2022-04-27 23:13:35
<<የእብድ ገላጋይ ድንጋይ ያቀብላል>>
አሚር ሰይድ
ራዕይ በተግባር የሚቀረፅ ህልም እንጂ በአእምሮ ብቻ የምናስበዉ መዳረሻ አይደለም፡፡
አንድ ልጅ እናቱ ጋር ይኖራል ከዛም እንቁላል ይሰርቃል እናቱ ዝም አለችዉ ከዛ በሂደት የሌላ ሰዉ ዶሮ ይሰርቃል ከዛም ሌባ ሲባል እናቱም ስትቆጦ
ልጁም"" እናቴ ምነዉ በእንቁላሉ በቀጣሽኝ ዶሮ ባልሰረኩ "" አላት..
ምን ለማለት ፈልጌ ነዉ ሞጣ ላይ ባደረጉት ድረጊት ስላልተቀጡ አሁንም በእነሱ አልፈረድም
የእኛ ዝምታ ጥግ ደረሰ
የእነሱ ጥጋብ ሞልቶ ፈሰሰ
ችግሩ ከራሳችን ነው ጠንካራ ሁኖ ማሳየት አቃተን ተጠራቅመን የአገሪቱ ከግማሽ በላይ ነን እያሉ ወሬ ስም ብቻ ...የአሁን ዘመን ሙስሊም እሰዉ ቤት የሄደ እንግዳ ይመስል መሽለጥለጥ ማሽቃበጥ ይወዳል፡፡ የሀይማኖት መሪ ተብየዎች በተለያየ ጊዜ ሙስሊሞች ሲገደሉ ሲፈናቀሉ ለሙስሊሙ ከመድረስ ድምፅ ከማሰማት ይልቅ ከመንግስት ሹመኛ ጋር ፎቶ መነሳት ይቀላቸዋል፡፡ጠና ቢል ቢሰሩ ሰላማዊ ሰልፍ ወይ በየመስጊዱ ተቃዉሞ ከዛ ቆፍጠን ያለ የአቋም መግለጫ አንብቦ ይበተናል ሙስሊሙ ቁጣዉን በሰልፍ በመስጊድ ባነር አሰርቶ ፎቶ ተነስቶ በሚዲያ ይለቃል ከዛ ይረሳል በዛዉ ተድበስቦሶ ያልፋል፡፡
ከመንግስት ጎን ይለጠፉና የእብድ ገላጋይ ዲንጋይ ያቀብላል ነዉና ነገሩ መንግስት የጠቀሙ መስለዉ ሙስሊሙን ግን እንዲጎዳ ያደርጋሉ፡፡
☞በሂደት የ ጎንደርን መስጅድ ለመገንባት እና ወንድሞቻችንን ለማቋቋም ተብሎ ገንዘብ ይሰበሰባል ....ዲኑን እየተጫወቱበት ያሉ የሴት ሊቀመንበር ሙነሺዶች ስለ ጎንደር ጥቃት ነሺዳ አዘጋጅተዉ ለአንድ ቀን ይለቀሳል....ከዛ በቲሸርትና በባነር የጎንደር ሙስሊሞች ህመም የኔም ህመም ነዉ ይባላል....ከዛስ .....ከዛማ ዝም ዝም ነዋ ሌላ ምን ይፈጠራል፡፡ ሙስሊሙ ልቡ በዱንያና በሴት ፍቅር ታዉሯል አዉርቶ ይቀራል ከዛ እነሱ እንደ ስለት በአመት አንዴ የሚፈልጉትን አጀንዳ ያስፈፅማሉ፡፡
☞የሚገርመዉ አሁን ድረስ ብሄርን ከእስልምና የሚያስበልጥ መኖሩ ነዉ ...የዛሬ 2 አመት በፊት በፁሁፍ ስለአማራ ክልል ሙስሊም ፅፌ የአማራ ክልል የሚኖሩ ሙስሊሞች ተችተዉኝ ከቻናል ፁሁፉን ለመሰረዝ ተገድጄ አጥፍቸዋለሁ ..የዛን ጊዜ የተናገርኩት በሁለት አመቱ በጎንደር ሙስሊሞች ላይ ደረሰ ...ምን ዋጋ አለዉ
በፊት ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ
አሁን ምን ያደርጋል ድስት ጥዶ ማልቀስ
እናም እኛ ሙስሊሞች የምናየዉ የዛሬን እና የነገን ብቻ ነዉ እንጂ ከትናንት ወዳ ምን ነበር? ከነገ ወዳስ የዛሬ አመትስ ምን ይፈጠራል?ብለን ማሰብ ስለማንችል እነሱ ግን ለወደፊት 50 ወይ 60 አመት ፕላን አዉጥተዉ ሲንቀሳቀሱ በእነሱ ወጥመድ እንወድቃለን፡፡
ስለ ኢትዮጲያ የምንሰማዉ የ13 ወር ፀጋ ነገር ግን የምናየዉ የ13 ወር ለሙስሊም ጥላቻ ነዉ፡፡
☞ግን የጎንደር ሙስሊሞች በረመዳኑ በጥይት ያስፈጠሯቸዉ በአደባይይ ኢፍጣር ላይ የታቀደ ነበር ..ግን በቀብሩ ጀመሩት እንጂ ..ግን ይሄ የአደባባይ ኢፍጣር እኔ ብዙም አልተዋጠልኝ ጉዳቱ ግን አንደ ጎንደር ያሉ ሙስሊሞችን ዋጋ አስከፍሏል፡፡
እኛ ሙስሊሞች የምንዋረደዉ በሱና በኸይር ስራ መሸቀዳደም ትተን ከሌሎች ሀይማኖት ተከታዮች ጋር ፉክክር ስንገባ ነዉ ዉድቀታችን መታወቅ አለበት፡፡ አሏህ በተከበረ ቅዱስ ቁርአኑ በዱንያ እነሱ እንደሚደሰቱ ግን በአኼራ እንደሚቀጡ ነግሮናል እነሱ በስኳር መንፈስ መንገዱን አደባባዩን እንደፈለጉ ሲጠቀሙበት እኛ ሙስሊሞች እነሱ ጋር ምን አፎካከረን?? የነብዩ ሱና ይበልጣል ወይስ ከአነሱ ጋር ፉክክር??
