Get Mystery Box with random crypto!

Ethio University

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiouniversty1 — Ethio University E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiouniversty1 — Ethio University
የሰርጥ አድራሻ: @ethiouniversty1
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.85K
የሰርጥ መግለጫ

ለማንኛውም አይነት የማስታወቂያ ስራ እና ክሮስ(Cross)
💰💰 @Cozboy0 💰💰
ያናግሩን🎫🎟🎪🎪🎪🎪

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-04-25 00:32:53 #ብሔራዊ_ፈተና

" እስካሁን የመፈተኛ ጊዜ አልተገለጸም " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

የ2015 ት/ት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች የፈተና ምዝገባ እስከ ሚያዝያ 20/2015 ዓ/ም ድረስ ብቻ እንደሚካሄድ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

አገልግሎቱ ፥ ማንኛውም የስም፣ የፆታ፣ የተፈጥሮ/የማህበራዊ ዘርፍ እና የፎቶ ማስተካከያ ከፈተና በፊት ስለማይደረግ እያንዳንዱ ተፈታኝና እና መዝጋቢ ትክክለኛነቱን የማጣራትና የማረጋገጥ ኃላፊነት አለበት ብሏል።

ይህ መሆን ያለበትም ምዝገባው በበየነ መረብ በመሆኑ በትምህርት ቤት ደረጃ የተካሄደው የምዝገባ መረጃ በቀጥታ በማንም ሳይነካ ወደ ተቋሙ የመረጃ ቋት የሚገባ በመሆኑ ነው ሲል አስረድቷል።

ከሚያዚያ 20/2015 ዓ/ም በኋላ በግለሰብ ወይም በተቋም በኩል የሚመጡ ተመዝጋቢዎችን #አላስተናግድም ሲል በጥብቅ ያሳሰበው አገልግሎቱ ፥ ፈተናው የሚሰጠው በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥና የመፈተኛ ጊዜን ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኋላ እንደሚገለፅ አሳውቋል።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፥ እስካሁን የመፈተኛ ጊዜ አልተገለጸም ያለ ሲሆን ተፈታኞች ተገቢውን ዝግጅት እንዲያደርጉ አሳስቧል።
144 views21:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-24 15:49:11 በትግራል ክልል የተቋረጠውን ትምህርት ለመጀመር በቀጣይ ሳምንት የተማሪዎች ምዝገባ ይጀመራል፦ የክልሉ ትምህርት ቢሮ
******

በትግራይ ክልል በጦርነቱ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን የመማር ማስተማር ሂደት ለማስጀመር በቀጣይ ሳምንት በሁሉም ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ምዝገባ የሚካሄድ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

በትግራይ ክልል በጦርነት ምክንያት ለሦስት ዓመት ተኩል ገደማ ትምህርት ተቋርጦ መቆየቱን የትግራይ ክልል ትምህርት ቢሮ ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ዳኘው አይጠገብ ተናግረዋል።

በተደረሰው የሰላም ስምምነት መሠረት አንፃራዊ ሰላም የተፈጠረ በመሆኑ በክልሉ ከሚያዝያ 18 ጀምሮ በሁሉም ትምህርት ቤቶች የተማሪዎች ምዝገባ ይጀመራል።

ትምህርት ሚኒስቴር በክልሉ ትምህርት ለማስጀመር እያደረገው ያለው መልካም ተግባር እና ጥሩ ተነሣሽነት የሚደነቅ እንደሆነ የጠቆሙት ዳይሬክተሩ፤ ሚኒስቴሩ ቡድን በመላክ ያሉ ችግሮች እንዲፈቱ መሥራቱን ተናግረዋል።

በትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ የተመራ ቡድን መቐለ በመገኘት ትምህርት እንዲጀመር የሚያስችል ሥራ ሲሠራ መቆየቱን በማንሳት፤ በዚህም የጋራ ዕቅድ ተዘጋጅቷል ብለዋል።

በተለይ ችግሮች የሚፈቱበትን መንገድ በመለየት የትምህርት ሚኒስቴር ትኩረት ሰጥቶ ለማገዝ የሚያስችለውን አቅጣጫ ነድፎ ወደ ሥራ መገባቱን ገልጸዋል።

