Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Press Agency/አማርኛ /

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethpress — Ethiopian Press Agency/አማርኛ / E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethpress — Ethiopian Press Agency/አማርኛ /
የሰርጥ አድራሻ: @ethpress
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.66K
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 9

2023-04-23 17:28:17 የአፍሪካ አገራት በሰሜን ኢትዮጵያ አጋጥሞ የነበረው ችግር ከተፈታበት መንገድ ትምህርት ሊወስዱ ይገባል
- ኡሁሩ ኬኒያታ የቀድሞ የኬንያ ፕሬዝዳንት
*****
(ኢ ፕ ድ)

በግጭት ውስጥ ያሉ የአፍሪካ አገራት በሰሜን ኢትዮጵያ አጋጥሞ የነበረው ችግር ከተፈታበት መንገድ ትምህርት ሊወስዱ እንደሚገባ የቀድሞ የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬኒያታ ተናገሩ።

በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም በመንግስትና ህወሃት የሰላም ስምምነት የመጣውን ውጤት ተከትሎ “ጦርነት ይብቃ ሰላምን እናጽና” በሚል መሪ ሃሳብ በአዲስ አበባ ወዳጅነት ፓርክ የእውቅና እና ምስጋና መርሃ ግብር በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በመርሃ ግብሩ ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የቀድሞው የኬንያ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬኒያታ በኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የተከናወነው ስራ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለመላው አፍሪካ ኩራት ስለመሆኑ ጠቅሰዋል።

የዛሬው እለት የኢትዮጵያውያን ቀን ነው ያሉት ኡሁሩ ኬንያታ "ለሰላም ጥረት ያደረጋችሁ ሁሉ እና መላ ኢትዮጵያዊያን እንኳን ደስ አላችሁ" ብለዋል።

በኢትዮጵያ የሚፈለገው ሰላም እውን ሆኗል፤ በመሆኑም በግጭት ውስጥ ያሉ የአፍሪካ አገራት በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ችግር ከተፈታበት መንገድ ትምህርት በመውሰድ ሰላም ማምጣት አላባቸው ሲሉ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

አፍሪካ ለራሷ ችግር በራስ መፍትሄ ማምጣት እንደምትችል በተግባር አሳይታለች ያሉት የቀድሞው ፕሬዝዳንት በኢትዮጵያ የመጣው ሰላም ለመላ አፍሪካዊያን ጥሩ ተምሳሌት ተደርጎ ሊወሰድ ይገባል ነው ያሉት።

መጪው ጊዜ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብና አጠቃላይ ለአፍሪካ ዘላቂ ሰላምና ብልጽግና እውን እንዲሆን እመኛለሁ ብለዋል።

