Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Press Agency/አማርኛ /

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethpress — Ethiopian Press Agency/አማርኛ / E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethpress — Ethiopian Press Agency/አማርኛ /
የሰርጥ አድራሻ: @ethpress
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.66K
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-06-11 17:24:21
ከ597 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለው የሶማሌ ክልል ምክር ቤት ግንባታ 85 በመቶ ተከናውኗል
************************
(ኢ ፕ ድ)

ከ597 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ እየተገነባ ያለው የሶማሌ ክልል ምክር ቤት ግንባታ 85 በመቶ መከናወኑን የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ጣሂር አብዲ ተናግረዋል።

ግንባታው በቀጣይ 2016 በጀት ዓመት ይጠናቀቃልም ብለዋል።

በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባዔ አቶ ታገሰ ጫፎ የተመራው በድን የክልሉን ምክር ቤት የሕንጻ ግንባታ ምን ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ተዘዋውሮ ጎብኝቷል። በጅግጅጋ ከተማ ችግኝ በመትከል አሻራቸውን አስቀምጠዋል።

የፕሮጀክቱ ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ጣሂር አብዲ፣ የሕንጻ ግንባታ የተያዘለት በጀት ከ597 ሚሊየን ብር በላይ እንደሆነና የግንባታው አፈጻጸም አሁን ላይ 85 በመቶ ላይ እንደሚገኝ ገልጸው ግንባታው በበጀት ምክንያት የዘገየ ቢሆንም በቀጣይ 2016 በጀት ዓመት የሚጠናቀቅ እንደሆነ አስረድተዋል።

የምክር ቤቱ ሕንጻ ግንባታ በ2011 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን በ26 ሺህ ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ መሆኑን ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ሀገር አቀፍ የህግ አውጪዎች የውይይት መድረክ በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ በተለያዩ ርዕሰ-ጉዳዮች ዙሪያ ሲመክር መቆየቱ ይታወሳል።
1.4K views14:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 17:13:23 ለድሬዳዋ ፖሊስ የጦር መሣሪያን ለመቆጣጠርና ለማስተዳደር የሚያስችል ሲስተም ሶፍትዌር ተረከበ
*****
(ኢ ፕ ድ)

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የጦር መሣሪያን ለመቆጣጠርና ለማስተዳደር የሚያችል ሲስተም ሶፍትዌር በማበልፀግ ለድሬዳዋ ፖሊስ አስረክበዋል።

በፕሮግራሙ ላይ የኢትዩጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል የፖሊስ ሥራ የሚሳለጠው በቴክኖሎጂ የተደገፈ ስራ ሲሰራ መሆኑን ጠቁመው ለድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ መምህራን ምስጋና አቅርበዋል።

የፖሊስን ተቋም በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማስታጠቅ የፖሊስን ስራ ቀላል ከማድረጉም በላይ ትክክለኛ የሆነ መረጃ ለማግኘት ወሳኝ በመሆኑ በቀጣይ ፖሊስን የሚያዘምኑ ስራዎች ለመስራት በስትራቴጂክ እቅዱ ላይ በግልጽ የተቀመጡ ግቦችን ወደ ታች በማውረድ ስራዎች በትጋት ይሠራሉ ብለዋል፡፡

በቀጣይ ቴክኖሎጂዎቹን በማስፋት በሁሉም የፖሊስ ተቋማት ተደራሽ የሚሆኑበትን ሁኔታ ማመቻቸት እንዲቻል የኢትዮጵያ ፖሊስ ዩኒቨርሲቲና የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በጋራ መስራት እንደሚገባቸው ኮሚሽነር ጀነራል ገልጸዋል፡፡

ምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የፖሊስ ተቋማት የተስማሙበት ቴክኖሎጂዎችን ወደ ሀገር ውስጥ በማስገባት የፖሊስ ተልዕኮዎችን ቀላልና ቀልጣፋ ማድረግ የሚያስችለውን ሲስተም በማበልጸግ መጠቀም ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል።

