Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Press Agency/አማርኛ /

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethpress — Ethiopian Press Agency/አማርኛ / E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethpress — Ethiopian Press Agency/አማርኛ /
የሰርጥ አድራሻ: @ethpress
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 23.41K
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 140

2022-09-03 11:11:00
490 views08:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-03 11:09:21
#የማይረሱትየትህነግግፎች 8
የትህነግ ግፍ ያረፈባቸው ቤተ እምነቶች
አሸባሪው ትህነግ የተሰጠውን የሰላም እድል ወደጎን ትቶ ሶስተኛ ዙር ጦርነት
ከፍቷል። መንግስት ያደረገውን የሰላም ጥረት ሁሉ መና ያስቀረው ትህነግ፤ አሁን
በከፈተው ወረራ “ከአማራ እና ከአፋር ክልል ህዝብ ጋር ጸብ የለኝም” የሚል
የማዘናጊያ ፕሮፖጋንዳ እየረጨ ይገኛል። መሬት ላይ ያለው እውነታው ግን ይህ አይደለም።
ትህነግ በሁለተኛው ዙር ወረራው በሁለቱ ክልል ህዝቦች ላይ ያደረሰው ግድያ፣ ዝርፊያና አስገድዶ መድፈር ከፍተኛ እንደሆነ ዓለም አቀፍ ተቋማት ሳይቀሩ ባወጧቸው ሪፖርቶች አረጋግጠዋል። በአፋር እና አማራ ክልል የሚገኙ ቤተ እምነቶችንም በዚህ መልክ አራክሷል፤ አውድሟል።
#የማይረሱትየትህነግግፎች -8
619 views08:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 19:52:32
አሸባሪው ህወሓት ሶስተኛውን ዙር ጦርነቱን ከመጀመሩ በፊት የቡድኑ መሪ ደብረጺዮን ህዝብ ሰብስቦ በቅርቡ ባደረገው ዲስኩር

"ዐብይ እህል ይሰጠናል ወይም ቴሌኮም ይሰጠናል፣ ብር ይሰጠናል ብለን ልናስብ አንችልም። ተገዶ፡ ባፍንጫው ተይዞ አፍንጫውን ይዘን፣ በክንዳችን መሰረተዊ አገልግሎት እንዲያቀርብ እናደርጋለን።" ሲል ተደምጦ ነበር።
2.6K views16:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 16:17:40
#የማይረሱትየትህነግግፎች 7
በአሸባሪው የተደፈሩት የ85 አመቷ መነኩሴ
"አሁንማ ምንኩስናዬም ፈረሰ፤ አረከሰኝ”
በትህነግ ታጣቂ የተደፈሩት የ85 አመቷ የሸዋሮቢቷ መነኩሴ ለኢፕድ የተናገሩት።
በአማራ ክልል ሸዋሮቢት ከተማ የቀበሌ 02 ነዋሪ የሆኑት እማሆይ በላይነሽ (ስማቸው የተቀየረ) 10 ልጆችን ወልደው የሳሙ የ85 ዓመት የእድሜ ባለፀጋ መነኩሲት ናቸው።
በወቅቱ ላነጋገሯቸው የኢፕድ ዘጋቢዎች እንደተናገሩት፤ የአሸባሪው ህወሓት ታጣቂዎች ከተማዋን ተቆጣጥረው በነበረበት ወቅት የእለት ጸሎታቸውን አድርሰው ሰላም አሳድረኝ ብለው በተኙበት እኩለ ሌሊት በእነዚህ ታጣቂዎች ተደፍረዋል።
“...ያ ሰው መሳይ አውሬ አርክሶኝ ሄደ፤ በማግስቱ ሙሉ ቀን ከማህጸኔ ደም ሲፈሰኝ ዋለ። አካላቴ ሁሉ ደቋል፤ የሰውነቴ ህመም አሁንም ድረስ አለ" ያሉት እማሆይ በላይነሽ፤ ወገባቸውን እንደሚያማቸው፣ ሽንታቸውን ሲሸኑ ፊኛቸውና ማህጸናቸው አካባቢ ህመም እንደሚሰማቸው ገልጸውልናል።
ቆመው ለመራመድ መቸገራቸውንና በሰው ድጋፍ እንደሚንቀሳቀሱም ዘጋቢዎቻችን በወቅቱ ተመልክተዋል።
ዛሬም ይህ የሽብር ቡድን ከመንግሥት የተሰጠውን የሠላም ውይይት ወደ ጎን ትቶ ለ3ኛ ጊዜ አገር የማፍረስ ዕቅድ መፈጸሚያውን ጦርነት ከፍቷል። ለዳግም ዝርፊያ፣ ግድያ ብሎም አገር የማፈረስ ውጥኑን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶችን ጋር ተባብሮ ጦርነት የከፈተው ትህነግ፤ "የአማራ እና አፋር ህዝብ ከጎኔ ቁሙ፤ ከእናንተ ጋር ጸብ የለኝም" ሲል የአይናችሁን ጨፍኑ ላሞኛችሁ ጥሪ አቅርቧል።
