Get Mystery Box with random crypto!

Ethiopian Press Agency/አማርኛ /

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethpress — Ethiopian Press Agency/አማርኛ / E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethpress — Ethiopian Press Agency/አማርኛ /
የሰርጥ አድራሻ: @ethpress
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 19.66K
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-04-28 09:57:01
የ90 ቀን ፕሮጀክቶች ለከተማዋ ውበት ከማጎናጸፍ ባሻገር የሥራ ዕድል እየፈጠሩ ነው
***
(ኢ ፕ ድ)
የ90 ቀን ፕሮጀክቶች ለከተማዋ ውበትና መልካም ገጽታን ከማጎናጸፋቸውም ባሻገር ለዜጎች የሥራ ዕድል እየፈጠሩ መሆኑ ተገለጸ። በቂርቆስ ፓርክ የመሥሪያ ቦታ ያገኙ ወጣቶች የዕድሉ ተጠቃሚ በመሆናቸው ሕይወታቸውን ለመቀየር ምቹ አጋጣሚ እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።
https://www.press.et/?p=98059
2.0K views06:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-28 09:54:27
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ከሱዳን ተፋላሚ ሃይሎች ጋር መወያየታቸውን ገለፁ
*********************
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከሱዳን ጦር ዋና አዛዥ ጀኔራል አብዱል ፈታህ አልቡርሃን እና ከሱዳን ፈጥኖ ደረሽ ሃይሎች ዋና አዛዥ ሞሃመድ ሃምዳን ዳጋሎ ጋር በስልክ ተወያይተዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስ ገጻቸው፣ ሁለቱ መሪዎች ልዩነቶቻቸውን በምክክር እንዲፈቱና ለሀገራቸው መረጋጋትን ማምጣት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ተወያይተናል ብለዋል። የሱዳን ሕዝብ ሰላም ያስፈልገዋል ሲሉ ገልጸዋል።
1.8K views06:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 18:27:58
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መልዕክት

ሐሳብን በሐሳብ ማሸነፍ ያቃታቸው አካላት የወንድማችንን የግርማ የሺጥላን ነፍስ ነጥቀዋል።

ልዩነትን በሠለጠነ መንገድ መፍታት ባህል በሆነበት ክፍለ ዘመን፣ በሐሳብ የተለየንን ሁሉ በጠመንጃ ለማሳመን መነሣት የጽንፈኝነት የመጨረሻው ጥግ ነው።

ተወልዶ ባደገበት አካባቢ ፣ ከእኛ የተለየ ሐሳብ ማሰብ አልነበረበትም ብለው የሚያምኑ ነውጠኛ ጽንፈኞች የፈጸሙት አስነዋሪና አሰቃቂ ተግባር፣ ጽንፈኝነትን በጊዜ ታግለን ካላስወገድነው ወደ መጨራረስ እንደሚወስደን ጉልሕ ማሳያ ነው።

ነፍስህ በሰላም ትረፍ
2.5K views15:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 17:21:29
"ከትግራይ ወንድሞቻችን ጋር ችግሮቻችንን በውይይትና በመግባባት ለመፍታት ዝግጁ ነን"
- ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ
***********************
(ኢ ፕ ድ)
ከትግራይ ወንድሞቻችን ጋር ችግሮቻችንን በውይይትና በመግባባት ለመፍታት ዝግጁ ነን ሲሉ መቀሌ ካመራው የመንግሠት የሥራ ኃላፊዎች ጋር የተጓዙት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶክተር ይልቃል ከፋለ ተናገሩ።

ርዕሰ መስተዳደሩ ሠላምና መግባባት ያስፈልገናል፤ችግሮችን በሰለጠነ መንገድ በውይይት ለመፍታት ዝግጁ ነን ብለዋል።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደርና የኃይማኖት አባቶች ባህርዳር መጥታችሁ እንድንወያይ ሲሉ ጥሪ አቅርበዋል።

በቀጣይም ወደ ትግራይና አፋር ክልሎች የህዝብ ተወካዮችን በመያዝ እንደሚሄዱም ተናግረዋል።

በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ የተመራ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና የመንግሥት ሥራ ኃላፊዎች ቡድን በትግራይ ያደረገው ጉብኝት በጋራ የትብብር መንፈስ ለመስራት ጅማሮ የታየበት መሆኑን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ገልጸዋል።