ዘመናዊ የወንጀል ምርመራውን ለማዘመን የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የተጠርጣሪውን ሰብአዊ መብት በጠበቀ አኳሃን ስራዎችን መሰራት መጀመራቸውንና የድሬዳዋ ፖሊስ ወደ ድሬዳዋ ከተማ የሚገባ ማንኛውም ሰው መረጃ ቀድሞ እንዲደርሰው የሚያስችልና የሰውን ህይወትና ንብረት እያወደመ ያለውን የትራፊክ አደጋ በቀላሉ መረጃን ለመሰብሰብ የሚያግዙ ሲስተም ሶፍትዌሮችን መዘርጋቱን የሚበረታታ ተግባር ነው ብለዋል።

ሌሎች ከተሞችም የከተማዋን ተሞክሮ በመቅሰም የዜጎችን ሰላምና ደህንነት መጠበቅ እንደሚገባቸው ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲዎች ለሀገሪቱ የሚጠቅሙ ጥናትና ምርምሮችን እያደረጉ የፀጥታ መዋቅሩን ሥራን እንዲያጠናክሩ ኮሚሽነር ጀነራሉ ጥሪ አቅርበዋል።

የድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አዛዥ ኮሚሽነር አለሙ መግራ በበኩላቸው የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ለድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ስራዎችን ሊያቀሉ የሚችሉ ሶፍትዌሮችን አበልጽጎ መስጠት በመቻሉ ምስጋና አቅርበዋል።

የድሬዳዋ ፖሊስ በከተማው ያለውን የጦር መሣሪያ መቆጣጠርና ማስተዳደር እንዲችል መደረጉ፣ እየተበራከተ የመጣውን የትራፊክ አደጋን ለመቀነስ የሚያስችል ሲስተም ሶፍትዌር መጠቀም መጀመራቸው የወንጀል መከላከል ሥራውን ቀላል ከማድረጉም ባሻገር ህገወጦችን በቀላሉ በቁጥጥር ሥር አውሎ ለህግ ለማቅረብ ድርሻው ከፍተኛ እንደሆነ ጨምረው ተናግረዋል።

በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከፍተኛ አመራሮች፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የድሬዳዋ እና የፌደራል ፖሊስ አመራር እና አባላት፤ የድሬዳዋ ማህበረሰብ አቀፍ የፖሊስ አገልግሎት የየቀጠናው አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
1.3K views14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-11 17:13:21
1.1K views14:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 20:07:25
1.1K views17:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 20:07:22 የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በሚቀጥለው ዓመት በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች ይካሄዳል-ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ
******
(ኢ ፕ ድ)

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር በሚቀጥለው ዓመት በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች የሚካሄድ መሆኑን የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ገለጹ።

የዝግጅት ምዕራፍ አካል የሆኑትን የተሳታፊ መረጣና የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራ የ2015 በጀት ዓመት ከመጠናቀቁ በፊት ለመጨረስ እየተሰራ መሆኑንም ኮሚሽነሩ ተናግረዋል።

ኮሚሽኑ የተሳታፊዎች ልየታን በሚያካሂድበት ወቅት ግልፅነት፣ አካታችነት፣ ፍትሐዊ ውክልና፣ አዳዲስ ከዋኞችና ተባባሪዎች እንዲሁም በቂ ጊዜ ታሳቢ እንደሚደረጉ ገልጿል።

የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፣ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር፣ የኢትዮጵያ ሀገር አቀፍ የእድሮች ማህበራት ጥምረት፣ የኢትዮጵያ ሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ፣ የወረዳ ፍርድ ቤት ዳኞች፣ የወረዳ (ልዩ ወረዳ) አስተዳደር ተወካዮች በተሳታፊ ልየታ ተባባሪነት ተመርጠዋል።

