Get Mystery Box with random crypto!

ISLAMIC SCHOOL

የቴሌግራም ቻናል አርማ islam_and_science — ISLAMIC SCHOOL I
የቴሌግራም ቻናል አርማ islam_and_science — ISLAMIC SCHOOL
የሰርጥ አድራሻ: @islam_and_science
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 18.51K
የሰርጥ መግለጫ

✍ ጅልከሆንክ ጅል ተከታይ ጀንትል ከሆንክ አስከታይ ትሆናለህ..!
ጅልም ጀንትልም ካልሆንክ ደግሞ አርፈህ በራስህ ዓለም ትኖራለህ..! አንባቢ እንሁን፡፡ለውጥ ከራስ ቢጀመር ...የቸገረን ጥሩ መካሪ ሳይሆን፤
የሰማነውን መተግበር ነው ያቃተን!ጅህልና በሽታ ነዉ፡፡
🎖For any comment T.me/Aisuu_bot
💠Another channal
@IslamisUniverstiy_public_group

Ratings & Reviews

3.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-06-22 15:30:35 የጁሙአ ስጦታ 2


#ቢስሚከ_ነህያ_አል_ወዱድ



በ #ዉድ እና #ሁብ  ያለው ልዪነት ምንድነው
ምን ያክልስ ከአሏህ ስሞች ጋር እየኖርን ነው??!!!
وَذِكۡرَىٰ لِلۡمُؤۡمِنِینَ

https://t.me/+-zHkXQeSZdc4MjY0
1.7K views12:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-22 15:30:00 የጁሙአ ስጦታ

#ቢስሚከ_ነህያ አልገፉር


በ #ገፋር #ገፊር #ጋፊር ያለው ልዪነት ምንድነው
ምን ያክልስ ከአሏህ ስሞች ጋር እየኖርን ነው??!!!
https://t.me/+-zHkXQeSZdc4MjY0
1.6K views12:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-16 21:33:44 እናም ከሁሉም አቀላቀልኩት ከሚዲያ ጠፋ ስላልኩ ነዉ በቃ የማየዉ የምሰማዉ ልቤን ነክቶኝ ልተንፍሰዉ ብየ ነዉ...ወደዋናዉ አጀንዳ ስመለስ ለወደፊት ደሴ ላይ ስለHIV positive ትዳር የማገናኘቱን እና ያለባቸዉ መድሀኒት እንዲወስዱ ለማድረግ እና ከታይታ የፀዳ ለአላህ ብለዉ ብቻ የሚሰረትን ተኮር ያደረገ በተለይ የተቸገሩና Hiv pos ጋር ያተኮረ የሆነ ተቋም ለመመስረት በስልክ እየተወያየን ነዉ እስካሁን ሂደቱ ጥሩ ላይ ነዉ እናሳዉቃለን...ከብር ማሰባሰብ ምናምን የሌለበት ነዉ ...ሰዉነት ግንባታ ጋር የተያያዘ ነዉ ....እናም ከደሴ ከተማ  ዉጭ ያላችሁ  ወይም በደሴ ያላችሁ እንደዚህ ወገን ለመርዳት በተለይ hiv pos የሆኑት ጋር ትኩረት ያደረገ ንያ ካላችሁ በዚህ bot

T.me/Aisuu_bot T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot T.me/Aisuu_bot

አሳዉቁኝ በጣም ከባድ ነዉ ግን እኔ ባለሙያዎች በስልክ ስለማገኛቸዉ  ሂደቱን እንዴት እንደሆነ አስረዳችሆለሁ መስጊዶች ላይ ያተኮረ ስለሚሆን ሀሳብ አካፍላችሆለሁ በዚህ bot አሳዉቁኝ

T.me/Aisuu_bot T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot T.me/Aisuu_bot


ለማንኛዉም ገንቢ አስተያየት በዚህ bot ይቻላል
ግን ስድብ ነቆራ አልፈልግም ምክር እቀበላለሁ፡፡ከምር ስድቡ ምኑ ነዉ ከሚዲያ ያራቀኝ ብቻ በማስረጃ አስተያየት መላክ ይቻላል

T.me/Aisuu_bot T.me/Aisuu_bot
T.me/Aisuu_bot T.me/Aisuu_bot
2.3K views18:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-16 21:33:02 አሁን እኔ በምኖርበት ከተማ ደሴ ከባድ ሁኗል፡፡ ወሎየ የቆንጆ ሀገር እየተባለ Hiv ተስፋፍቷል፡፡
በዚህ ሰሞን አንዲት ልጅ ብቻ ተረድታኝ ደሴ ላይ ትልቅ ስራ እየሰራን ነዉ ፡፡የሚገርማችሁ ከ9 እስከ 12 ክፍል ተማሪዎች hiv ያለባቸዉ በጣም ብዙ ናቸዉ ግን ራሳቸዉን የለብንም ብለዉ አሳምነዋል  እነሱን በምክር
መድሀኒት እንዲጀምሩ እያረገች ነዉ ያለችዉ አላህ እድሜዋን ይጨምርላት፡፡ የአዲስ አበባን አላቅም ሰፊ ስለሆነ ወሎ ጠቅላላ ከተሞች በተለይ ደሴ በጣም ልቅ ተሁኗል፡፡ የአሊሞች ሀገር ወሎ በፊት ድሮ ቀረ አሁን ወሎ የቆንጆ ሀገር እየተባለ ብዙ ሴቶች hiv እየተገኘባቸዉ ነዉ፡፡ በነገረችን ላይ አላህ ተዉበቱን ይስጣችሁ ሸይጧን አሳስቷችሁ ዚና ላይ የወደቃችሁ ወንድም ሴቶች ራሷችሁን ተመርምራችሁ ብታቁ ጥሩ ነዉ...ለወደፊት ሚዲያ ላይ መፃፍ ከቻልኩ የማሳዉቃችሁ ይሆናል ጊዜዉ ከብዷል...እኔ ለራሱ ደንግጬ ሂጄ ተመረመርኩ ..እናም hiv በመመርመር ራሳችንን ብናቅ ጥሩ ነው፡፡