እንደ አቶ ዳኘው ገለጻ፣ ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ጋር በመተባበር በክልሉ ትምህርት ለማስጀመር ሁለንተናዊ ዝግጅት ተጠናቋል።

ከቅድመ አንደኛ ክፍል (ኬጂ) እስከ 12ኛ ክፍል ትምህርት የሚጀምር ሲሆን በተለያየ ምክንያት የተበታተኑ መምህራንን የማሰባሰብ ሥራ ለማከናወንም ራሱን የቻለ ወጥ ሰነድ ተዘጋጅቷል።

የነበረው የደመወዝ አለመከፈል ችግር እንዲፈታ እና ወደ ትምህርት እንዲገባም ውሳኔ ላይ መደረሱን ኢፕድ ዘግቧል።

በክልሉ ላይ የተፈጠረው ችግር ከባድ ከመሆኑ አንፃር በክልሉ ትምህርት ቢሮ ብቻ ለመፍታት ያዳግታል ያሉት ዳይሬክተሩ፤ ሁሉም አካላት ለትግራይ ክልል እገዛ ሊያደርጉ ይገባል ብለዋል።
298 views12:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-23 22:08:09
#JimmaUniversity

ጅማ ዩኒቨርሲቲ የእንግሊዘኛ ቋንቋ መመዘኛ ፈተና (IELTS Test) በተቋሙ ዋና ግቢ ለመስጠት ከብሪቲሽ ካውንስል ጋር ተስማምቷል፡፡

ፈተናው በጅማ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ መሰጠቱ የዩኒቨርሲቲውን ማህበረሰብ እንዲሁም በምዕራብ የሀገሪቱ ክፍል የሚኖሩና ፈተናውን ለመውሰድ ፍላጎት ያላቸው ግለሰቦችን ተጠቃሚ ያደርጋል ተብሏል፡፡

ምዝገባ በማድረግ ነጻ የመዘጋጃ የኦንላይን ኮርሶችን፣ ነጻ የሙከራ ፈተናዎች፣ በየትኛውም ቦታ ለመዘጋጀት የሚያስችል የሞባይል መተግበሪያ እንዲሁም ቪዲዮዎችና ተጨማሪ ግብዓቶችን ማግኘት ይችላሉ፡፡

በኦንላይን ለመመዝገብ፦

ieltsregistration.britishcouncil.org

ፈተናው የሚሰጠው፦ ሰኔ 17/2015 ዓ.ም
419 views19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-22 21:35:48
በርቀት ፕሮግራም በሁለተኛ ዲግሪ ማስተማር ሆነ መማር ተከለከለ

የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን በርቀት መርሐ ግብር በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ማስተማር እንደማይቻል አሳውቋል፡፡

በርቀት መርሐ ግብር በሁለተኛ ዲግሪ ፕሮግራም ማስተማር የማይቻል መሆኑን በባለሥልጣኑ የተቋማት ቁጥጥር፣ ኢንስፔክሽን እና የትምህርት ማስረጃ ማረጋገጫ ም/ዋ/ዳይሬክተር ቸሩጌታ ገነነ ገልጸዋል።

ተማሪዎችን ሲመዘግቡም ሆነ ሲያስተምሩ በሚገኙ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ላይ ጠበቅ ያለ ዕርምጃ እንደሚወሰድ ኃላፊው ተናግረዋል።

በተጨማሪም በዲፕሎማ ደረጃ በግብርና እና በመምህርነት የተማሩ ግለሰቦች ወደ ሌላ የትምህርት ስልጠና ዓይነት ቀጥለው መማር እንደማይችሉ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አስታውሰዋል።

share share

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
508 viewsedited  18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 22:13:09
#RayaUniversity

በራያ ዩንቨርሲቲ መደበኛ ትምህርት ስትከታተሉ ቆይታቹህ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት ትምህርታችሁን ላቋረጣቹህ ተማሪዎች በሙሉ፣

በራያ ዩንቨርሲቲ በመደበኛ ፕሮግራም ከ2ኛ እስከ 5ኛ ዓመት ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የነበራችሁና ወደ ሌሎች ዩንቨርሲቲዎች ተመድባቹህ የመማር ዕድል #ያላገኛቹህ ተማሪዎች በስራ ሰዓት ብቻ ከ09-13/2015 ድረስ በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች እየደወላቹህ ተመዝገቡ።

