Get Mystery Box with random crypto!

ISLAMIC SCHOOL

የቴሌግራም ቻናል አርማ islam_and_science — ISLAMIC SCHOOL I
የቴሌግራም ቻናል አርማ islam_and_science — ISLAMIC SCHOOL
የሰርጥ አድራሻ: @islam_and_science
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 15.55K
የሰርጥ መግለጫ

✍ ጅልከሆንክ ጅል ተከታይ ጀንትል ከሆንክ አስከታይ ትሆናለህ..!
ጅልም ጀንትልም ካልሆንክ ደግሞ አርፈህ በራስህ ዓለም ትኖራለህ..! አንባቢ እንሁን፡፡ለውጥ ከራስ ቢጀመር ...የቸገረን ጥሩ መካሪ ሳይሆን፤
የሰማነውን መተግበር ነው ያቃተን!ጅህልና በሽታ ነዉ፡፡
🎖For any comment T.me/Aisuu_bot
💠Another channal
@IslamisUniverstiy_public_group

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 17

2022-05-09 04:53:08
#ዚክራ_ኦንላይን_የቁርአን_ማእከል
ቁርአንን ባሉበት ቦታ ሆነው በተመቻቸው የቂርአት ሰአት እና የአቀራር ሰርአት ቁርአንን ማንበብ ይፈልጋሉ?እንግዲያውስ ዚክራ የቁርአን ማእከልን ይጎብኙ

በማእከላች የሚሰጡ ትምህርቶች
ቁርአን በነዞር እና ተጅዊድ
ለአዲስ ጀማሪዋች ምቹና ቀላል በሆነ ቃኢዳ
ተውሂድ እና የአቂዳ ኪታቦች
የተርቢያ ትምህርቶች
አነቃቂ ትምህርቶችና ፍሪ ቶክ
ደርሱ የሚሰጠው በ ዙም እና ቴሌግራም አፕሊኬሽን መሆኑ አቀራሩን ምቹ እና ቀላል ያደርገዋል።

ዒልም ፈላጊወች በሙሉ ወደ ማእከላችን ስንጋብዛቹ በደስታ ነው።

አህለን ወመርሀበን ቢኩም እያለን መተው የቂርአት ጥማታቸውን እንደሚያወጡ እና ደስተኛ ሆነው የሙራድወ ሰምሮ እንደሚረኩ ልናበስሮት እነወዳለን።
#ለህፃናት_ልዩ_ቦታ_እንሰጣለን
#ዚክራ_ኦንላይን_የቁርአን_ማእከል

የድረገፅ መገኛችን
ቴሌግራም ሊንክ https://t.me/+2zOmq9mULQ8xYzhk
ዋትሳፕ ሊንክ https://chat.whatsapp.com/L8qdI6iuHjdBIyCmAi6XLs

ስልክ ቁጥር 0931800835
ይሰልሙን አለን እንለወታለን
ያሉንቦታ ውስን በመሆኑ ፈጥነው ይመዝገቡ
##ዚክራ


ዚክራ Online የቁርአን ማዕከል በOnline ለምትቀሩ ተመራጭ በጣም አሪፍ ነዉ ትልልቅ ሰዎች ጀምረዉ ለዉጥ አምጥተዉበታል፡፡ የሚያስቀራዉን ልጅ አቀዋለሁ በዲን እዉቀቱ በፀባይ በባህሪ አላህ አሟልቶ የሰጠዉ ነዉ ...እናም ብትጠቀሙበት በጣም አሪፍ ነዉ
2.0K viewsedited  01:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-03 18:02:58
#ወሎ_ደሴ

የኢድ ሶላት በደሴ
በዳና መልቲሚዲያ በድሮን ካሜራ የተቀረፀ

ምስጋና ዳና መልቲ ሚዲያ

#1443ተኛው_የኢድ_አል_ፊጥር_በአል

https://t.me/Islam_and_Science
2.1K views15:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-02 15:34:17
በዒድ ሰላት ወቅት የተከሰተው ክስተት በክርስቲያኑና በሙስሊሙም መካከል የተፈጠረ አይደለም።