በጌትነት ተስፋማርያም(መቐለ)
2.3K views14:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-27 13:25:28
በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ የተመራው ቡድን በውቅሮ ጉዳት የደረሰባቸውን ኢንዱስትሪዎች ተዘዋውሮ ጎበኘ
*******************
(ኢ.ፕ.ድ)
በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አደም ፋራህ የተመራውና የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የተካተተበት ቡድን በትግራይ ውቅሮ የሚገኙና በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውን ኢንዱስትሪዎች ተዘዋውሮ ጎብኝቷል።
ቡድኑ በጦርነቱ ወቅት ሠፊ ጉዳት የደረሰባቸው የሠማያታ የእምነበረድ ማምረቻ ፋብሪካና ሼባ ሌዘር ኢንደስትሪዎችን ጎብኝቷል።
የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮችና የከተማ አስተዳደሮች ለትግራይ ክልል መልሶ ግንባታ የሚውል የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያደርጉም ታውቋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሁሉም ክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች በብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት እየተመሩ ወደ መቀሌ ይሄዳሉ ባሉት መሠረት ፤በአቶ አደም ፋራህ የተመራውና የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች፣ ሚኒስትሮችና ባለስልጣናት የተካተቱበት ቡድን መቀለ ዛሬ ማለዳ መግባቱ ይታወሳል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳና ሌሎች የአስተዳደሩ ኃላፊዎችም አቀባበል እንዳደረጉለት ኢፕድ ከስፍራው መዘገቡ ይታወቃል።
በጌትነት ተስፋማርያም (መቀለ)
2.1K views10:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 19:06:26
የትግራይ ህዝብ አሁን ያገኘው ሰላም ወደ ኋላ እንዲመለስ ፈጽሞ አይፈቅድም - አቶ ጌታቸው ረዳ
********************
(ኢ ፕ ድ )

የትግራይ ህዝብ አሁን ያገኘው ሰላም ወደ ኋላ እንዲመለስ ፈጽሞ አይፈቅድም ሲሉ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርእሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ ገለጹ።

"ከይዋጣልን መንፈስ ወጥተን ለኢትዮጵያ ሰላም በየቀኑና በጋራ መስራት አለብን" ሲሉም ተናግረዋል።

የፕሪቶሪያውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ በሂደቱ አስተዋጽኦ ላደረጉ ሁሉ በአዲስ አበባ የእውቅና እና ምስጋና መርሐግብር በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በመድረኩ ላይ መልእክት ያስተላለፉት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርእሰ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ፤ የትግራይ ህዝብ አሁን ያገኘውን ሰላም ወደ ኋላ እንዲመለስ ፈጽሞ አይፈቅድም ሲሉም ተናግረዋል።

በመሆኑም ሰላምን ማስፈንና በጋራ መልማት የጋራ እጣ ፈንታችን በመሆኑ የጀመርነውን የሰላም መንገድ ማጽናት ይገባናል ብለዋል።

ፖለቲከኞች ከግጭት አባባሽ አስተሳሰብ ተላቀው ለሰላም ቅድሚያ በመስጠት በትብብር መስራት እንደሚገባቸውም ገልጸዋል።

እንደ ኢዜአ ዘገባ በሰላም ሂደቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ፤ የነበራቸው ቁርጠኝነትና የሄዱበት ርቀት የሚደነቅ ስለመሆኑ ጠቅሰው የሰላም ርምጃዎች እንዲሰፉ ሁሉንም አቅም በማስተባበር መስራት አለብን ብለዋል።
1.2K views16:06
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 18:24:27 ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ለሰላም ስምምነቱ ተግባራዊነት ላደረጉት ብርቱ ጥረት ምስጋና እናቀርባለን
- የናይጀሪያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ
****
(ኢ ፕ ድ)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ለሰላም ስምምነቱ ተግባራዊነት ላደረጉት ብርቱ ጥረት ክብርና ምስጋና ይገባቸዋል ሲሉ በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልእክተኛና የናይጀሪያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ ተናገሩ።

በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም የመንግስትና ህወሃት የሰላም ስምምነትን ተከትሎ የተገኘውን መልካም ውጤት ተከትሎ ለሰላም ሂደቱ አስተዋጽኦ ላደረጉ ሁሉ በአዲስ አበባ የእውቅና እና ምስጋና መርሃ ግብር በመካሄድ ላይ ይገኛል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልእክተኛና የናይጀሪያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ፤ በኢትዮጵያ የተደረሰው የሰላም ስምምነት የአፍሪካን ችግር በአፍሪካውያን መፍታት እንደሚቻል ትምህርት የሰጠ ነው ብለዋል።

በሰላም ስምምነቱ አተገባበር መጀመሪያ ሁሉም ነገር አስቸጋሪ ቢመስልም በስኬት እንደሚጠናቀቅ ጽኑ እምነት ነበረኝ ሲሉ ተናግረዋል።

በሰላም ሂደቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በተለየ መልኩ ለነበራቸው ቁርጠኝነትና ብርቱ ጥረት የላቀ ምስጋና ይገባቸዋል ብለዋል።

በኢትዮጵያ የተደረሰው የሰላም ሰምምነት ስኬት ሁሉንም አፍሪካዊ ያኮራ መሆኑን ጠቅሰው ትጥቅ የፈቱ ታጣቂዎችን መልሶ ለማቋቋም እየተደረገ ያለውን ጥረት ሁሉም አካል እንዲደግፍ ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

የትምህርት ቤቶች ፣ ጤና ጣቢያዎች ዳግም ስራ መጀመር የትራንስፖርት አገልግሎት መከፈት የሰላም ሂደቱን ውጤታማነት የሚያሳዩ መሆኑን ጠቅሰው የሰላም ስምምነቱን ሙሉ ለማድረግ ቀጣይ ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል ይገባል ብለዋል።

የሰላም ስምምነቱን የተሟላ ለማድረግ ሁሉም አካላት በጋራ ሊሰሩ እንደሚገባና በሰላም ስምምነቱ ያገኘነውን ስኬት ስናከበር ለሰላም ያለንን ቁርጠኝነት በተግባር በማረጋገጥ ሊሆን ይገባል ብለዋል።

በጦርነቱ ጉዳት የገጠማቸውና የተፈናቀሉ ዜጎችን መልሶ ለማቋቋም የሚደረገውን ጥረት ሁሉም አካላት እንዲያግዙ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ከዚህ በኋላ በህዝቦች መካከል ዕርቅ በማስፈን፣ የመልሶ ማቋቋም ተግባራትን በማፋጠን ሰላምን፣ ደህንነትንና ልማትን ማፋጠን ይገባል ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ የአፍሪካ መሪ ለመሆን የጀመረችውን ጥረት በስኬት እንደምታጠናቅቅ ያላቸውን ተስፋ መግለጻቸውን የኢዜአ ዘገባ ያመለክታል፡፡

በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም መንግስትና ህወሃት ባደረጉት የሰላም ስምምነት መሰረት የእስካሁኑ የአተገባበር ሂደት በስኬት እየተከናወነ መሆኑ ይታወቃል።

በመርሐግብሩ ላይ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ፣ በአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልእክተኛ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ፣ የኬኒያ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ፣ የደቡብ አፍሪካ የዓለም አቀፍ ግንኙነት እና ትብብር ሚኒስትር ናሌዲ ፓንዶር እና ሌሎችም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።
1.2K views15:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 18:24:24
1.1K views15:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 17:49:48 የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛች አፍሪካዊት ሀገር ብቻ ሳትሆን በሰላም ረገድም አርዓያነትን ያረጋገጠችበት አጋጣሚ ነው
- የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናሌዲ ፓንዶር
********
(ኢ ፕ ድ)

የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛች አፍሪካዊት ሀገር ብቻ ሳትሆን በሰላም ረገድም አርዓያነትን ያረጋገጠችበት አጋጣሚ መሆኑን የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናሌዲ ፓንዶር ተናገሩ።

በሰሜን ኢትዮጵያ የነበረው ጦርነት የተፈታበት መንገድ የአፍሪካን ችግር በአፍሪካ መፍትሄ መቅረፍ እንደሚቻል ያረጋገጠ ነው ብለዋል።