#የማይረሱትየትህነግግፎች -7
2.9K views13:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 14:11:10
"በባህላዊ የወርቅ ማዕድን ምርት ላይ የሚደርጉ ህገወጥ እንቅስቃሴዎችን ሥርዓት የማስያዝ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል" - የማዕድን ሚኒስትር ኢንጂነር ታከለ ኡማ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
በባህላዊ የወርቅ ማዕድን ምርት ላይ የተሰማሩትን የአከባቢ ወጣቶችም ይሁን ከውጭ ዜጎች ጋር በመመሳጠር የሚደርጉ ህገወጥ እንቅስቃሴዎችን ሥርዓት የማስያዝ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ የማዕድን ሚኒስትር ኢንጂነር ታከለ ኡማ ገለፁ።
ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው እንዳስታወቁት በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ( አሶሳ )፣ በኦሮሚያ ( ሻኪሶ) ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ( ቤሮ), እና በጋምቤላ ( ዲማ) ወረዳ በህጋዊ መንገድ እየሰሩ ያሉትን ኩባንያዎች እና ባህላዊ የወርቅ አምራቾች ይበረታታሉ ።
ህገወጦችን በህግ ቁጥጥር ስር እያዋልን እንገኛለን ነው ያሉት ሚኒስትሩ በምንም መስፈርት ህገወጦችን አንታገስም፤ እርምጃ መውሰዳችን ይቀጥላል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን የትዊተር ገጽ ይከተሉ
https://twitter.com/PressEthio
213 views11:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 14:09:53
አሸባሪው ህወሓት በወልቃይት ግንባር በከፈተው ማጥቃት ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ እንደደረሰበት የሽብር ቡድኑ ምርኮኞች ተናገሩ
****************
(ኢ ፕ ድ)
ኢትዮጵያን ለማፈራረስ በሙሉ አቅሙ ቆርጦ የተነሳው የሽብርተኛው ህወሓት ሀይል በወልቃይት ግንባር በከፈተው ማጥቃት ከፍተኛ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ እንደደረሰበት የሽብር ቡድኑ ምርኮኞች ተናገሩ።
አሸባሪው ህወሓት ያለንን አቅም ሁሉ ተጠቅመን ወልቃይትና ራያን አስመልሰን ታላቋ ትግራይን እንመሰርታለን ብሎ ጦርነት ቢያስገባንም ሳናሳካ ሙት ፣ ቁስለኛና ምርኮኛ ለመሆን መገደዳቸውን ምርኮኞቹ ተናግረዋል።
የሽብር ኃይሉ የትግራይ ወጣቶችና ታዳጊዎችን በየግንባሩ ለጦርነት በመማገድ ላይ እንደሚገኝም ምርኮኞቹ መናገራቸውን የሀገር መከላከያ ሠራዊት በማህበራዊ ትስስር ገጹ ዘግቧል።
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን የትዊተር ገጽ ይከተሉ
https://twitter.com/PressEthio
243 views11:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 13:11:42
#የማይረሱትየትህነግግፎች 6
ሁለቱ የአፋር ወንድማማቾች