አንዳንድ አካላት ችግሩን ከመንግስት ጋር ለመሰያያዝ መሞከራቸውም የተሳሰተ መሆኑን አረጋግጠናል።

በዒድ ሰላት ወቅት የተፈጠረው ችግር ምን እንደሆነ በስፍራው ከነበሩ በጎ ፍቃደኛ አስተባባሪዎቻችን ደርሶናል። በአንድ ፌደራል ፓሊስ ድንገት (ባርቆብኝ ነው ብሏል) በተተኮሰ አስለቃሽ ጭስ ምክንያት የተፈጠረ ግርግር ነበር።የአስለቃሽ ጭሱ እንደተተኮሰ በቦታው የነበሩ የበአሉ ታዳሚዎች በከፍተኛ ደረጃ ተደናግጠዋል።ወደ ፌደራል ፓሊሱ በማቅናት ይዘውታል።ፓሊሱም ድንገት ባርቆበት እንደሆነ ተናግሯል ሆኖም ህዝቡ ከፍተኛ የሆነ መረበሽ ውስጥ ስለገባ ለመግባባት አልተቻለም።

በመጨረሻም የፌደራል ፓሊሱ በኤግዢቢሽን አካባቢ ወደ ሚገኘው የፌደራል ፓሊስ ካምፕ እዲገባ ተደርጎል።ይህን ተከትሎ ሌሎች ፓሊሶች ከካምፑ ሲወጡ ተኩሱ የፈጠረው ግርግር ባለመረጋጋቱ ችግሩ ሊባባስ ችሏል።

ከዚህ በተረፈ ከስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ኦርቶዶክስ እምነት ተለታዮች ጋር ችግሩን የሚያያይዘው ነገር አለመሆኑ ተረጋግጧል።በመንግስት በኩልም ሆነ ተብሎ የተፈጠረ ችግር አለመኖሩን አረጋግጠናል።በመሆኑም ህዝቡ እንዲረጋ መልእክታችንን እናስተላልፋለን።

የአዲስአበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት


ይሄን video ይመልከቱ አስለቃስ ጭሱን ሲተኩሱ አንስቶ ወደ እነሱ
ወላሂ ጀግና ነዉ
3.2K viewsedited  12:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-02 15:07:12
የኢድ ሶላት በመቀሌ

አላህ ሆይ አገራችንን ሰላም አርገህ ብሄር ዘር ሀይማኖት ከመከፋፈል ተላቀን ከሴረኞች ፓለቲካ ተላቀን....ከትግራይ ህዝብ ጋር አብረን እንደ በፊቱ አንድ የምንሆንበት ኢድ ያርግልን ያረብ ...ኢድን ለወደፊት ለአገራችን ሰላም አንድ ሁነን ዘር ሳንቆጥር ኢትዮጲያን ነን ብለን ለወደፊት የምናሳልፍ ያርገን በማለት የተጨቆኑን በማስታወስ ዱአ በማድረግ እናሳልፍ
ጥጋብ ደስታ ልክ አለዉ ብዙ የተጨቆኑ አሉና

የትግራይና የጎንደር ወንድሞቻችን አብሽሩልን። ይህ ግፍ የቱንም ያክል የዒዱን ደስታና ድባብ ቢያደበዝዝባችሁም ግን ደግሞ በእርግጠኝነት ይወገዳል። ኢንሻ አላህ
3.0K viewsedited  12:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-02 14:52:28
ለጊወርጊስ ሲዘሉ የነበሩ የገራዶ #ፈረሶች ዛሬ ወደ ኢስላም ተመልሰዋል
#ማስታወሻ፦ እነዚህ ፈረሶች ለክርስቲያኖች በዓል ወሎ-ደሴ ላይ ለፈረሰኛው ጊዮርጊስ ማጀቢያ ከገራዶ #ሙስሊሞች በየ አመቱ የሚላኩ ነበሩ። ነገር ግን ከዚህ በሗላ ግን ብዙ ጥያቄ አለን

ባለፈዉ ጥምቀት ላይ አማራ Tv ሲያነጋግራቸዉ አልለምዱሊላህ ታቦታችን በሰላም ገቡ ያሉ ነበሩ፡፡ ዛሬ ግን ለመጀመሪያ ጊዜ እነዚህ ባለፈረሰኞት የኢድን ሰጋጅ አጅበዉ አብረዉ ፉርቃን መስጊድ ሂደዋል፡፡
በዲን ከመጣ ጃሂልም አሊምም ሀብታም ደሀ ሴት ወንድ ልዩነት የለም


ደሴ ሙስሊሙ ማህበረሰብ የነበረን ትንኮሳ በአሚሮች ትዕዛዝ በብልሀት ነበር ያሳለፈው ከሰላት በፊትም ቡኃላ ምንም አይነት ተቃውሞ ሳያሰማ ነበር የተመለሰው