"ጦርነት ይብቃ፤ ሰላምን እናጽና" በሚል መሪ ሀሳብ በመንግስት እና በሕወሃት መካከል በፕሪቶሪያ ለተደረሰው የሰላም ስምምነት ቁልፍ ሚና ለተወጡ አካላት የዕውቅና እና የምስጋና መርሐግብር በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው።

በአፍሪካ ሕብረት መሪነት የተደረሰው የሰላም ስምምነት የተፈረመው ጥቅምት 23 ቀን 2015 ዓ.ም ሲሆን ቀጥሎም በስምምነቱ ትግበራ አፈጻጸም ላይ ወታደራዊ አመራሮች በኬኒያ ናይሮቢ ከተማ ስምምነት ፈርመው ወደ ተግባር ተግብቶ፤ የሰላም ስምምነቱ ተግባራዊ መደረጉ ይታወቃል።

የዕለቱ መርሐግብርም የተደረሰውን የሰላም ሂደት ለማጽናት ያለመ ነው።

በመርሐግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ናሌዲ ፓንዶር በአፍሪካ ሕብረት መሪነት የተደረሰው የሰላም ስምምነት የኢትዮጵያውያን ድል ብቻ ሳይሆን እንደ አፍሪካዊያን የሁላችንም ኩራት ነው ብለዋል።

የፕሪቶሪያ ሰላም ስምምነት የመንግስትና የሕወሃት አመራሮች ወደ ሰላም ለመምጣት ቁርጠኛ አቋም ማሳየታቸውን አስታውሰው፤ አፍሪካ ሕብረትን እና ሂደቱ እንዲሳካ ሚና የተወጡ አካላትን አመስግነዋል።

የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ዕውን መሆን የጥይት ድምጽ የማይሰማባት አፍሪካን ዕውን ለማድረግ ለተያዘው ግብ ስኬት መሆኑን ጠቅሰው፤ ለሰላም ስምምነቱ ዘላቂ ትግበራ ሁሉም ጥረት ማድረግ አለበት ብለዋል።

የሰላም ስምምነቱ ስኬት ወረቀት ላይ መፈረሙ ሳይሆን በተግባር መሬት ላይ ያለው ትግበራ መሆኑን ያወሱት ሚኒስትሯ፤ የድሕረ ሰላም ስምምነት ትግበራው ባደረጉት ክትትል በትግራይ ክልል የሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም በጥሩ ደረጃ እየተተገበረ መሆኑን ማረጋገጣቸውን አንስተዋል።

በቀጣይም ትግበራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ለመከላከያ ሰራዊትና ለሚመለከታቸው አካላት ድጋፍ ማድረግ እንደሚገባ ጠቅሰዋል።

ስምምነቱ ዘላቂ ሰላም፣ ልማትና አንድነት ለማምጣት የተገባ ቃል በመሆኑ ለተግባራዊነቱ ሁሉም ወገኖች በቁርጠኝነት እንዲሰሩም አሳስበዋል።

መሰል የሰላም ሂደቶች አፍሪካ በ2063 አጀንዳ የበለጸገች፣ ሰላሟ የተረጋገጠ፣ አካታች እና ዘላቂ ልማት የተረጋገጠባት አህጉር የማድረግ ግብ እንዲሳካ ሁነኛ አስተዋጽኦ እንዳላቸው አንስተዋል።

ኢትዮጵያ ቅኝ ያልተገዛች ሀገር ብቻ ሳትሆን ችግሮችን በሰላም በመፍታት ለአፍሪካ አርዓያነቷን ያረጋገጠችበት አጋጣሚ መሆኑን ጠቅሰዋል።

እንደ ኢዜአ ዘገባ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በተቀረው የአፍሪካ ክፍል የጥይት ድምጽ የማይሰማባት አህጉር መፍጠር፣ ሰብዓዊ መብት መከበር፣ የዜጎችን ነጻነትና ብልጽግና ዕውን ማድረግ እንዲቻል በጋራ መስራት እንደሚገባም ጥሪ አቅርበዋል።
1.2K views14:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 17:49:45
957 views14:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