አሸባሪው ትህነግ አፋር ክልል በፈጸመው ወረራ በህጻናትና ሴቶች ላይ ያደረሰው ግድያና አስገድዶ መድፈር መቼም የሚዘነጋ አይደለም። ይህ አሸባሪ ቡድን በሁለተኛ ዙር ወረራው በአፋር ክልል የፈጸመውን ወንጀል ለመመልከት በሥፍራው ያቀኑት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ዘጋቢዎች ዱብቲ ጠቅላላ ሆስፒታል ተገኝተው ነበር። በወቅቱ በሽብር ቡድኑ ታጣቂዎች በተፈጸመ ጥቃት ጉዳት የደረሰባቸውን ሁለት ወንድማማቾችን አግኝተው አነጋግረውም ነብረ።
ህጻናቱ ጣሂር ደርሳ እና ኑር ደርሳ ይባላሉ፡፡ የ 8 እና የ10 አመት ልጆች ሲሆኑ፤ የአብአላ ወረዳ ነዋሪዎች ናቸው፡፡ ይህ የሽብር ቡድን የህጻናቱን መንደር በከባድ መሳሪያ ሲደበድብ የሁለቱ ወንድማማቾች መኖሪያ ቤትም ከጥቃቱ አላመለጠም። በዚህም በርካቶች ሲሞቱ እነዚህ ምንም የማያወቁ ሁለት ህጻናት በዚህ መልኩ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
ይህ አሸባሪ ቡድን ዛሬ ሶስተኛውን ዙር ወረራ አፋር ላይ ፈጽሞ ሲያበቃ "ከህዝቡ ጋር ትናንትም ዛሬም ችግር የለብንም” ሲል ተደምጧል። ያለጦርነት መኖር የማይችለው ትህነገ ግን አሁንም በተመሳሳይ በአፋር ህዝብ ላይ ተመሳሳይ ወንገሎችን እየፈጸመ ይገኛል።
#የማይረሱትየትህነግግፎች -6
819 views10:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 11:21:34
በዓለም ባንክ የሚደገፉ የመሠረተ ልማት ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረገ የምከክር መድረክ ተካሄደ
******************
(ኢ ፕ ድ)
የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ የዓለም ባንክ ልዑካንን በጽ/ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።
ውይይቱ በዓለም ባንክ የሚደገፉ የከተማና መሠረተ ልማት ሥራዎች ያሉበትን ወቅታዊ ሁኔታ በመገምገም ቀጣይ አቅጣጫዎችን ማስቀመጥን ዓላማው ያደረገ ነው፡፡
በዓለም ባንክ ከሚደገፉ ፕሮጀክቶች መካከል በጥሩ የአፈጻጸም ደረጃ ላይ የሚገኙ ፕሮጀክቶች የመኖራቸውን ያህል በጸጥታና በሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የሚታዩ መጓተቶች ሊታረሙ እንደሚገባቸውም ተጠቁሟል።
ለዚህ ተፈጻሚነት የሚመለከታቸው አካላት የየድርሻቸውን ኃላፊነት መወጣት እንደሚጠበቅባቸው ተገልጸዋል።
በውይይት መድረኩ ላይ ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደርና ከዋናው መ/ቤት በዓለም ባንክ የሚደገፉ ፕሮጀክቶችን የሚመሩ አመራሮችና የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈውበታል፡፡
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን የትዊተር ገጽ ይከተሉ
https://twitter.com/PressEthio
1.3K views08:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 11:19:34
የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከሬዳዋ ሞተር ኢንዱስትሪ ጋር ስምምነት ተፈራረመ
******************
(ኢ ፕ ድ)
ሬዳዋ ሞተር ኢንዱስትሪ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር ስምምነት ተፈራረመ።
ስምምነቱ ሬዳዋ ሞተር ኢንዱስትሪ ወደ ኢንዱስትሪ ፓርክ አልሚነት መሸጋገሩን አስመልክቶ የተደረገ መሆኑን ተገልጿል።
ሬዳዋ ሞተር ኢንዱስትሪ በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ ሲገባ ወደ 17 ቢሊዮን ብር ኢንቨስትመንት ያካሂዳል።
በፊርማ ስነስርዓቱ ላይ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ታረቀኝ ቡልልታ እንደገለጹት፣ ሬዳዋ ወደ ኢንዱስትሪ ፓርክ አልሚነት የተሸጋገረ የመጀመሪያው የግል ኢንዱስትሪ በመሆኑ ትልቅ ፋይዳ አለው።