ዛሬ ጎንደር ላይ በኢድ ቀን ሳይሰግዱ በቤታቸዉ ለሚያሳልፉና የትግራይ ሙስሊሞችን በማስታወስ በአልን እናሳልፍ

መልካም ኢድ ሙባረክ

https://t.me/IslamisUniverstiy_public_group
2.8K viewsedited  11:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-05-01 12:36:59 የ13 ዓመት ልጅ ከመደብር ዳቦ ሰረቀ ዘበኛው ይዞት ነበርና ሊያመልጥ ሲል የመደብሩ መደርደሪያ ወድቆ ተሰበረ።
ከዛ ልጁ ተይዞ እንደሌባ ተደብዶቦ ወደ ፍርድ ቤት ሄደ
ዳኛው የወንጀሉን ክስ ሰማና ልጁን እንዲህ ሲል ጠየቀው!
ዳቦ ሰርቀህ ነበር?"
ልጁ - እያፈረ "አዎን ሰርቂያለሁ"
ዳኛው - "ለምን?"
ልጁ - "አስፈልጎኝ"
ዳኛው - "መግዛት አትችልም ነበር?"
ልጁ - "ገንዘብ አልነበረኝም"
ዳኛው - "ከቤተሰብህ ለምን አትወስድም?"
ልጁ - "እናት ብቻ ናት ያለችኝ፥ እሷም በጠና ታምማ እቤት ተኝታለች"
ዳኛው - "ምንም ስራ የለህም?"
ልጁ - "መኪና እጥበት እሰራ ነበር፥ ነገር ግን እናቴን ለማስታመም አንድ ቀን ከስራ ስቀር አባረሩኝ" 
ዳኛው - "ሌሎች እንዲረዱ አልጠየቅኽም?"
ልጁ - "በጧት ነው ከቤት የወጣሁ፥ እንዲረዱኝ 50 የሚሆኑ ሰዎች ጋ ሄጄ ነበር፤ አንድም የሚረዳኝ ሰው ግን አላገኘሁም፤ በቃ መጨረሻ ላይ ይህንን
መጥፎ ውሳኔ ወሰንሁ" 

ጥያቄው ሲጠናቀቅ #ዳኛው ውሳኔ ማስተላለፍ ጀመረ።
እንዲህም አለ
"ዳቦ መስረቅ፥ በተለይ የተራበ ልጅ ዳቦ መስረቅ እጅግ በጣም አሳፋሪ ወንጀል ነው፤ እናም እኛ ሁላችንም የዚህ ወንጀል ተጠያቂ ነን። እኔን ጨምሮ በዚህ ቤት ውስጥ ያላችሁ በሙሉ ወንጀለኛና ተጠያቂ ነን። ስለዚህ እያንዳንዱ በዚህ ችሎት ላይ የታደመና እዚህ ቤት ውስጥ ያለ አስር (10) አስር ዶላር እንዲከፍል ፍርድ ቤቱ ወስኗል። ማንም ሰው ሳይከፍል መውጣት አይችልም በማለት አስር ዶለር ከኪሱ አውጥቶ ወረቀት ላይ መመዝገብ ጀመረ።

በተጨማሪ ዳቦ ቤቱ የተራበ ልጅ ለፖሊስ አሳልፎ በመስጠቱ 1000 ዶላር እንዲከፍል ውሳኔ አስተላለፈ።
ይህ በ24 ሰአት ውስጥ ካልተፈጸመ ፍርድ ቤቱ ዳቦ መደብሩን ያሳሽጋል።

ፖሊስም የተራበ ልጅ ፍርድ ቤት በማቅረቡ 1000 ዶላር እንዲቀጣለት ወሰነ።

የተወሰነለትን ገንዘብ ለልጁ ካስረከበ በኋላ ፍርድ ቤቱ ልጁን ህዝብ ፊት ይቅርታ ጠየቀው! 
የዳኛውን ውሳኔ ከሰሙ በኋላ በችሎቱ ላይ የነበሩ ታዳሚዎች ሁሉ በእንባ ተራጩ።
የልጁ እጅ ላይ የነበረው ሰንሰለት ተፈታለት። ዳኛው እንባ እየተናነቀው ሲያወራ ልጁ ያይ ነበር።
በኛ ማህበረሰብ ውስጥ ያለው የፍትህ ስርዓት ግን ምን ይመስላል? 