በሀገራዊ ምክክሩ የሚሳተፉ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተመረጡ ሲሆን እነሱም፤ እራሳቸውን የሚገልፁበት ዋና መተዳደሪያ ያላቸው ሰዎች፣ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ ዕድሮች፣ የማህበረሰብ መሪዎች /አባቶች/ እናቶች፣ የመንግስት ሰራተኞች፣ መምህራን፣ የእጅ ባለሙያዎች፣ የንግድ ማህበረሰብ ናቸው።

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የዝግጅት ምዕራፍ ማጠናቀቂያ የሆኑት የአጀንዳ መሰብሰብና የተሳታፊዎች ልየታ ስራ እየተከናወነ ይገኛል።

በየአካባቢው ተፈናቅለው የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በያሉበት የመጠለያ ስፍራ እንደ 10ኛ ባለድርሻ አካል የራሳቸውን ተወካዮች የሚያመጡበትን አሰራር ተዘርግቷል ብለዋል።

በአሁኑ ወቅት በድሬዳዋ፣ በሀረሪ፣ በሲዳማ እና በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልሎች እየተካሄደ መሆኑን ጠቅሰው፤ በሚቀጥሉት 10 ቀናት በነዚህ አካባቢዎች የተጀመረው የልየታና የማሰባሰብ ስራ ይጠናቀቃል ነው ያሉት።

ዜጎች በየትኛውም መንገድ አልተወከልንም ብለው ካሰቡ አጀንዳዎቻቸውን ለኮሚሽኑ በአካል፣ በፖስታ፣ በስልክ፣ በበይነ መረብ የሚያስገቡበት አሰራር መዘርጋቱንም ተናግረዋል።

ግጭት ባለባቸው አካባቢዎች የምክክር ዝግጅቶችን ለማከናወን የሚያስችሉ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር ከየአካባቢው አስተዳደሮች ጋር ውይይት በማድረግ በጋራ ለመስራት መግባባት መፈጠሩንም ጠቅሰዋል።

ኮሚሽኑ በተንቀሳቀሰባቸው አካባቢዎች ህዝቡ ሰላም እንደሚፈልግ እና ጥያቄዎቹንም በውይይት የመፍታት ፅኑ አቋም እንዳለው ተረድተናል ነው ያሉት።

ለትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርም በምክክሩ አስፈላጊነትና አካሄድ ላይ ውይይት አድርጎ ወደ ስራ ለመግባት ደብዳቤ ተፅፎ ምላሽ እየተጠባበቅን ነው ብለዋል።

በመሆኑም ትግራይ ክልልን ጨምሮ በሁሉም ክልሎች በሚገኙ ወረዳዎች የተሳታፊዎች ልየታና አጀንዳ የማሰባሰብና የመረጣ ስራ አስቸጋሪ ሁኔታ ካላጋጠመ በስተቀር የ2015 በጀት ዓመት ከመጠናቀቁ በፊት እንደሚጠናቀቅ ጠቁመዋል።

ይህን በስኬት በማጠናቀቅ በሚቀጥለው ዓመት በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ሀገራዊ ምክክሩን ለማካሄድ ሰፊ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

እያንዳንዱ የህብረተሰብ ክፍል ከየወረዳዎች 50 ሰዎችን በተሳታፊነት እንደሚልክ ጠቅሰው በሀገራዊ ምክክሩ እስከ 700 ሺህ ኢትዮጵያውያን በቀጥታ ሊሳተፉ እንደሚችሉም ኮሚሽነሩ ጠቁመዋል።

በክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ደረጃ ለሚደረጉ የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራዎች ሁሉም የሕብረተሰብ ክፍሎች ሁለት ሁለት ተወካዮችን ይመርጣሉ ብለዋል፡፡