እኔም ለወደፊት መስጊድ ኢማሞች ጋር መጅሊስ ድረስ ደርሶ ቋሚ የሆነ Hiv pos የሆኑትን የማገናኘት ስራ ወንዱ ራሱን እንዲያጋልጥ የማድረግ ጥረት እያረኩ ነዉ ኢንሻ አላህ ጫፍ ላይ ደርሻለሁ አላህ ያሳካዉ

ልላችሁ የፈለኩት አሁን በhiv pos ሰሞኑን ለማገናኘት ጥረት ስናደርግ ያወኩትን ትዳር ማማረጥ ያበዛችሁ ሀሳባችሁ ለብራይድ ለሰርግ ብቻ የሆናችሁ ሴቶች በተለይ ከ22 አመት የሆናችሁ ሴቶች በምሳሌ በእዉነታ ላስረዳችሁ ብየ ነዉ ሰከን በሉ ..

እኔ የማቃቸዉ ብዙ ወንዶች አሉ ትዳር ይፈልጋሉ ግን የወር ገቢያቸዉ ከ4,000 እስከ 6,000 የሆነ ግን እንዴት ብለን እናግባ ?? የቤት ኪራይ አስቤዛ ወጥቶ  እንዴት ይበቃል ነዉ የሚሉት ወላሂ ከባድ ጊዜ ነዉ፡፡


የሚገርመኝ ሴቱ ሷሊሁን ኢማን ያለዉን ትዳር ስጠን ብሎ ዱአ ያረጋሉ አንዳንዴም ሰምታችሁ ከሆነ በመስጊድ መዋጮ ጥሩ ትዳር እንዲሰጠኝ ወርቄን ብሬን ሰጠሁ ይላሉ ..ግን በስንት ዱአ ባሉን ሲያገኙ የሰጡትን ወርቅና ብር በ10 አባዝተዉ ባላቸዉ እንዲሰጣቸዉ ይመኛሉ

የህንድ የቱርክ አማረኛ ፊልም ላይ ያለዉን ትዳር እርሱትና በኪራይ ቤት በአንድ ክላስ በ5000 ብር የወር ገቢ ያለዉ ጋር ለመኖር ራሳችሁን ብታዘጋጁ ይሻላል፡፡ካልሆነ ይሄ የኖሮ ዉድነት ወንዱ ትዳርን እየሸሸ ነዉ ያለዉ...
ለሚመጣዉ አመት የመንግስት ስራ ቅጥር የለም ተብሏል፡፡ በጣም ከባድ ነዉ ዩኒቨርስቲ ላይ ስራ ስንይዝ እንጋባለን የተባለ ቃል ኪዳን ፈረሰ ማለት ነዉ ጎበዝ....በተጨማሪ ወንድ 2016 የመንግስት ስራ ባገኝ አገባለሁ ያለ አያገባም ማለት ነዉ፡፡እናም ሴቶች በtiktok በyoutube በህንድ ፊልም በአማረኛ ፊልም ያያችሁትን ትዳር አትመኙ ሰከን ማለት ያስፈልጋል፡፡

ሴቶች እባካችሁ ባህሪያችሁ አቋማችሁ አንድ ይሁን እቤት ጨዋ አደበኛ ..ትቤት እዉጭ ደግሞ ሌላ ..ለትዳር የሚፈልጋችሁ ሌላ አይነት ባህሪ አታሳዩ ..እንደ እስስት የራስህን ባህሪ ሌላዉ ጋር መመሳሰል ለህሊና ከባድ ነዉ በቃ አንድ ባህሪ የማይቀየር ያዙ ይጠቅማችሆል ወንዱንም አታወዛግቡ


እዚህ ቻናል ያላችሁ  ከ6እስከ10 ክፍል ያሉ ሴቶች ልጆች እህት ያላችሁ በጣም ተከታተሉ ስለዚና ቦይ ፍሬንድ ሀራም መሆኑን አስተምሩ፡፡ምን ገጠመኝ መሰላችሁ የአክስቴ ልጅ 7ክፍል ተማሪ ነች ከክላሳ ልጆች ጋር ትግባባለች ጠይቂያት ስትነግረኝ እነሱ ክፍል 42 ሴቶችአሉ ከእነዚህ ዉስጥ 37 የሚወዱት ደብቀዉ የሚያወሩት boyfrind አላቸዉ፡፡
የሚገርመዉ የወንድ ቁጥር አናሳ ሁኖ እንዴት ብየ ሳስበዉ ሴቶች እወቂ አንቺን እወድሻለሁ እያለሽ የሚያወራሽ 5 ወይ 4 ሴት እወድሻለሁ ሊል ይችላል ተብሎ ይገመታል፡፡ እናም ከ7-10 ያሉ ልጆች ጋር ይሰራ
ለምን የጉርምስና ምልክት የሚጀመርበት ስለሆነ፡፡
ማወቅ ያለብን ሴት ልጅ በ9 አመቷ የወር አበባ ታያለች ወንድ ደግሞ በ15 አመቱ ነዉ የዘፈር ፈሳሽ ማየት የሚጀመርዉ.. ተረዱኝ ይሄ ማለት በአመለካከት በአስተሳሰብ በስሜት ደረጃ የ6 አመት ሴት ልጅ ከ12 አመት ወንድ ልጅ ጋር እኩል ነች ማለት ነዉ፡፡ የ18 አመት ሴት ልጅ ከ24 አመት ወንድ ልጅ ጋር እኩል አስተሳሰብ አላት ማለት ነዉ...እናም ሴትን ልጅ 9 አመቷ ነዉ ወይም ገና 14 ወይ 15 አመቷ ነዉ ህፃን ነች ማለት ዋጋ ያስከፍላል፡፡ አኢሻ ረዐ ነብዩ ሰዐወ በስንት አመቷ እንዳገባች የምናቀዉ ነዉ እናም ሴቶች በእናታችን አኢሻ ረዐ እድሜ ከደረሰች ልጅ ነች ማለት ራስን ማሞኘት ነዉ ለአቅመ ሂዋን ደርሳለች በኢትዮ ህግ 18 አመቷ በ2ተባዝቶ መሆኑን አንዘንጋ


