Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Press Agency/አማርኛ /

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethpress — Ethiopian Press Agency/አማርኛ / E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethpress — Ethiopian Press Agency/አማርኛ /
የሰርጥ አድራሻ: @ethpress
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.66K
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 143

2022-08-30 15:48:27
1.4K views12:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 15:47:21 ከ81 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የጉምሩክ ኮሚሽን ነሐሴ 13 እስከ 19 ቀን 2014 ዓ.ም ባደረገው ክትትል 74 ነጥብ 9 ሚሊዮን የገቢ ኮንትሮባንድ እቃዎች እና 6 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ የወጭ በአጠቃላይ 81 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ ኮንትሮባንድ እቃዎችን በተለያዩ ቅርንጫፍ ጽህፈት በቁጥጥር ስር አውሏል፡፡
የገቢ ኮንትሮባንድን በመቆጣጠር ረገድ ቀዳሚውን ስፍራ የሚይዙት ሀዋሳ፣ ድሬድዋ እና አዳማ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች ሲሆኑ በቅደም ተከተላቸው 23 ነጥብ 9 ሚሊዮን፣ 12 ነጥብ 2 ሚሊዮን እና 6 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የኮንትሮባንድ እቃዎችን መያዝ ችለዋል፡፡
በቁጥጥር ስር ከዋሉት የኮንትሮባንድ እቃዎች መካከል አልባሳት፣ ነዳጅ፣ የቁም እንስሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ቡና፣ መድሀኒት፣ ተሽከርካሪዎች፣ የመዋቢያ እቃዎች የጦር መሳሪያዎች፣ ጫት፣ አደንዛዥ እጾች፣ የምግብ ዘይት እና የተለያዩ ሀገር ገንዘቦች ይገኙበታል፡፡
የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ በጉምሩክ ኮሚሽን ሰራተኞች ፣ በፌደራል ፖሊስ፣ በክልል ፖሊስ አባላትና ህብረተሰቡ ባደረጉት የጋራ ጥረት በፍተሻ፣ በበረራና በጥቆማ የተያዙ ሲሆን የኮንትሮባንድ እቃዎቹን ሲያዘዋውሩ የተገኙ ሁለት ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡
የጉምሩክ ኮሚሽን በዚህ የህግ ማስከበር ስራ ላይ ለተሳተፉ የኮሚሽኑ ሰራተኞች ፣ የክልልና የፌደራል ፖሊስ አባላት እንዲሁም ለመላው ህዝብ ምስጋናውን አቅርቧል።
የኮንትሮባንድ እና ህገወጥ ንግድ የአፈጻጸም ስልቱ ተለዋዋጭ በመሆኑ ድርጊቱን ለመግታትና በሀገር ኢኮኖሚ የሚያሳድረውን አሉታዊ ተጽእኖ ለመከላከል ጉምሩክ ኮሚሽን ብቻ የሚያደርገው እንቅስቃሴ በቂ ባለመሆኑ ሁሉም ባላድርሻ አካላትና ህብረተሰቡ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ የጉምሩክ ኮሚሽን ጥሪውን አቅርቧል።
1.5K views12:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 15:47:18
1.5K views12:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 13:44:50
የሶማሌ ክልል ፕሬዝደንት የደቡብ ኮሪያና የአለም ምግብ ድርጅት ከፍተኛ ልዑካን ተቀብለው አነጋግረዋል
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የሶማሌ ክልል ፕሬዝደንት አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ ከደቡብ ኮሪያ ፓርላማ አባላትና ከአለም ምግብ ድርጅት የተወጣጡ ከፍተኛ የአመራር ልዑካን ቡድንን ዛሬ በጽ/ቤታቸው ተቀብለው በክልሉ ስላለው ሰብዓዊ ድጋፍ ዙሪያ ላይ መክረዋል።
ከዚህ በተጨማሪም አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ በደቡብ ኮሪያ ፓርላማ አባል ጃጁንግ ሊ የተመራውን የዓለም ምግብ ድርጅት እና የኮሪያ መንግስት ባለስልጣናትን በክልሉ ስለላው አጠቃላይ ሁኔታ በተለይም ስለተፈናቀሉ የክልሉ ማህበረሰብ ለሚደረገውን ድጋፍ ሁኔታ ማብራሪያ ሰጥቷቸዋል።
