈ የተለያዩ እንስሶችን እየበሉ ሲዋጉ የኛ የወገን ጦር ግን በኮቾሮ ብስኩት እየበላ ነዉ የሚዋጋዉ....የጦር ግንባር ሂደን ስቃያቸዉን አይተን እንምጣ ፡፡ ዛሬ በተለያዩ ግንቦሮች ለመከላከያ ሰራዊት ዉሀና ምግብ እያቀበልን ነዉ...የሚዲያ ወሬና ተግባር ይለያያል የወሎ ህዝብ ሆይ የተግባር ሰዉ እንሁን!!
ሆዳችን ብዙ እሳት ተቀጣጥሏል ይሄን ጦርነት ካሸነፍን ቡሀላ በወሎ የተሰራዉን ቁማር አሻጥር በወሎየዎች በመተባበር ይፈታል ለታሪክ ይነገራል
እንተጋገዝ እናሸንፋለን
አረ ደሴ ደሴ ፣ ገራዶ ገራዶ
ገደል ገባ ጁንታ ፣ ተንዶ ተንዶ
ሞቱን አፋጠነ ፣ የደሴን መሬት ወዶ
ነደደ ወያኔ ፣ ወሎ እሳት ወልዶ
አሁን ደሴ ላይ ያለ ተፈናቃይ ብቻ ከአንድ ሚሊየን ይበልጣል እነሱ ወደ ደሴ መጡ እኛ ግን ሲመጡ ጥለን የምንሄድበት ከተማ የለንም
መቼም ቢሆን ደሴን ጥለን የምንሸሽበት የምንጠጋበት ከተማ የለንም አብሽሩ አላህ ከእዉነት ጋር ነዉ
ድል ለኢትዮጲያ ወሎ ደሴ ኮምቦልቻ
9.7K viewsedited 11:19