አንድ ቤተሰብ አለ 10 ክፍል እግል ትቤት የሚማር እኔ የማቃት ጅልባቢስት ነች የምላቸዉ ስናያቸዉ ልብሱን ለብሰዉታል አንገታቸዉን ደፍተዋል ግን በቃ ስልካቸዉን ከፍታችሁ ብታዩት ሞዴላቸዉ ቲክቶከሮች ናቸዉ ..እነሱ እንደ ቲኩተከሮች ሰርተዉ አስቀምጠዉታል በቲክቶክ አይለቁት አላህን ሳይፈሩ ቤተሰብ ፈርተዉ ትተዉታል ግን ቤተሰብ ባይኖር እንደ ለቀቁት ነዉ የሚቆጠረዉ እናም እባካችሁ ሴትን ልጅ ስታሳድጉ  እንደ እህት ሁናችሁ ቢሆን አሪፍ ነዉ፡፡

ደግሞ አሁን ለሴቶች ትልቅ አደጋ የዚና መስፋፊያ
የሆኑት ጀመአ ,በጎ አድራጎት ማህበር, የቲም እንከባከብ, አሮጋዉያን እንደጉም,የተቸገረ እንርዳ የሚል ብዙ ኢስላማዊ ጀመአዎች በሁሉም ከተማ አሉ
..እኔ ስማቸዉን መጥራት አልፈልግም የአደባባይ ሀቅ ነዉ በየመስጊዱ በሁሉም ቦታ ከተሞች አሉ ሴቱ ወንዱ አንፀባራቂ ለብሰዉ ሴቱ የዉበት ዉድድር የወጣ ይመስል ተበጃጅቶ ..ጀመአችንን ለማጠናከር እየተባለ
☞ በየመንገዱ ሲዋክ መሸጥ
☞ ቡና እያፈሉ መሸጥ
☞ሴቶች የወንድ ጫማ እስከመጥረግ
☞ ወንድ ሂዶ ሴቷን..ሴቷ ደግሞ ወንዱን የሆነ ነገር ይዞ ግዛኝ ማለት
☞ ወንድ ባለበት ሱቅ 4ሴት ወይ ከዛ በላይ ሴት ያለበት ሱቅ ሰበብ ብሎ ወንድ እየሄዱ በይሉኝታ ብር መቀበል
☞ በየአዳራሹ ተቀላቅሎ መሰብሰብ
☞ የአረጋዉንያ ቤት ማፅዳት እየተባለ 6ሴት 3ወንድ እየሆኑ አብሮ መስራት መሳቅ ምን ይሉታል??
እኔ የሚገርመኝ የሴቶቹ አይደለም ወላሂ እናት አባት እህት ወንድም መንገድ ለመንገድ ስትገራፈጥ ስታሽካካ እያየ መፍቀዱ ነዉ..,
ቆይ እስኪ መንገድ ለመንገድ ለጀመአ ማጠናከሪያ እየተባለ ሲዋክ ወዘተ ከመሸጥ መጀመሪያ የእናት የአባት የጎረቤት የዘመድ ሀቅ ጠብቀሻል

ግልፁን ከተነጋገርን ይሄ ጀመአ አጅር የሌለዉ ንያዉ ሙሀላጣን የሚያስፋፋ የማወራትን ልጅ በምን መንገድ ላግኛት ካፌ ይሻላል ሌላ ቦታ?? ተብሎ ይታሰብ ነበር በፊት ዛሬ ግን በጀመአችን ወርሀዊ ስብሰባ የገቢ ማሰባሰቢያ ስም መገናኘት ነዉ ወዳጄ በኢስላም ስም ብዙ ካባ የለበሱ ስራዎች በዝተዋል፡፡ እኔ ጀመአ መቃወሜ አይደለም ግን የትኛዉ ነዉ ከሙሀላጣ የፀዳ ወንድና ሴት የማይቀላቀልበት አላህ ብለዉ የሚሰሩ??
ለአንድ ኪሎ ሩዝ የ10 ቤተሰብ ፎቶ ማንሳት ካሜራ ካልያዙ አይሰጡም..ለአላህ ብለዉ ያለካሜራ አይንቀሳቀሱ በቃ አለ አይደል የሆነ እስልምና በነዚህ ጀመአዎች ሲመዘን እንጃ ነገን ያስፈራል፡፡ እህቴ ሆይ በደንብ እሰቢበት ካለሽበትም አባል ከሆንሽም በደንብ እሰቡበት
1.9K viewsedited  18:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-16 21:32:34 ቆይ ግን ምንድን ነዉ ነገሩ??
       አሚር ሰይድ

   በቃ መፃፍ መናገር አስጠልቶኝ ሰልችቶኝ ነገሮችን እያየሁ ከአቅም በላይ ሁነዉ ዉስጤ እየተቃጠለ ብዙ ነገሮችን እያለፍኩ እና በቻልኩት አቅም ከሚዲያ ርቄ በተቻለኝ  አቅም በቻልኩት ብቻየን እየሰራሁ ነዉ ግን አንድ እጅ አያጨበጭብም ግን አሁን ዘመን ካለ ሙስሊሞች ጋር የኢንሻ አላህና የአላሁ አክበር ከማለት ዉጭ ወደ ተግባር የማይሄዱ ጋር ከመስራት ብቻ መስራት ይሻላል፡፡