በመርሐ ግብሩ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ፣ በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልእክተኛ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ፣ የደቡብ አፍሪካ የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ትብብር ሚኒስትር ናሌዲ ፓንዶር፣ የአፍሪካ ሀብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ሙሳፋኪ ማሃማት እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል ሲል ኢዜአ ዘግቧል።
1.2K views14:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 17:28:06
1.1K views14:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 11:50:43
ለውጭ ገበያ ከቀረበ የሥጋና የእርድ ተረፈ ምርት 74 ሚሊዮን ዶላር ተገኘ
*****************
(ኢ ፕ ድ)
ባለፉት ዘጠኝ ወራት ኢትዮጵያ ለውጭ ገበያ ካቀረበችው የሥጋና የእርድ ተረፈ ምርቶች 74 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን የእንስሳት ልማት ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡
የኢንስቲትዩቱ የማህበራዊ ምጣኔ ሀብት አስተዳደር ምርምር ዘርፍ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሳህሉ ሙሉ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የሥጋና የእርድ ተረፈ ምርቶች በኢንዱስትሪ ውስጥ ተቀነባብረው በስፋት ለውጭ ገበያ ተልከዋል።
ለውጭ ገበያ ከቀረበው 16 ሺህ 300 ቶን የሥጋና የእርድ ተረፈ ምርት 74 ሚሊዮን ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=97553
1.8K views08:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 11:49:51
በሶማሌ ክልል ከ593 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት እየለማ ነው
****************
(ኢ ፕ ድ)
የወቅቱን ዝናብ በመጠቀም ከ593 ሺህ በላይ ሄክታር መሬት እየለማ መሆኑን የሶማሌ ክልል አስታወቀ። ከበልግ ግብርና ሥራዎችም ከ20 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡
የሶማሌ ክልል የግብርና ቢሮ የሰብል ልማትና ጥበቃ ዳይሬክተር አቶ አብዲ አደን ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በክልሉ የወቅቱን ዝናብ በመጠቀም በተለያዩ አካባቢዎች የግብርና ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።
ለማልማት ከታቀደው 593 ሺህ 324 ሄክታር መሬት 20 ሚሊዮን 197 ሺህ 712 ኩንታል ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=97549
1.4K views08:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 11:03:08
የኦሮሚያ ክልል ለአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር 12ሺህ ኩንታል የችግኝ ዘር አሰራጭቷል
**********************
(ኢ ፕ ድ)
የኦሮሚያ ክልል ለአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር ከ12ሺህ ኩንታል በላይ የችግኝ ዘር ለተለያዩ የችግኝ ጣቢያዎች ማሰራጨቱን አስታወቀ።
በአሁኑ ወቅትም አራት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ችግኝ መዘጋጀቱ ተጠቅሷል፡፡
የኦሮሚያ ክልል ግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ጌቱ ገመቹ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንዳስታወቁት፤ የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ሥራው በዋናነት አርሶ አደሩ የተፋሰስ ልማት ላይ ትኩረት አድርጎ እየተሠራ ይገኛል።ከ12ሺህ ኩንታል በላይ የችግኝ ዘር በእያንዳንዱ የችግኝ ጣቢያ ላይ ተከፋፍሎ በአሁኑ ወቅት ወደ አራት ነጥብ ስድስት ቢሊዮን ችግኝ ተዘጋጅቷል።
እንደ ቢሮ ኃላፊው ገለጻ፤ በበጋው ስድስት ሺህ የሚሆኑ የተፋሰስ ...
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=97539
1.3K views08:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 11:02:30
ክልሉ ከአራት ቢሊዮን ብር በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች ፈቃድ ሰጥቷል
**********************
(ኢ ፕ ድ )
ባለፉት ስምንት ወራት ከአራት ቢሊዮን 323 ሚሊዮን በላይ ካፒታል ላስመዘገቡ ባለሀብቶች የኢንቨስትመንት ፈቃድ መስጠቱን የአፋር ክልል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።ከሰላም ስምምነቱ በኋላ በክልሉ በኢንቨስትመንቱ ዘርፍ ላይ ከፍተኛ መነቃቃት መታየቱ ተጠቁሟል፡፡
የአፋር ክልል ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ኮሚሽነር ወይዘሮ አይሻ መሐመድ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ ባለፉት ሁለት እና ሦስት ዓመታት በሰሜን ኢትዮጵያ ከነበረው ጦርነት ጋራ ተያይዞ የክልሉ ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=97534
1.3K views08:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 10:11:52
አንጋፋው የአፋን ኦሮሞ ድምፃዊ ዘሪሁን ወዳጆ አረፈ
**************
(ኢ.ፕ.ድ)

አንጋፋው የአፋን ኦሮሞ ድምፃዊ ዘሪሁን ወዳጆ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

