Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Press Agency/አማርኛ /

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethpress — Ethiopian Press Agency/አማርኛ / E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethpress — Ethiopian Press Agency/አማርኛ /
የሰርጥ አድራሻ: @ethpress
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.66K
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 3

2023-06-06 12:54:36
ሂዩማን ራይትስ ዎች ላወጣው ሪፖርት ከኢ.ፌ.ዲ.ሪ. መንግሥት የተሰጠ ምላሽ
1.7K views09:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-06 11:58:25
የግንቦት 29 ቀን 2015 ዓ.ም የስራ ማስታወቂያ
1.7K views08:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 15:11:15
ባለፉት 10 ወራት ከ20 ሺ በላይ ግብር ከፋዮች የኤሌክትሮኒክ የክፍያ ዘዴን ከ61 ቢሊዮን ብር በላይ ከፍለዋል
************************
(ኢ ፕ ድ)
በበጀት ዓመቱ ባለፉት 10 ወራት ከ20 ሺ በላይ ግብር ከፋዮች በኤሌክትሮኒክ የክፍያ ዘዴን በመጠቀም ከ61 ቢሊዮን ብር በላይ ከፍያ መፈጸማቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አሰታወቀ።
በገቢዎች ሚኒስቴር የገቢ ሂሳቦች ዳይሬክቶሬት ገቢ ሂሳቦች ማጠቃለያ ቡድን አስተባባሪ ወ/ሮ ኤልሳቤጥ አሸናፊ እንደገለፁት በ2015 በጀት ዓመት አስር ወራት ውስጥ በኤሌክትሮኒክ የመክፈያ ዘዴ ግብራቸውን ከከፈሉ 20 ሺህ 772 ግብር ከፋዮች ውስጥ 8 ሺህ 56 ግብር ከፋዮች በዘንድሮ የበጀት ዓመት የክፍያ አማራጩን ለመጠቀም የተመዘገቡ ግብር ከፋዮች ናቸው፡፡
በተጨማሪም 61 ቢሊዮን 468 ሚሊዮን 847 ሺህ 530 ብር በአስር ወሩ በዚሁ የክፍያ መንገድ መሰብሰብ ተችሏል።
ስርዓቱ ግብር ከፋዮች ከአላስፈላጊ የገንዘብና የጊዜ ብክነት ተላቀው በቀላሉ ግዴታቸውን እንዲወጡ ያስቻለ መሆኑን ቡድን አስተባባሪዋ አንስተዋል፡፡
በአጠቃላይ የኤሌክትሮኒክ መክፈያ ስርዓት ከተዘረጋበት ጊዜ አንስቶ 22 ሺህ 419 ግብር ከፋዮች የከፈሉ ሲሆን 127 ቢሊዮን 180 ሚሊዮን 14 ሺህ 279 ብር በዚሁ የመክፈያ አማራጭ መሰብሰቡ ተመልክቷል፡፡
1.7K views12:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 12:53:44
1.8K views09:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 12:00:31
የኢፕድ የስራ ማስታወቂያ፤ መልካም ዕድል
2.0K views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 11:53:38
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አሜሪካ አትላንታ ከተማ በሳምንት አራት ጊዜ የሚያደርገውን በረራ ጀምሯል
*********************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ አሜሪካ አትላንታ ከተማ በሳምንት አራት ጊዜ የሚያደርገውን በረራ መጀመሩን አሰታውቋል።
በሥነ-ሥርዓቱ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ መስፍን ጣሰው፣ የአትላንታ ከተማ ከንቲባ አንድሬ ዲክሰን፣ በኢትዮጵያ የአሜሪካ ጉዳይ ፈፃሚ ትሬሲ አን ጃኮብሰንን ጨምሮ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በአትላንታ ከተማ ከንቲባ አንድሬ ዲክሰን የተመራልዕኩ በአዲስ አበባ የስራ ጉብኝት ማድረጉ ይታወሳል።
1.9K views08:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 10:22:08 ከኢትዮጵያና ከውጭ ሀገራት የተውጣጡ ከ500 በላይ ተሳታፊዎች የሚካፈሉበት ሀገር አቀፍ ኮንፍረንስ ይዘጋጃል
**********************
(ኢ ፕ ድ)
ከኢትዮጵያና ከውጭ ሀገራት የተውጣጡ ከ500 በላይ ተሳታፊዎች የሚካፈሉበት ሀገር አቀፍ ኮንፍረንስ ሊያዘጋጅ መሆኑን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር አሰታወቀ።