የኪነጥበብ ባለሙያዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ ፖለቲከኞች፣ ምሁራን፣ ወጣቶችን ጨምሮ ሁሉም ለኮሚሽኑ እያደረጉ ያሉትን ትብብር አጠናክረው እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል።
1.1K views17:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 20:00:29
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ ከማይክ ሀመር ጋር ተወያዩ
********************
(ኢ ፕ ድ)

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሐመር እና በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ ጉዳይ ፈጻሚ አምባሳደር ትሬሲ አን ጃኮብሰን ጋር መከሩ፡፡

ውይይታቸውም የሁለቱን ሀገራት የሁለትዮሽ ግንኙነት ማጠናከር በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ነው።

የአገራቱ የጋራ ፍላጎት በሆኑ ጉዳዮች ላይ ተቀራርበው ለመስራት መስማማታቸው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
967 views17:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 16:03:20 ኢጋድ ግጭትን ቀድሞ ለመከላከልና ችግሮችን በእርቅ መፍታት የሚያስችሉ ስራዎችን እየሰራ መሆኑን ገልጸ
******
(ኢ ፕ ድ)


የምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት ድርጅት(ኢጋድ) ግጭትን ቀድሞ መከላከልና ከተከሰቱም በኋላ በእርቅ እንዲፈቱ እየሰራ እንደሚገኝ የድርጅቱ ዋና ጸኃፊ ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ ገለጹ።


ድርጅቱ የ2022 ዓመታዊ ሪፖርቱን ይፋ ባደረገበት ወቅት ጽንፈኝነትንና ተሻጋሪ ወንጀሎችን ለመከላከልም እየሰራ መሆኑን ዋና ጸሀፊው አሰታውቀዋል።


ባለፈው አንድ ዓመት በቀጣናው የተከሰቱ ሰፊና ውስብስብ ችግሮችን ከመፍታት ረገድ ኢጋድ ጉልህ ሚና መጫወቱን ዋና ጸኃፊው ተናግረዋል።


በተለያዩ የድርጅቱ አባል ሀገራት ውስጥ ለተከሰቱ የፖለቲካና የጸጥታ ችግሮች ምላሽ ለመስጠት የግጭት ቅድመ መከላከል ዲፕሎማሲን እንዲሁም ችግሮች ከተከሰቱም በኃላ በእርቅ የመፍታት ስራዎችን መስራቱንም ዋና ጸኃፊው ገልጸዋል።


በዚህም ድርጅቱ በደቡብ ሱዳንና በኢትዮጵያ የተፈጠሩ ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ በእርቅ እንዲፈቱ ያደረገውን አስተዋጽኦ እንደ አብነት አንስተዋል።

በተጨማሪም፤ በሱማሊያና በቀይ ባህር እንዲሁም በኤደን ባህረ ሰላጤ አካባቢዎች በድረ-ግጭት መልሶ ግንባታ ላይ ድርጅቱ ያበረከተውን ሚና እንደ ምሳሌ ጠቅሰዋል።

በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ የሚከሰት ድርቅና የምግብ እጥረትን ለመከላከል የአደጋ ስጋት አመራር፣ የአየር ንብረት ማጣጠሚያና አደጋን የመቀነስ እንዲሁም ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢንሼቲቭን በመንደፍ ሲንቀሳቀስ መቆየቱንም ገልጸዋል።

በተጨማሪም የቀጣናውን የግብርና እንቅስቀሴ ለማዘመን ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱን የተናገሩት ዶክተር ወርቅነህ የግብርና ምርታማነትን ለማዘመን እንደ “ብሉ ኢኮኖሚ” የመሳሰሉ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ማድረጉን አመላክተዋል።

እንደ ኢዜአ ዘገባ ፍልሰትን በተመለከተም በዓመቱ ቀጣናዊ የፍልሰት አስተዳደር ኢኒሼቲቮችን ተግባራዊ ማድረጉን የገለጹት ዋና ጸኃፊው ድርጅቱ በቀጣናው በነጻነት የመዘዋዋር ፕሮቶኮልንና የሬሚታንስ ፖሊሲ ማሻሻያዎችን መተግበሩን አብራርተዋል።