በቃ ለሴት የተጣመመ መጥፎ አመለካከት አለህ ምናምን ስድብ ወቀሳ ሲበዛ ከሚዲያ ራሴን አራኩ ግን በቃ ነገሮች አያስችሉም

ዛሬ ወረረኝ በቃ አለ አይደል በጣም ልቤን የነካኝ በጣም ያሳዘነኝ ነገር ገጠመኝና ለመፃፍ ተገደድኩ፡፡
በጂልባብና በኒቃብ ዙሪያ ከምር ከባድ ነዉ ..ጅልባብ ኒቃብ የሸፈናቸዉ ነገሮች እየከበዱ ትክክለኛ ለባሾችን በኛም በሙስሊሙ ለሌላም ሀይማኖት አያጋለጥናቸዉ ነዉ  እያዮቸዉም ነዉ ፡፡

!!!ሴቶች ሆይ እባካችሁ ከአረብ ሀገር ስትመጡ አትልበሱ በቃ ኢትዮ ኤርፓርት ስደርሱ አዉልቁትና ስታምኑበት ልበሱ...ሴቶች ሆይ ኢማን ይጨምራል ይቀንሳል ኢማናችሁ ሲጨምር ወይም አንድ ሁለት ኪታብ ስትቀሩ ዲኑ የገባችሁ መስሏችሁ ኒቃብ ጅልባብ ለብሳችሁ አላህን የማይፈራ ሴት ጓደኛ ይዛችሁ ወይም የቱርክ ልብስ ወይም በራሳችሁ ሳይዝ አሰፍታችሁ መልበስ ስትፈልጉ ኒቃብን ጅልባብን አታሰድቡ እባካችሁ፡፡ ከለበሱ ቡሀላ ኢስላም ከሚሰደብ እባካችሁ በቃ አዉልቁትና እንደገና የጂልባብ የኒቃብ ትርጉሙ ጥቅሙ ሲገባችሁ ልበሱት፡፡
..,አላህን ፍሩ ማለቱ ከቃላት ማባከን ዉጭ ለዉጥ አላመጣም በቃ አላህን አታስቆጡ ዲነል ኢስላምን አታሰድቡ...ኢስላምን መጥቀም  ባንችል በኛ እንዲሰደብ ለምን እናደርጋለን???

ዛሬ ጁምአ የገጠመኝን ልንገራችሁ
እኔ የምኖርበት ሰፈር ቤተክርስቲያን በቅርብ አለ ጠዋት ስወጣ ብዙ ሙስሊም ሴቶች ፀበል ሲያስጠቅሙ ሲገቡ እኔ ለስራ በጠዋት ነዉ ከቤት የምወጣዉ መቼም መንገድ የማያሳየዉ የለም አያቸዋለሁ፡፡ ጠዋት ጠዋት እየመጡ ሳገኛቸዉ እኔ አረ አላህን ፍሩ በቁርአን መጀመሪያ ሞክሩ የሚሰማ የለም ኢንሻ አላህ ብሎ ከማለፍ ዉጭ.. ግዴታ ማድረስ ስላለብኝ አይቶ ማለፍ ወንጀል ነዉ በቻልነዉ አቅም እናገራለሁ...

ዛሬ ያየሁት ግን በቃ ለአቅል ከበደኝ ሁለት ኒቃብ የለበሱ ሴቶች እኛ ሰፈር ያለ ቤተክርስቲያን እናታቸዉ ወይ ዘመዷን ይሆናል ይዘዉ ሲገቡ አየሁ ደነገጥኩ ...ግን ወደ ቤተክርስቲያኑ ሲገቡ እዛ የነበሩ ሰዎች ስልካቸዉን አዉጥተዉ ፎቶ ሲያነሷቸዉ አየሁ   .. ወደ ቤተክርስቲያኑ አልገባ ጁምአ ነበር ጀለብያ ለብሻለሁ ጀለብያ ለብሼ ብገባ የነዛ ሰዎች ካሜራ ዉስጥ እገባለሁ ምን እንደሚያደርጉ ስለማይታወቅ...እስከምትወጣ ወደ 1 ሰአት ያክል ጠበኩ አልወጡም እኔም ከዛ አካባቢ ተንቀሳቀስኩ ... ዛሬ በአይኔ አየሁ ግን ከአሁን በፊትም ይገባሉ አላገጠምኝ ማለት ነዉ፡፡

እና ምንድን ነዉ ነገሩ???ሊታወቅልኝ የሚገባዉ ጅልባብ ኒቃብን ተቃዉሜ አይደለም ግን በጅልባብና በኒቃብ ጀርባ ብዙ ከኢስላም ያፈነገጡ ነገሮች አሉ... ትክክለኛ ኒቃብ ጅልባብ ለባሽ በነዚህ ፎርጅድ ለባሾች አብረዉ እየተወቀሱ አንገታቸዉን እየደፉ ነዉ፡፡


ከምር ጊዜዉ ከባድ ነዉ ብዙ የማቃቸዉ ወንዶች ኒቃቢስት ጅልባቢስት ነች ብየ አግብቻት እንዲህ እንዲህ ሆን እያሉ ብዙ ነገሮች እየሰማን አሁን ዘመን ላይም እያየን ነው...ያኒቃምን የጅልባብን  ትርጉሙን ሳያቁት የሚለብሱትም ግራ እየተጋባን ነዉ፡፡

አሁን ላይ እሷ ሷሊህ ነች ኢማን አላት ወይም ኢማን አለዉ ማለት ይከብዳል .. አፍ ሞልቶ የኔ ልጅ ወይ የኔ እህት እተማመንባታለሁ ማለት ከባድ ነዉ....እኔ እንደሚመስለኝ
ኢማን የሴት ልጅ..ሷሊህ የወንድ ስም ነዉ ወዳጄ ..እከሌ ኢማነኛ እሱ ሷሊህ ነዉ ማለት የማይቻልበት ዘመን ላይ ነን ..
ሷሊሀ ነች ሳይሆን በግልባጩ ጧሊሀ የሆነበት ተጨባጭ እያየን ነዉ፡፡