ድምጻዊ ዘሪሁን ወዳጆ ከረዥም ጊዜ ህክምና በኃላ ከህመሙ ማገገም ባለመቻሉ ማረፉ ነው የተገለጸው።

የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ በድምጻዊው ህልፈ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ለአርቲስቱ ቤተሰቦች፣ ወዳጅ ዘመዶቹና አድናቂዎቹ መጽናናትን ይመኛል።
1.3K views07:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 10:03:13
ለኩላሊት ሕክምና በቂ ትኩረት ባለመሰጠቱ መቸገራቸውን ታካሚዎች ገለጹ
ጤና ሚኒስቴር አገልግሎቱን ለማሻሻል እንደሚሠራ አስታውቋል
*************************
(ኢ ፕ ድ)
ለኩላሊት በሽታ የሚሰጠው ትኩረት እጅግ አናሳ በመሆኑ በሕክምና ተቋማት በቂ ሕክምናና የመድኃኒት አቅርቦት እያገኘን አይደለም ሲሉ የኩላሊት በሽታ ታካሚዎች ገለጹ።የጤና ሚኒስቴር በበኩሉ አገልግሎቱን ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑን አስታውቋል፡፡
የኩላሊት ታማሚ ሆኖ ዲያሊሲስ ከጀመረ አንድ ዓመት ከ6 ወር የሆነው ወጣት አቶ ሁሴን አሊ እንደገለጸው፤ የኩላሊት ሕመም ሲያጋጥም ፈተናዎቹ በርካታ ናቸው።ምንም እንኳን የጳውሎስ አጠቃላይ ሆስፒታል የኩላሊት ንቅለ ተከላ ሕክምና መስጠት ከጀመረ ዓመታት ቢቆጠሩም አሁንም በርካታ ታማሚዎች ወደ ውጭ አገር ሄደው እየታከሙ ነው።ውጭ አገር ሄደው ሕክምናውን ለማግኘት ጎዳና ላይ ወጥተው የሚለምኑም በርካቶች ናቸው።

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ
https://www.press.et/?p=97531
1.5K views07:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 09:51:46
ግብርናው ከዝናብ ጥገኝነት ተላቆ ወደመስኖ ሥራ እንዲሸጋገር እየተሠራ ነው

እስካሁን 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በመስኖ ለምቷል
****************
(ኢ ፕ ድ)

ግብርናው ከዝናብ ጥገኝነት ተላቆ ወደ መስኖ ሥራ እንዲሸጋገር በትኩረት እየተሠራ ነው ሲሉ በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሀብት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር እያሱ ኤሊያስ ገለጹ።

በኢትዮጵያ በተለያዩ የውሃ አማራጮች 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በመስኖ ማልማት እንደተቻለ የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

ፕሮፌሰር እያሱ ኤሊያስ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ግብርና ላይ የተመሠረተ ቢሆንም ግብርናው ዝናብ ላይ ጥገኛ ሆኖ በመቆየቱና በአየር ለውጥ ምክንያት የዝናብ መቆራረጥ ሲያጋጥም ጫና ይደርስበታል።

ጫናውን ለመቀነስ በዋናነት በዝናብ ጥገኝነት ላይ ተመስርቶ ለበርካታ ዓመታት ሲሠራበት የቆየውን አሠራር ወደመስኖ ልማት እንዲቀየር ሰፊ ጥረት እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=97411
757 views06:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 09:50:09
በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ጥቅምና ደህንነት የሚያስከብር ሕጋዊ ሥርዓት ተዘረጋ
****************
(ኢ ፕ ድ)
በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን ጥቅም፣ መብትና ደህንነት ማስከበር የሚያስችል ሕጋዊ ሥርዓት መዘርጋቱን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ።

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል ከውጭ አገራት የሥራ ስምሪት ጋር ተያይዞ የተገኙ ውጤቶችን በተመለከተ መግለጫ ሰጥተዋል።

በሚኒስትር ሙፈሪያት ካሚል የተመራ ልዑክ በቤይሩት፣ በሊባኖስና በሳዑዲ አረቢያ ተዘዋውሮ ዜጎች የተሻለ ደመወዝ እንዲከፈላቸው፣ መብትና ደህንነታቸው እንዲከበር ለማድረግ ከአገራቱ መንግሥታት ጋር ስምምነት መደረጉን በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል።

የተደረሰው ስምምነት ዜጎች ወደነዚህ አገራት በሕጋዊ መንገድ ገብተው መሥራት ....
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ https://www.press.et/?p=97415
691 views06:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