የተራበ ልጅ ዳቦ ሰርቆ ቢያዝ ወንጀሉም እፍረቱም ለህዝቡ ነው፡፡
ፅሁፉን ከዚህ ቀደም አንብባችሁት ይሆናል ነገር ግን በኢድ ቀን ብዙ የተራቡ የተቸገሩ ጎረቤቶች አሉ...ደግሞ ዘንድሮ ረመዳን የኑሮ ዉድነት ጣራ ነክቶ የተፆመ ረመዳን ስለሆነ ለኢድ በደስታ ቀን እነሱ ግን ደስታን በሌሎች ብቻ እያዩ የሚያከብሩ ስላሉ እነሱን በተቻለን አቅም መዘየር እንዳለብን እና ዘካተል ፊጥርን መስጠት እንዳንዘነጋ ፡፡


በተጨማሪ ደግሞ ብዙ ሰዉ በረመዳን ከተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያ ራሱን ያገላል በረመዳን ያልተጠቀመዉን ቀዷዉን ለማዉጣት ይመስል ከረመዳን ቡሀላ ማህበራዊ ሚዲያን ከልክ ባለፈ መልኩ ሲጠቀም እናያለን...መቼም ምክንያቱ ሸይጧን ተፈቷል ነዉ....
በረመዳን ላይ አንድ በሚዲያ ፍቅር ተብየ ሞንጨር ያደረገዉ...ሸህየዉን የሚያስቅ ፈትዋ ይጠይቃቸዋል....

ሼኺ በጣም ጥርጣሬ ዉስጥ እገኛለሁ..አንድ የማፈቅራት ልጅ ነበረች እሷም በርግጥ ታፈቅረኛለች የተዋወቅነዉ በFacebook ነዉ በአካል አንተዋወቅም፡፡ ፍቅር ከመሰረትን ለአመት 3 ወር ይጎለዋል ..ረመዳን ከመግባቱ በፊት በጣም እናወራ ነበር፡፡ነገር ግን ረመዳን ሊገባ አንድ ለሊት ከቀረዉ ለት ጀምሮ በፍፁም ሚዲያ ላይ በfacebook በtelegram በimo. የለችም ...ስደዉልም ቁጥሯ አይሰራም ከኢንተርኔት offline ነች
...እናም እኔም ጥርጣሬ የሆነብኝ ነገር እሷን እያሰብኩ በዉስጤ ሰዉ አይደለችም ሸይጧን ነበር ሲጀነጅንህ የነበረዉ እና ልጂቱ ታስራ ይሆናል በማለት ዉዝግብ ላይ ነኝ ሼይህ ሲል
ሼይሁ በሳቅ ....

እናም በሚዲያ ወሬ ብዙዉ በረመዳን ይቀንሳል የሚያቆምም አለ ...በዛዉ ሚዲያን ለመራቅ መሞከር እንጂ ረመዳን ተፈታ ተብሎ በረመዳን ያቆምንበትን የሚዲያ ቀዷን ከማዉጣት እንቆጠብ