አሁን ሴቱ እሁድ ተጋብቶ ከወር ቡሀላ ብትፈታ ችግር የለባትም
ሀሳባቸዉ ብራይድ ሰርግ እንጂ ነገን ከነገ ወዳስ ትዳር ላይ እንዴት ነዉ ብለዉ ብዙዎች አያስቡም በተለይ ከ22 አመት በታች የሆነች ሴት፡፡
የሴት ኢማኗ የሚለካዉ ሰርጓ አካባቢ ነዉ በፊት ጅልባብ ለባሽ ኒቃብ ናቸዉ የተባሉት ለሰርጋቸዉ ኢማናቸዉ እንደ ወራጅ ወንዝ ወደ ታች ይፈሳል ልባቸዉ ላይ አይረጋም፡፡

የአማረኛ የቱርክ ፊልም እያዩ  በኑሮ ዉድነት እዳዉን ያየ ወንድ ሰርፕራይዝ ምናምን ነዉ ሀሳባቸዉ እንጂ ትዳሬ የምትል ሴት እንጃ እየጠፋች ነዉ፡፡ ወንዱም በሴቱ ባህሪ ማግባት ባለመቻሉ ዝሙት ላይ እየወደቀ ነዉ

አንድ ነገር ሴቶች ላስታዉሳችሁ ነገሮች አሁን ወንድን ልትረዱ አልቻላችሁም  የኑሮ ዉድነት
የክርስቲያን ወንድ በ6000 ደመወዙ ማግባት ይችላል፡፡ የሙስሊም ወንድ ግን ከሴቱ ፍላጎት አንፃር 12,000 ደመወዝ ይዞ ማግባት አይችልም፡፡
በነገራችን ላይ ፍቅር ወንድም ሴትም እወዳታለሁ እወደዋለሁ እንጂ ይወደኛል ትወደኛለች ማለት ራስን ማሞኘት ነዉ፡፡ብዙ ያፈቀረ ሰዉ በህይወትህ ምን ተሳስተሀል ቢባል ማፍቀሬ ነዉ የሚለዉ ፍቅር እወዳታለሁ እወደዋለሁ በሉ እንጂ ይወደኛል ትወደኛለች ብላችሁ ራሳችሁን አታሳምኑ በራሳችሁ ብቻ እርግጠኛ ሁኑ....

በተጨማሪ በዚህ 3ወር ዉስጥ Hiv positive የሆኑትን ትዳር ለማገናኘት በሚል ከእነሱ ጋር እየሰራሁ ወላሂ ከባድ ጊዜ ላይ ነዉ ያለነዉ...
አዲስ አበባ,ደሴ,ባህርዳር,ጎንደር,ጅማ,ድሬድዋ,አፋር ክልል,ኦሮሚያ ክልል
ወዘተ ከተማ ላይ ከተለያዩ ሙስሊሞች ነርሶች ጋር ለማገናኘት ጥረን ነበር፡፡
ከባድ ነዉ የሰማሁት ለአቅል የሚከብድ ነዉ
አዲስ አበባ ሆስፒታሎች ደሴ የተለያዩ ከተሞች ላይ ያሉት በብዛት ከወንድ ብዙ እጥፍ ሴቶች ናቸዉ፡፡

አዲስ አበባ የሚያገናኝ ጀመአ ነበሩ እነሱን ስጠይቅ እንኳን Hiv pos ወንድ ኖርማል ወንድ ሴቶችን ለማገናኘት ጀምረን ለትዳር ዝግጁ የሆነ ወንድ አጣን ነዉ ያሉኝ...አሁን አቋም ያለዉ ወንድ የለም የሚያጮልቅ የሚያደባ እንጂ ሴቱ በምላስ ፍቅር ተተብትቧል ግን መቼ ድረስ???

አሁን በተለይ ሴቶች hiv pos የሆኑ እኔ እንኳ አሁን ለማገናኘት የማቃቸዉ ብዛትና ከተለያዩ ሆስፒታሎች ያገኘሁት መረጃ አለቅል ስለሚከብድ ዝምታ ይሻላል..አሏህ ለነዚህ ሴት እህቶች ይድረስላቸዉ፡፡ የሚገርመዉ ብዙ hiv pos ወንድ ወጣት ገና ከ16-25 እድሜ ያለዉ ይበዛል እነሱ የሚሉት አቅም የለንም ነዉ፡፡ ደግሞ አቅም አለን የሚሉት ስናገናኝ 1ሳምንት አዉርተዉ  ስልካቸዉን ጥፍት በቃ ለምን በሴት ልብ እንጫወታለን???
Hiv pos የሆኖት ብቻ ሳይሆን ወንድ ሆይ!!! የትዳር process አገባሻለሁ እያልክ እድሜ ህልሟን ተስፋዋን አታጨልምባት ተስፋ አትስጥ ቶሎ ወስኑ ቀልብ አንስበር

ነገሮችን ስናጠና ወንዶች hiv ሲገኝባቸዉ ራሳቸዉን እየደበቁ በዚና ሴቶችን እያስያዙ እያገቡ እንደሆነ 90% እርግጥ ሁኗል፡፡
1.6K views18:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-15 06:46:14 አዎ ! እሱ ጋ ያመኛል መጽሐፍን ዉስጥ አንዳንድ ሀሳቦች ፦
___

➫ ሁልጊዜ እሮሮ የሚዘበዝቡ፣ ሁልጊዜ ሰው ማጣጣል ላይ የተመሰጡ ሰዎች፣ ሁልጊዜም አልተሳካልን ዓይነት ደረት የሚመቱ፤ ለውድቀታቸው ሰው የሚወቅሱ ሰዎች፣ ለመውደቃቸው ኃላፊነት ከማይወስዱ ጋ አትወዳጅ ” ( ገጽ 17 )