ዶክተር ወርቅነህ ድርጅቱ የጀመራቸውን ስራዎች አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸው አባል ሀገራትም ሚናቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል።
1.6K views13:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 16:02:59
1.4K views13:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 15:37:08
ኢትዮጵያ ከተባበሩት መንግስታት ዩኤን ሀቢታት መርሃ-ግብር ጋር ያላትን አጋርነት ለማጠናከር ቁርጠኛ ነች
********************************
(ኢ ፕ ድ)

የኢትዮጵያ መንግስት ከተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ሰፈራ መርሃ-ግብር (UN-Habitat) ጋር ያለውን ትብብርና አጋርነት የበለጠ ለማጠናከር ቁርጠኛ መሆኑን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር አስታወቀ።


"ለተሻለ የከተማ ዕድገት!" በሚል እየተካሄደ የሚገኘውን ጉባኤ የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ በይፋ ከፍተዋል።


በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ፈንታ ደጀን የሚመራ የኢትዮጵያ ልዑክ በጉባኤው እየተሳፈ ነው። በመድረኩም ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ፈንታ ደጀን ኢትዮጵያን አሰመልክተው ማብራሪያ ሰጥተዋል።


ሚኒስትር ዴኤታው በንግግራቸው፣ የኢትዮጵያ መንግስት ከተባበሩት መንግስታት ከዩ ኤን ሃቢታት መርሃ ግብር (UN-Habitat) ጋር ያለውን ትብብር እና አጋርነት የበለጠ ያጠናክራል፡፡


የኢትዮጵያ መንግስት በከተማ ሴክተር እያከናወናቸው ያሉ ዋና ዋና የፖሊሲ መዋቅራዊ ለውጦችንም ገልጸዋል።


ጉባኤው እስከ ሰኔ 2 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ እንደሚቀጥል ከሚኒስቴር መሠሪያ ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
1.5K views12:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 14:08:56
በመንገድ ትራፊክ አደጋ ምክንያት ከአንድ ነጥብ ሰባት ቢሊየን ብር በላይ ጉዳት ደርሷል
*******************
(ኢ ፕ ድ)


በበጀት ዓመቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በመንገድ ትራፊክ አደጋ ምክንያት ከአንድ ነጥብ ሰባት ቢሊየን ብር በላይ ጉዳት መድረሱን የመንገድ ደንነትና መድን ፈንድ አገልግሎት አስታወቀ፡፡


ከግንቦት 30 እስከ ሰኔ 25 የመንገድ ደንነት የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐግብር ይካሄዳል።


የመንገድ ደንነትና መድን ፈንድ አገልገሎት ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል አባሶ ጋዜጣዊ መግለጫ በሰጡበት ወቅት ባለፉት ዘጠኝ ወራት በደረሰ የትራፊክ አደጋ ምክንያት ከአንድ ነጥብ ሰባት ቢሊየን ብር በላይ ንብረት ወድሟል፡፡


የመንገድ ትራፊክ አደጋ ለመቀነስ በቅንጅት እየተሰራ ነው ያሉት ዋና ስራ አስፈጻሚው አደጋውን ለመቀነስ ከግንቦት 30 እስከ ሰኔ 25 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መረሐግብ ይካሄዳል።


በፌደራል ፓሊስ ወንጀል መከላከል ጠቅላይ መምሪያ የትራፊክ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር ደነቀ ክፍሌ በበኩላቸው የሚሰጠው የመንገድ ደህንነት ግንዛቤ አደጋውን ለመቀነስ ይረዳል። በአዲስ አበባ፣ በድሬ ደዋ፣ በአማራ፣ በደቡብና ሐረሪ ክልሎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሐግብሩ እንደሚካሄድ ተናግረዋል፡፡

በልጅዓለም ፍቅሬ
1.7K views11:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