ዉድ የቻናል ቤተሰቦች መልካም ኢድ አልፈጥር በአል ተመኘሁ፡፡ ለተጨቆኑ በግፍ የተገደሉ የጎንደር ሙስሊሞችን እንዳንረሳ የሶስት ቀን ሀዘን ብቻ ሆኖ እንዳይቀር....በተጨማሪ የደባርቅ ሙስሊሞች እና
በትግራይ ክልል የሚኖሩ የሁሉም እምነት ተከታዮችን በማስታወስ እናሳልፍ ..ደግሞ በትግራይ ክልል ያለዉን  አስባችሁታል?? ከሁለት አመት በላይ በጦርነት ላይ ናቸዉ የኑሮ ዉድነት አሁን ባለንበት እያየን ነዉ..ትግራይ ክልል እንዴት ፁመዉ እንዴት ኢድን ያከብሩ ይሆን??
በትግራይ ክልል ያሉ ሚስኪኖች እንዴት ይሆን በአልን የሚያከብሩት?? ይሄንን በማሰብ በአልን ብናከብር ኸይር ነዉ...ለምን አይታወቅም ነግ በኔ ነዉ ዱንያ  በደስታና ሀዘን ሀዲድ የምትረማመድ ነች ..ነገ ፈጣሪ የኛን በምን እንደፃፈዉ አናቅም...የጦርነትን ክፋት ችግር ጭንቀትና ስነልቦና ጉዳት እንዴት እንደሚያደርስ
የሚያቀዉ ጦርነትን ያየ ብቻ ነዉ...ጦርነት የከባድ መሳሪያ ድምፅን ያልሰማ ያላየ ከአየዉ ጋር  በጭራሽ ሊረዳ አይችልም ...በዛ ሰዉ ጫማ እስካልተራመድክ ድረስ የዛን ሰዉ ህመም ችግር መረዳት ይከብዳል፡፡
ትግራይ ወራሪ ሀይል መጥፎ ጎናቸዉ ቢበዛም ግን እንደሰበአዊነት እኛስ አላህ ዘራችንን ትግሬ አርጎት ቢሆንስ? አሁን በዚህ ሰአት እኛ ትግራይ ክልል ሁነን በነበረን ምን ይገጥመን ይሆን ?? ብለን ማሰብ መቻል አለብን...ኢትዮጲያ ዉስጥ ለፓለቲካ ጥቅም ተብሎ በዘር በሀይማኖት ዉስጥ ተሰግስገዉ ምንም የማያቀዉን የደሀ ልጅ ሞት አላህ በቃችሁ ይበለን...
አላህ ችግርና መከራን አንስቶ በደለኛን የሚቀጣበት ፣ሰላምና ፍትህን የሚያሰፍንበት ኢድ እንዲሆንል እመኛለሁ!
ሙስሊሞችን የበደሉ የጨቆኑ የገደሉትን አላህ ሂድያ ሰጥቶ ኢስላምን ይወፍቃቸዉ ካልሆነ አላህ በዱንያ የሚታይ የማያዳግም ቅጣት ያስጣቸዉ ያረብ

መልካም የኢድ አልፈጥር በአል ተመኘሁ ..ፁመዉ ተራቡት ከሚባሉት ባርያዎቹ ሳይሆን ለፆመኞች በተዘጋጀዉ በር ከሚገቡት ባርያዎቹ ያድርገን
      ኢድ ሙባረክ!!!


https://t.me/IslamisUniverstiy_public_group
3.2K viewsedited  09:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-29 17:31:16 የደሴው የኹጥባ
=============
የስልጣኔ ማማ የአሸናፊነት ተምሳሌት ጥንታዊቷ የደሴ ከተማ ዛሬ ኮስተር ብላ ውላለች።
በዚህ መልኩ ሹራዋን አድርጋ ደምድማለች። «ለሃገር ሰላም ብለን እንጂ ሙተንም ገድለንም አሸናፊዎች ነን!» ብለዋል።

ዝምታችን ለሃገር ህልውና ብለን ነው። ነገር ግን በሸሪዓችን የአንድ ሙስሊም ነፍስ ከዱንያና በውስጧ ካለው ሁሉ ይበልጣል። ስለዚህ የ1 ሙስሊም ነፍስ እንኳን ከኢትዮጵያ ከዓለምም ይበልጣል። የ40 ሙስሊሞች ነፍስ ሲሆን ደግሞ…!


እስኪ ይህን ድንቅ የጁሙዓህ ኹጥባቸውን ተጋበዙልኝ።

ረመዳን 28, 1443 E.C

https://t.me/Islam_and_Science
3.5K viewsedited  14:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-29 10:06:10
#ሙስሊም_ማለት_እንደ_አንድ_ስጋ_ነው

ያኔ ለፍልስጤም እንደዛ ስንጮህ ምን አገባችሁ? ይመለከታችኀል? ስትሉን የነበራችሁ ያው ዛሬ እነሱም ፍልስጤሞች የኛ መነካት አስጨንቋቸው እየጮሁልን ነው ስለ መስጅዶች መደፈር ስለ ሸሂዶች እያወሩልን ነው ...ኢስላም ላኢልሀኢሏህ የሚል አካል ከተነካ አንድ አካል ነዉ...ምን ትሉ ይሆን??


ኢስላም ማለት፦ ጦርነት ሲያውጁበት
የሚጠነክርና ሲተውት ደግሞ የሚስፋፋ
ቀደውትም አቃጥለውትም የማይበረዝ
ጠንካራ መመሪያ ያለው ትልቅ ሐይማኖት ነው ።


https://t.me/Islam_and_Science
6.9K viewsedited  07:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-04-28 20:06:28
ያሳዝናል!
4.0K viewsedited  17:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