የደቡብ ኮሪያ ፓርላማ አባላትና የዓለም ምግብ ድርጅት ባለስልጣናቱ በበኩላቸው የክልሉ መንግስት ለተፈናቃዮች የሚያደርገው የአስቸኳይ ምግብ ድጋፍ ጥረት አበረታች መሆኑን ገልፀው ከወዲሁ ለዜጎች የሚደረግለት ድጋፍ የበኩላቸው ሚና እንደሚጫወቱና ከሶማሌ ክልል መንግስት ጋር በዘላቂ ልማት ስራዎች ላይ እንደሚሰሩ ማናገራቸውን የክልሉ የመንግስት ኮምንኬሽን ቢሮ አስታውቋል።
1.8K views10:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 12:18:51
1.6K views09:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 10:59:31 "ተመራቂዎች ያገኙትን እውቀት ወደ ስራ በመለወጥ የገጠመንን ችግር በአንድነት መመከት ይገባል"
- ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
ተመራቂዎች ያገኙትን እውቀት ወደ ስራ በመለወጥ የገጠመንን ችግር በአንድነት መመከት እንዳለባቸው የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ አሳስቡ።
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በተለያዩ የትምህርት መስክ ያሰለጠናቸውን 5 ሺህ 58 ተማሪዎችን አስመርቋል።
ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች የምረቃ ሥነ- ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር መማር ማለት የባህሪ ለውጥ ማምጣት ነው፤ ተመራቂዎች በዘር፣ በሀይማኖት ከመከፋፈል ወጥተው ለአገር የሚጠቅም ስራ እንዲሰሩና የገጠመንን ችግር በአንድነት መመከት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ኢትዮጵያን ባላችሁበት ሆናችሁ ልክ እንደ ቀደሞ አባቶችና እናቶቻችሁ ውደዷት፣ ያገናችሁትን እውቀት ወደ ስራ በመለወጥ ሀገሪቱ የገጠማትን ችግር እንድታቃልሉና በሙያችሁ ህዝባችሁን በፍፁም እኩልነት እንድታገለግሉ አደራ እላለሁ ብለዋል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ላለፉት 72 አመታት በማስተማርና ምርምር በማድረግ ኢትዮጵያ ሲያገለግል ቆይቷል። በግብርናው፣ ኢንዱስትሪዎችና ሌሎች ዘርፎች የሚፈልጉትን የተማረ የሰው ሃይል በጥራት ሲያቀር ቆይቷል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በርካታ ችግር እያስተናገደች ነው ያሉት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ፣ አገር ለማሳደግ መረባረ ሲገባ የበርካታ ንጹሃን ደም እየፈሰሰ ነው። ህዝባችን የሚፈልገው በሰላም ሰርቶ በሰላም መግባት ነው፣ መሰረት ልማቶች እንዲሟሉለት ነው።
አገራቱ ከጦርነት፣ ከስጋት፣ ከመፈናቀል ወጥታ ወደ ተሻለ ደረጃ እድትደርስ መንግስት የተለያዩ እቅዶችን ቀርጾ እየሰራ መሆኑን ጠቅሰውየተማረ ሰው ችግር ውስጥ ያለን ህዝብ ከችግር ማውጣት እንዳለበት አሳስበዋል።
አዲስ አበባ ዪኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ጣሰው ወልደሀና፣ ዩኒቨርስቲ በአሁኑ ወቅት 11 የምርምር ተቋማትና ሁለት የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አሉት። ከ40 ሺህ በላይ ተማሪዎችን እያሰተማረ ነው። 40 በመቶ የድህረ ምረቃ ተማሪዎች ሲሆኑ 33 በመቶው ደግሞ ሴቶች ናቸው ብለዋል።
ኢትዮጵያ ከውስጥና ከውጭ ጠላት በበዛባት ወቅት እናንተን ተንከባክባ ለዛሬው ቀን አብቀታኋለች፣ በዘርና በጎሳ ከመከፋፈል ወጥታችሁ ሀገሪቱን በጥናትና ምርምር መርዳት አለባችሁ ብለዋል።
በሞገስ ፀጋዬ
1.4K views07:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 10:59:20
1.1K views07:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 10:08:19
1.3K views07:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-16 10:06:46
"ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚከሰቱ ጥፋቶች ጀርባ ህወሓት ይጠፋል ብለን አናምንም"
– አቶ ሙሉብርሃን ኃይሌ የትግራይ ዲሞክራሲ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ
********************
(ኢ ፕ ድ)