ከውጭ አገር ጥገኝነት ለመላቀቅ ያግዛል፤ በአሁኑ ጊዜ አብዛኛው ነገር ከውጭ የሚገባ በመሆኑ ሉአላዊነትን አሳልፎ መስጠት በመሆኑ የሀገር ውስጥ ምርትን ማሳደግ ያስፈልጋል ብለዋል።
እንደ አገር ምርትን ማሳደግ ካልተቻል ኩሩ ህዝቦች መሆን አንችልም። ሬድዋ ሞተርስ ኢንዱስትሪ የውጭ ምርትን በአገር ውስጥ ምርት ለመተካት ትልቅ ጥቅም ነው።
ኢንዱስትሪዎችን ለማሳደግና የስራ እድል ለመፍጠር የፋይናንስ ተቋማት ድጋፍ ማድረግ አለባቸው ብለዋል።
የድሬዳዋ ከተማ ከንቲባ አቶ ከድር ጀዋር በበኩላቸው ኢንዱስትሪው ለአገር ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው፣ ከሌሎች ኢንዱስትሪዎች ልዩ የሚያደርገው የራሱ የሄሊኮፕተር ማረፊያና መገጣጠሚያ ያለው መሆኑን ገልጸዋል።
በኢንዱስትሪው ፓርክ ውስጥ የመኪና መገጣጠሚያ፣ የኬብል፣ የታሸገ ውሃና የተለያዩ ምርቶችን የሚያመርትበት ፋብሪካዎች አሉት። በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ ሲገባ ወደ 17 ቢሊዮን ብር ኢንቨስትመንት ያካሂዳል ብለዋል።
በሞገስ ፀጋዬ
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅትን የትዊተር ገጽ ይከተሉ
https://twitter.com/PressEthio
1.1K views08:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-02 10:39:41
አሸባሪው ሕወሓት ዛሬም ለሰላማዊ ዜጎች ሞት፣ መፈናቀልና ስደት ምክንያት ሆኗል
*************
(ኢ ፕ ድ)
አሸባሪው ሕወሓት ከውጪ ታሪካዊ ጠላቶች ጋር በማበር እና በመንግስት በኩል የተደረገውን የተናጠል ተኩስ አቁም ስምምነት ወደ ጎን በመጣል እንዲሁም ለሰላም የተደረጉ ጥረቶችን ባለመቀበል ኢትዮጵያን ለመበታተን ለሦስተኛ ጊዜ በከፈተው ጦርነት አሁንም ለሰላማዊ ዜጎች ሞት፣ መፈናቀልና ስደት ምክንያት መሆኑን የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን አስታወቀ።
የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጂማ ዲልቦ በትናንትናው ዕለት በተደረገው የተቋሙ ዓመታዊ ስብሰባ ላይ እንደተናገሩት፤ የኢትዮጵያን ሰላም የማይፈልገው አሸባሪው ሕወሓት መንግስት ሳይወድ በግድ ሌላ ጦርነት እንዲገባ አድርጎታል። መንግስት አሁንም ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት ቡድኑ የወረረውን አካባቢ በመልቀቅ ወደ ሰላም እንዲመለስ እያደረገ ይገኛል። ችግሮችን በውይይት ብቻ እንዲፈቱ አሁንም ተስፋ ባለመቁረጥ ጥረቱ ቀጥሏል።
የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችም ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የቡድኑን አካሄድ እንዲገንዘብ፣ እንዲያወግዝና ሰላም ብቸኛው አማራጭ ሆኖ እንዲቀርብ ተገቢውን የማሳወቅ ስራ መፈጸም እንዳለባቸው አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያውያን አገራዊ አንድነታችንን በማጠናከር ፊታችንን ወደ ልማት ልናዞር ይገባናል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፣ በጦርነት ውስጥ ሆኖ ዘላቂ ልማት.....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=80515
1.1K views07:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