ኮንፈረንሱ "ማህበራዊ ጥበቃ ለሃገር ገጽታ" በሚል መሪ ቃል ግንቦት 15 እስከ 16 ቀን 2015 ዓ.ም የሚካሄድ ይሆናል።
የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶክተር) በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቁት፣ በኮንፈረንሱ ከኢትዮጵያና ከተለያዩ የውጭ ሀገራት የተውጣጡ ከ500 በላይ ተሳታፊዎች ይሳተፋሉ።
በመድረኩ የማህበራዊ ጥበቃ ፕሮግራሞች አተገባበርና ሥርዓት ግንባታን የሚሳዩ አገራዊና ዓለም አቀፋዊ ይዘት ያላቸው መልዕክቶች ይቅርባሉ ያሉት ሚኒስትሯ በምሁራንና በባለሙዎች ጥናታዊ ጽሁፎች ቀርበው ውይይት ይደረጋል።
በሃገሪቱ በተለያዩ ተቋማት በማህበራዊ ጥበቃ እየተተገበሩ ያሉ ፕሮግራሞችን የሚያሳይ ኤግዚቢሽንም ለዕይታ ይቀርባል።
ኮንፈረንሱ የተለያዩ አካላትን ግንዘቤ ለማሳደግና በቀጣይ ሁሉም አካላት ሁለንተናዊ ተሳትፎና ድጋፍ እንደያጎለብቱ በማድረግ ጠንካራ የማህበራዊ ጥበቃ ስርዓት በመዘርጋት ዜጎችን ይበልጥ ተጠቃሚ ለማድረግ እገዛ እንደሚደርግ ይጠበቃል ብለዋል።
ኮንፈረንሱ ግንቦት 15 እና 16 የሚካሄድ ይሆናል ተብሏል።
በዳግማዊት አበበ
1.8K views07:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 10:22:05
1.6K views07:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 09:50:58
የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ልዑክ በ ’ላፕሴት’ ፕሮጀክት ስብስባ ላይ ለመሳተፍ ጁባ ገባ
*******************
(ኢ ፕ ድ)
የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ልዑክ በ ’ላፕሴት’ ፕሮጀክት ስብስባ ላይ ለመሳተፍ ደቡብ ሱዳን ጁባ ገብቷል።
ልዑኩ ጁባ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ በደቡብ ሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ነቢል ማሃዲ አቀባበል አድርገውለታል።
የኢትዮጵያ መንግስት ልዑክ በደቡብ ሱዳን በሚኖረው ቆይታ ኢትዮጵያ፣ኬንያና ደቡብ ሱዳንን በትራንስፖርት ለማስተሳሰር ያለመው ላፕሴት ፕሮጀክት አስመልክቶ በተዘጋጀው ውይይት ላይ እንደሚሳተፍ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
በተጨማሪም ከደቡብ ሱዳን የመንግስት የስራ ኃላፊዎች ጋር በሁለትዮሽና የጋራ ፍላጎት በሆኑ ቀጣናዊ ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ እንደሚጠበቅ ገልጿል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
የላፕሴት ፕሮጀክት እ.አ.አ በ2012 በኢትዮጵያ፣ኬንያና ደቡብ ሱዳን አገራት መሪዎች የጋራ ስምምነት ወደ ስራ እንዲገባ ውሳኔ መተላለፉ የሚታወስ ነው።
1.7K views06:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-17 09:31:33
ከ59 ሺህ በላይ የመዲናዋ ነዋሪዎች በከተማ ግብርና ላይ እየተሳተፉ ነው
******************
(ኢ ፕ ድ)
በአዲስ አበባ በከተማ ግብርና የሚሳተፉ ዜጎች ቁጥር ከ59 ሺህ በላይ መድረሱን የአዲስ አበባ ከተማ አርሶ አደርና ከተማ ግብርና ልማት ኮሚሽን አስታወቀ።
የኮሚሽኑ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አካሌ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በመዲናዋ በከተማ ግብርናና ሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ዜጎች በስፋት እንዲሳተፉ ጥረት እየተደረገ ይገኛል።
በዘጠኝ ወራት በእንስሳት ዘርፍ 17 ሺህ 224፣ በአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ 42 ሺህ 374 በድምሩ 59 ሺህ 571 ዜጎች በከተማ ግብርና ተጠቃሚ መሆን ችለዋል ሲሉ አስታውቀዋል።

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=99689
1.7K views06:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