➫ ደካማነት ምቹ ስፍራ ሲያገኝ እና ጊዜ ሲደላደልለት የሚያብብ ደዌ ነው። ( ገጽ 25 )

➫ መልካም አድራጎት የሚገዝፈው መልካም አድራጊው በየሰበቡ ካልፎከረበት ነው። ( ገጽ 28 )

➫ ወደ በጎ መለወጥ ብዙ ጠመዝማዛ መንገድ አለው። እንደ መበላሸት ቀላል አይደለም። ( 31 )

➫ አንዳንድ ትናንት ትናንት ላይ ብቻ አይቆምም። ዛሬያችንን የፈለገ ከትናንት አርቀን ሰቅለነዋል ብንል ፣ ጥለነው ብዙ መጥተናል ያልነው ትንናት ነጋችን ላይ በሁለት እግሩ ቆሞ እናገኘዋለን። ( ገጽ 49 )

ፍቅር ማለት ለሚያፈቅሩት ሲሉ ከማይችሉት ጋ መታገል እንጂ የሚያሸንፉትን ማሸማቀቅ አይደለም። ( ገጽ 59 )

➫ ከአማኝ ጥቅማጥቅማችን አንደኛው ከአቅማችን በላይ የሆነ ሁነት ሲጋረጥብን ፈጣሪ ላይ ሙጥኝ ማለት አይደል ?” ( ገጽ 65 )


➫ ለራስ ሰው አለመድረስን ያህል አርፋጅነት የለም። ( ገጽ 70 )

➫ ሴት ልጅ ትታለልልሃለች እንጂ አታታልላትም። ( 72 )


➫ ፍቅራችን ለምናፈቅራቸው እንድንጠነቀቅ ካላደረገን ፍቅራችን የእውነት ላለመሆኑ ምስክር ነው። ( 95 )

➫ ሰው በዕድሜ ብዛት ማስተዋል ከቻለ የሚማረው ነገር አለመፍረድን ነው። ( 96 )

➫ የበዳይን ምክንያት ሳንጠይቅ በደልን ከምንጩ ማድረቅ እንዴት ይቻላል ?” ( 99 )

➫ ችግራችንን የምናይበት መንገድ የገዘፈ ስለሆነ ነው ከችግራችን በታች የምንሆነው። ( 104 )

➫ በአለም ላይ ስሜቱን እንደሚከተል ሰነፍ የለም፤ ስሜቱን ብቻ መከተል የሰው ባሕሪ አይደለም፡፡ ከስሜት እውነት ይበልጣል ፣ እውነት ነው በጊዜ ብዛት የማይደበዝዘው ፣ ስሜት ዘለቄታዊ ደስታን አይፈጥርም። ማደግ ማለት ደግሞ እውነትን እየመረረንም ቢሆን የመዋጥ ክህሎትን የማዳበር ሂደት ነው። ( 118 )

➫ አሸናፊነት የሚመጣው ተጋጣሚ የሚፈልገውን ባለመስጠት ነው። የምንፈልገውን የምናገኘው እራሳችንን ከምንፈልገው ነገር ባለማሳነስ ነው። ( ገጽ 130 )

➫ ራስን የመሆን እና ራስን የማወቅ ጥግ ራስን መቀበል ነው። በዙሪያችን ያሉ ሰዎች እንዲቀበሉን እኛ ቀድመን ራሳችን መቀበል አለብን። ደካማ ሰው ነው ድክመት ላይ የሚመሰጠው ፣ በራሱ የማይተማመን ፣ እንከኑ የሚያሳቅቀው ነው ጉድለት የሚያስሰው። የማይለወጥ ነገርን መቀበል ከራስ ጋ ያዋሕዳል። ያየነውን ጥሩ ነገር በትክክለኛው ሰዓት ማንፀባረቅ በራስ መተማመን ይባላል። በራሳቸው የማይተማመኑ ሰው ማሳነስ ላይ ሲረማመዱ የሚውሉ ናቸው። ( ገጽ 130 )

➫ ማደጋችን የሚለካው የምንፈልገውን ሁሉ ባለማድረግ ነው። ( ገጽ 155 )

➫ ሕመማችን የሚባባሰው የበሽታችን ምክንያቶች እናክምህ ሲሉን አይደል ?” ወዳጃችን ሲያቆስለን ሕመማችን የሚበረታው እንደሚያስብልን ማስመሰሉ ስለማይቀር ነው። ( 155 )

➫ ባልተሳተፍንበት ነገር መስዋዕት የመሆን ያህል ከንቱነት የለም !! ( ገጽ 157 )

➫ ተገማች አለመሆን ዓላማን ለማሳካት ምቹ ነው። ( 162 )

➫ ከተበደለ የበለጠ ፣ መበደሉ የገባው በዳይ ኑሮው ሲኦል ነው !! ( 165 )
_



ሁሉ
ም አሪፎች ናቸዉ ይቺ ግን ከሁሉም ትለያለች

➫ ሕመማ
ችን የሚባባሰው የበሽታችን ምክንያቶች እናክምህ ሲሉን አይደል ?” ወዳጃችን ሲያቆስለን ሕመማችን የሚበረታው እንደሚያስብልን ማስመሰሉ ስለማይቀር ነው። ( 155 )