☞በደሴ በነበረዉ ኢፍጣር አይቻለሁ ሴቶች እንደ ኢድ ልብስ ለብሰዉ ተኳኩለዉ ፊታቸዉን በቡርሽ ቦርሸዉ ነበር የመጡት እናም በዛን ጊዜ ታዳ በዛ የአይን ዚና የእጅ ዚና የአፍ ዚና ወዘተ ወንጀል መሰራቱ ይቀራል ወይ?? በአደባባይ ኢፍጣር ወንድ ሴት ፊት ለፊት እየሆነ ሲያፈጥሩ አይተናል ይሄ የነብዩ ሱና ነዉ ወይ??
☞የኢፍጣሩ ብር ከተለያዩ ባንኮች እስፓንሰር ተደርጓል ..በወለድ የሚሰሩ ባንኮች ለዚህ ኢፍጣር ሰጥተዋል ...ግን ይበቃል ወይ?? ይሄ ጥያቄዉ ለአሊሞቻችን ነዉ
☞ በተለይ ሴቶች በTik tok በfb youtube ለመልቀቅ ነበር አመጣጣቸዉ...ብዙ ሰዉ የሄደዉ ማለት ይቻላል ብዙዉ ኢንተርኔት ላይ ተጥዶ tik tok እና fb ላይ ነበር
☞ ከፍጥሪያዉ ቡሀላ አንዳንድ ጀመአዎች በተለይ የአህባሽ አቂዳ የሚከተሉ ለብቻቸዉ ተገንጥለዉ ወንድ ከሴት ተቀላቅለዉ መንዙማ ከፍተዉ ሲጨፍሩ አይቻለሁ ...
ይሄ ሁሉ ማስረጃ በስልኬ video አለኝ ግን ሁሉም በሚዲያ ግልፅ ማድረግ አግባብ አይደለም፡፡
መዉሊድ የተጀመረዉ ቀስ በቀስ ነዉ ወደ ሰዉ ልብ የሰረፀዉ ..የኛም ህዝብ ይሄ የአደባባይ ኢፍጣር በአመት አንዴ በሆነ ቁጥር የሚመጣዉ ትዉልድ ሱና ነዉ ብሎ እንዳይዘዉ ያሰጋል
እናም አላህ ካደረሰኝ ለሚመጣዉ አመት ረመዳን ከአደባባይ ኢፍጣር ተብየ አዲስ የመጣ አንድነትን ለማሳየት ተብሎ ብዙ መዘዝ ይዞ ለሚመጣ እኔ አልሳተፍም...መታወቅ ያለበት ይሄ የራሴ ብቻ አመለካከት ነዉ፡፡
☞ በፊት ከዛሬ 3 አመት በፊት ጀምሬ ሙነሺዶች የያዙት አቋም ከባድ ነዉ ነቢይ እያሉ ሌላ ነዉ እቅዳቸዉ እል ነበር...በዚህ የተነሳ ብዙ ሰዉ ይወቅሰኝ ነበር...ይሄዉ ዛሬ አሊም የሚሰማ ጠፍቶ ፈተዋዉም ደአዋዉም ከሙነሺዶች ሆነ ...እኔ የሚገርመኝ በተለያዩ tv ቻናሎች ስለኢስላም ሀይማኖት ሲባል እነሱ ይቀርባሉ ..ግን የክርስቲያን ዘማሪዎች ክርስትናን ወክለዉ ቀርበዉ አያቁም እነሱ አምላክ ነዉ ብለዉ ለያዙት ጥርት ያለ ስራ እየሰሩ ነዉ በtv program ወሬ የለም...የኛ ሙነሺዶች ግን በተለያየ Tv ቀርበዉ ሲበጠረቁ እያየን ነዉ ...ነሺዳና ሙዚቃ መለየት የማንችልበት ዘመን ደርሰናል...አሁንም ስለጎንደር ሙስሊሞች ነሺዳ አዉጥተዉ አንድ ደቂቃ አስለቅሰዉ ያስረሱናል፡፡
ራዕይ በተግባር የሚቀረፅ ህልም እንጂ በአእምሮ ብቻ የምናስበዉ መዳረሻ አይደለም፡፡
ብቻ ከባድ ነዉ ብዙ ማለት ይቻል ነበር መፃፍ ሳልፈልግ ጊዜ አስገድዶኝ ነዉ ..ትናንት ዛሬም ጎንደር ደዉየ ነበር የሚሰማዉ ወላሂ በጣም ከባድ የሚያስለቅስ ነዉ ...
ዛሬ የረመዳን 27 ለይል ነዉ ሌላ ማድረግ ቢያቅተን ሳንተኛ በዱአ እንገዛቸዉ ...አላህ ይሰማን ይሆናል ኢንሻ አሏህ
በዱአ የጎንደር ሙስሊሞችን እንዳንረሳ
አዉፍ በሉኝ በችኮላ በ30 ደቂቃ ዉስጥ ያለዝግጅት የተፃፈ ነዉ....አደራ አደራ ለጎንደር ሙስሊሞች ዱአ እንድናደርግ
https://t.me/IslamisUniverstiy_public_group
4.7K viewsedited 20:13