ሁሌም ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚከሰቱ ጥፋቶች ጀርባ ህወሓት ይጠፋል ብለን አናምንም ሲሉ የትግራይ ዲሞክራሲ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ተናገሩ። ትግራይን መልሶ ለመገንባት የተያዘውን በጀት ህወሓት ለራሱ እኩይ አላማ እንዳያውለው ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባም አሳስበዋል።
የትግራይ ዲሞክራሲ ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሙሉብርሃን ኃይሌ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ አሸባሪው ህወሓት በለውጥ ተቃራኒ መጓዝ ከጀመረ ጊዜ ጀምሮ በኢትዮጵያ በርካታ ግጭቶችን ፈጥሯል፤ አገርን የማፍረስ ሙከራዎችንም አድርጓል።
ህወሓት በአገር ውስጥና ከአገር ውጭ ሆነው ሀሳቡን ከሚደግፉ ኃይሎች ጋር በመተባበርና በማስተባበር ግጭቶችን ሲመራና ሲያስተባብር ነበር ያሉት አቶ ሙሉብርሃን፤ ሁሌም ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚከሰቱ ጥፋቶች ጀርባ ህወሓት ይጠፋል ብለን አናምንም ብለዋል።
ወደ ኋላ መለስ ብለን ስናይ ህወሓት ከሸኔ ጋር በይፋ ለመስራት መግለጫ ሲያወጡ ነበር ያሉት ኃላፊው፤ ሰሞኑን ባሉ ግጭቶችም ህወሓት ከበስተጀርባ እንዳለበት መገመት ይቻላል ብለዋል።
እንደ አቶ ሙሉብርሃን ገለጻ፤ ቡድኑ ወደ መቀሌ ከገባ በኋላ በርካታ የሽብር ሥራዎችን....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=77169
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
1.5K views07:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-15 16:42:42 የአዲስ አበባ ፖሊስ እና የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ከ9 ሺህ በላይ ጥይት ከእነ ተጠርጣሪዎቹ መያዛቸውን አስታወቁ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
የአዲስ አበባ ፖሊስና የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት በጋራ በመቀናጀት ባደረጉት ክትትል ከ9 ሺህ በላይ የሽጉጥ ጥይት ከእነ ተጠርጣሪዎቹ መያዛቸውን አስታወቁ፡፡
የጦር መሳሪያ ዝውውሩን ለመቆጣጠር እየተሰራ ያለው ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል፡፡
መነሻውን ባህርዳር ከተማ ያደረገ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3-98555 አ/አ ኤፍ.ኤስ .አር ተሽከርካሪ ላይ ከጫት ጋር በማድረግ በማዳበሪያ ተጭኖ ወደ አዲስ አበባ የገባ ብዛቱ 9ሺ 950 የሽጉጥ ጥይት በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዩ ቦታው አጂፕ ቶታል አካባቢ ሐምሌ 7 ቀን 2014 ዓ/ም ከጠዋቱ 2 ሰዓት ላይ ከብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ጋር በመተባበር ከእነ ተጠርጣሪዎቹ እጅ ከፍንጅ እንደተያዘ የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
ጥይቱን ሲያዘዋውሩ የተገኙ አራት ተጠርጣሪዎች እና ለህገ-ወጥ ተግባር የተገለገሉበት አንድ ተሽከርካሪ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራው መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ገልጿል፡፡
ፀረ-ሰላም ኃይሎች አዲስ አበባን የጦር መሳሪያና ጥይት መዳረሻ አድርገው እየሰሩ ቢሆንም የፀጥታ አካላት በሚያደርጉት ብርቱ ክትትል እና በህብረተሰቡ ጥቆማ የጦር መሳሪያ አዘዋዋሪዎች እጅ ከፍንጅ እየተያዙ እንደሆነና የጦር መሳሪያ ዝውውርን ለመቆጣጠር እየተሰራ ያለው ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
የከተማዋን ሰላምና ደህንነት ለማወክ የሚንቀሳቀሱ ግለሰቦችን ህገ-ወጥ ተግባር በማጋለጥ ህብረተሰቡ ለፀጥታ አካለት እያደረገ ያለውን ትብብር አጠናክሮ እንዲቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪውን አስተላልፏል፡፡
ኢትዮጵያን እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
2.8K views13:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