ለእናንተስ???
2.1K views03:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-12 06:23:09 ለአንዲት ሴት በተለይ “ቆንጆ ሴት” ነን ብለን ለምናስብ ሴቶች ፣ አቅማችንን እንዳንጠቀም እስር ቤት የሚሆንብን የራሳችን ቁንጅና ነው፡፡ የራሳችን ቆዳ የራሳችን እስር ቤት ነው፡፡
በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ  ‘ሴትነት እና ቁንጅና’ የሚባል እስር ቤት ፍርግርጋችንን እያስዋብን ተሟሙቀን የወንዶችን ጭብጨባና አድናቆት እየጠበቅን እንድንኖር ሆነናል፡፡ ሁሉም እስር ሰንሰለቱ ፈጦ አይታይም….. እንደውም አንዳንዱ እስራት ለታሳሪው ለራሱ ጭምር አይታይም፡፡ ማኅበረሰቡ አንዲትን ሴት “የብረት መዝጊያ የሚሆን አማች የምታመጣ እንጂ፣ የብረት መዝጊያ መሆን የምትችል አድርጎ አያስብም፡፡ ስለዚህ የእነሱን የምኞት በር የሚዘጋ የብረት መዝጊያ ለማምጣት፣ አንዲት ሴት ዓይኗንም አእምሯዋንም ሳይሆን እግሯን እንድትከፍት ከሕፃንነቷ  ጀምሮ ሲያዘጋጃት ይኖራል ”
”እግር የተፈጠረበት የመጀመሪያ ዓላማው መራመድ ነው፤ ለሴት ልጅ ግን ከመራመድ በላይ እግር ውበት እንደሆነ እንድታስብ በሥነጽሑፉ፣ በፊለሙ አእምሮዋ ውስጥ ሲታጨቅባት ኖሯል፡፡ ከመራመዷ በላይ የአረማመዷን እና የእግሯን ውበት እንድታስብ ስትሰበክ ኖራልች፡፡ ለዚያም ነው ከፊታቸው የተነጠፈውን እሾህም ይሁን ጠጠር ረግጠውና ዋጋ ከፍለው ወዳሰቡበት ከሚራመዱ ሴቶች ይልቅ፤ ከየትም ባገኙአት ሳንቲም በየውበት ሳሎኑ ተጎልተው፣ እግራቸውን የጥፍር ቀለም ሲያስቀቡና ተረከዛቸውን ሲያስፈገፍጉ የሚውሉ ዘመነኞች የሚበዙት፡፡ እግራቸውን ከለሰለሰ በኃላ፣ አዝሎ የሚያሻግር ወንድ ሲጠብቁ ቁጭ ብለው ይኖራሉ፡፡
እጅ የተፈጠረበት የመጀመሪያ ዓላማው መሥራት ነው፡፡ ብዙ የፋሽን እና ዘመናዊውን የውበት ሚዛን የሚደፉ ’ዘመናዊ’ ሴቶች፣ እጃቸው ከሚበላሽ ስማቸውም ሕይወታቸውም ቢበላሽ እና እጃቸው እንደለሰለሰ ቢኖር ይመርጣሉ፡፡ በልስላሴ ሳይሆን በንጽሕናና ራስን ችሎ በመቆም እንጨባበጥ ከተባለ ማን ናት ደፍራ እጇን የምትዘረጋ?! ለብዙኃኑ ወንዶች ጠንካራ የሴት እጅ ሀገርን ያቆመ ሳይሆን፣ ሴትነትን የገፋ መስሎ ነው የሚታያቸው፡፡ ለዚያ ነው በሥራ ስለደደረ የሴት መዳፍ፣ ዘፋኙም መዝፈን፣ ገጣሚውም መግጠመ የማይወደው፡፡ ድንጋይ ፈልፍሎ እና እምነበረድ ጠርቦ ውብ የእጅ ጣት ያላት ሴት ሐውልት የሚያቆመውን ቀራጺ እጅ ግን ተመልከተው፣ በሥራ የጎለደፈ ሆኖ ታገኘዋለህ፡፡ ከግማሽ በላይ የሚሆነው ሕዝብ ሴት በሆነበት አገር፣ ሴቶች እጃቸውን አስውበው መደርደሪያ ላይ እንዲያስቀምጡ በማድረግ፣ ለውጥ ጠብ አይልም፤ እንዲሰሩ….. ማደፋፈር….እጅ ወደተፈጠረበት የመጀመሪያ ዓላማ እንዲመለስ መሰበክ አለበት፡፡
                                                                                                                                                                                            
ከእለታት ግማሽ ቀን; ገጽ 182-183
2.8K viewsedited  03:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-10 14:53:39 ------------------

በፈረንጆቹ በ1950ዎቹና በ1960ዎቹ አካባቢ የሴት ፍላጎት፣ መብትና ነፃነት አይደለም ሊከበር ቀርቶ አልታሰበም ነበር፡፡ ሴት ልጅ ያገባች ከሆነ የባሏ አገልጋይ፤ ለትዳር ካልደረሰች ደግሞ የእናቷ ረዳት፤  ወግ ሳይደርሳትና ዕድል ሳይገጥማት ሳታገባ ከቆየች ወይም ፈት ከሆነች ደግሞ በማህበረሰቡ የስድብ ናዳ ይወርድባታል፣ ትናቃለች፣ ትገለላች፡፡ ሴት ሆኖ መፈጠር ምን ያህል ከባድ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ታሪክ ነው፡፡ በአሜሪካ እንኳን እ.ኤ.አ. በ1950 ዓ.ም. የነበረው ለሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የተዘጋጀውን የኑሮ በዘዴ መማሪያ መፅሐፍ (Home Economics text book) ብናይ ያገባች ሴት የባሏን ፍላጎት እንዴት ማሟላት እንዳለባት የሚያስተምርና የሚተነትን ነበር፡፡ ሴት ግዴታዋና ሃላፊነቷ የበዛ ነገር ግን መብትና ነጻነቷ ያነሰ፤ ምንም ምርጫ ያልነበራት እንደነበረች እናቶቻችንን ማየት በቂ ነው፡፡

ያም ሆነ ይህ በዘመናችን ያለችው ሴት በእናቶቻችን ዘመን ከነበሩት ሴት በብዙ መልኩ ትለያለች፡፡ ትናንት ፍላጎቷ የማይከበርላት፤ ዛሬ በአንድም በሌላም መንገድ ፍላጎቷ ይከበርላት ዘንድ አቅምና ጊዜ አግኝታለች፡፡ የዘመናችን አንገብጋቢውና አሳሳቢው ጉዳይ ግን ሴቶቹ ራሳችን የምንፈልገውን ነገር አለማወቃችን ነው፡፡ ራሳችንን አለማወቃችን የወንዶች ብያኔ ተጠቂ እንድንሆን አድርጎናል፡፡ ለጉብዝናችን ወይም ለቁንጅናችን የምስክር ወረቀት የምናገኘው ከወንዶቹ ነው፡፡ በዛም አለ በዚህ የወንዶች ስነልቦና ተጠቂ ሆነናል፡፡ በኢኮኖሚ ራሳችንን እየቻልን ብንመጣም በአስተሳሰብ ግን አሁንም የወንዶች ጥገኛ ነን፡፡ ራሳችንን በምግብ ብቻ ሳይሆን በሃሳብም ካልቻልን ከወንዶች ጭቆና አንተርፍም፡፡

መቼስ ሴትን እንደ እንደስነልቦና ምሁሩ ሲግመንድ ፍሮይድ ያጠናት የለም፡፡ ሰውየው ሴት ልጅ ገና ከልጅነቷ ጀምሮ ምን ዓይነት አስተሳሰብና ባህሪ ሊኖራት እንደሚችል፤ እንዲሁም ትክክለኛ ፍላጎቷ ምን እንደሆነ ለማወቅ የተመራመረ ነው፡፡ ለዚህ ነው ‹‹ሴት የምትፈልገው ምንድነው? What do women want›› በሚለው ጥያቄው የሚታወቀው፡፡

ሴት በሴት መቀናናት ያለ ነው፡፡ የማታስቀናም የማትቀናም ሴት የለችም፡፡ ሴት በወንድ ስትቀና ግን ሊያስገርም ይችላል፡፡ ፍሮይድ ይሄን በተመለከተ አንድ ጥናት ነበረዉ፡፡ ይሄ ጥናት ሴት ገና ከአፍላ እድሜዋ ጀምሮ አጎጠጎጤዎች ስታወጣ፣ የመራቢያ አካሏ እየዳበረ ሲመጣ፣ ለአቅመ ሔዋን ስትደርስና እንደ ወንድ አለመሆኗን ስታውቅ በወንዱ መቅናት ትጀምራለች ይለናል፡፡ መቅናት ከሴት ተፈጥሮ ጋር የተዋሃደ ይመስላል፡፡ ይሄ የስነልቦና ተመራማሪ ስለሴቶች ባህሪ ለማወቅ ብዙ ጥናቶችን ቢያከናውንም ሴቶች ግን እንቆቅልሽ እንደሆኑበት ነው ህይወቱ ያለፈው፡፡ የሚገርመው ሴት ልጅ አይደለም ለወንዱ ለገዛ ራሷ ግራ አጋቢ ፍጥረት መሆኗ ነው፡፡ ኤቭሊን ሌት (Evelyn Leite) የተባለች ታዋቂ የስነልቦና አማካሪ “Women” በተባለ መፅሐፏ ‹‹ፍሮይድ -- ሴት ምንድነው የምትፈልገው? -- የሚለው ጥያቄው ወንዱን ብቻ ሳይሆን ሴቷ ራሷ መልስ ያጣችለት ነው፡፡ (Freud’s question – What do women want – frustrates men, It also frustrates women)›› በማለት ትገልጻለች፡፡

ብዙዎቻችን ሴቶች ባላችን ወይም ምን እንዲያደርግልን ከመፈለጋችን በፊት እኛ የምንፈልገውን ቀድመን ማወቅ ይጠበቅብናል፡፡ ሚስቶች ከባሎቻችን የምንፈልገው ነገር ብዙ ነው፡፡ ነገር ግን የምንፈልገውን ነገር በግልጽ አናውቀውም፡፡ ባሎችም ሚስቶቻቸው ምን እንደሚፈልጉ አለማወቅ ብቻ ሳይሆን የሚስቶቻቸው ፍላጎት በየጊዜው የሚለዋወጥ በመሆኑ ግራ ተጋብተዋል፡፡ ሴት የራሷን አካላዊ፣ መንፈሳዊ፣ ስሜታዊ እና ሌላም ፍላጎቷን ለይታ ካላወቀች እንዴት ብሎ ነው ባሏ ፍላጎቷን ሊያሟላ የሚችለው? ብዙዎቻችን ሴቶች ለይተን ባላወቅነው ፍላጎታችን ወንዶችን ተጠያቂ እናደርጋለን፡፡

ግራ የሚያጋባ ነዉ.....
715 viewsedited  11:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-21 16:32:11
ታላቅ የምስራች ተጅዊድን መማር ለምትፈልጉ ተማሪዎች

#ዚክራ_ኦንላይን_የቁርአን_ማእከል_የሁለተኛ #ዙር_ምዝገባ_መጀመራችንን_ስናበስር_በደስታ_ነው
#የሁለት_ወር_ጥቅል_የተጅዊድ_ትምሀርት


    
            #የትምህርቱ_አሰጣጥ

1,በዙም አፕልኪሼን
2,በቴሌግራም አፕልኬሽን

    
        #የቆይታ_ጊዜ
በሳምንት 3 ቀን


#ትምህርቱን_ለመከታተል_የሚያስፈልጉ
ዋይፋይ(ፈጣን ኔትወርክ)
ስማርት ስልክ


        #ያሉን_ቦታዎች

##በጀመአ (በግሩፕ)
##vip (በ ግል)

ከተሟላ በሰርተፍኬት ጋር

በግል ለመመዝገብ

@redwan6910

ዋትስ አፕ https://chat.whatsapp.com/I6YyupqN1TW8Nzf6DgVZXz

ወደ ተጅዊድ ትምህርት መስጫ ግሩፕ
https://t.me/+V3lxqKjWQHxiYzFk

ወደ public group

https://t.me/+-zHkXQeSZdc4MjY0

#zikra_Qur'anic_academy
2.8K views13:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-20 06:33:27
አግኝቶ ማጣት
2.4K viewsedited  03:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