# Raya University registration
የራያ ዩኒቨርስቲ ምዝገባ ከ 09-13/08/2015
via 1.0970140000
2.0970240000
3.0970230000
N.b-በስራ ቀንና በስራ ሰዓት ብቻ

ዩንቨርሲቲው ሙሉ ዝግጅቱን ሲያጠናቅቅ የግቢ መግቢያ ቀንን በመገናኛ ብዙሃን እንደሚያሳውቅ ገልጿል።

share share

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
194 viewsedited  19:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-21 21:24:01
#የኣክሱም ዩኒቨርሲቲ በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የቆየውን የመማር ማስተማር ሂደት ለማስቀጠል በዝግጅት ላይ እንደሆነ ገልጿል።

በመሆኑም በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ #የማይገኙ ሁሉም የዲግሪ (መደበኛ፣ ኤክስቴንሽን፣ ክረምት) እንዲሁም የማስተርስ (መደበኛ፣ ኤክስቴንሽን ፣ ክረምት) ተማሪዎች ከዚህ በታች ባለው ሊንክ እንዲመዘገቡ ጥሪ ቀርቧል።

ሊንክ ፦ http://196.190.28.50

ምዝገባው የሚያበቃበት ቀን ሚያዚያ 18 ቀን 2015 ዓ/ም መሆኑን ተቋሙ አሳውቋል።

ለበለጠ መረጃ ደግሞ ዘውትር በየስራ ሰአት በሚከተሉት ቁጥሮች መወደወል ይቻላል ፦ 0914485592 / 0921990158

ከኣክሱም ዩኒቨርሲቲ በተጨማሪ #የራያ_ዩኒቨርሲቲም በጦርነት የተቋረጠውን መደበኛ ትምህርት ለማስቀጠል እየሰራ ይገኛል።

በዚህም ከ2ኛ እስከ 5ኛ ዓመት በራያ ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ትምህርት ሲከታተሉ የነበሩና ወደ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው የመማር እድል ያላገኙ ተማሪዎች ከ09/08/2015 ዓ/ም እስከ 13/08/2015 ዓ/ም ባሉ የስራ ቀናት እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል።

ተማሪዎች የሚመዘገቡት ለዩኒቨርስቲው ረጅስትራር እየደሉ ሲሆን የስልክ ቁጥሮቹ 0970140000፣ 0970240000 ፣ 0970230000 ናቸው። ተማሪዎች ዘውትር በስራ ሰዓት ብቻ እንዲደውሉ ጥሪ ቀርቧል።

share share

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
241 views18:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-17 17:35:28
ማስታወቂያ

የተባበሩት ኤምሬትስ የሰጠውን ስኮላርሽፕ እየተጠባበቃችሁ ላላችሁ ተማሪዎች ሁሉ
የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መንግስት በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ጥሩ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች ነፃ የትምህርት ዕድል ለመስጠት በፈቀደው መሰረት ቀደም ሲል በተማሪዎች ቃል የተገባላችሁ ተማሪዎችና በዕድሉ ለመጠቀም ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎች Application Form link:
http://survey.ethernet.edu.et/index.php/518562?lang=en --
በመግባት ከዛሬ 09/08/15 ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 5 ቀናት ከላይ በተቀመጠው ሊንክ በመግባት፡-
1. የ12ኛ ክፍል የማትሪክ ውጤት ኮፒ (Grade 12 Result) copy
2. ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ኮፒ (Grade 9-12 transcript) copy
3. CV/ Curriculum Vitae copy
4. የልደት የምስክር ወረቀት ኮፒ (Birth Certificate) copy እና ሌሎች በሊንኩ የተጠቀሱ መረጃዎችን እንድትሞሉ እናሳስባለን ።
መረጃዎች ተጣርተው ለፈተና የሚቀረቡ ተማሪዎችን ስም ዝርዝር በቀጣይ በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የምናሳውቅ መሆናችንን እንገልጻለን።

share share

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
767 viewsedited  14:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-16 18:14:11
2.3 ሚሊዮን የሚጠጉ ህጻናት በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል አሁንም ከትምህርት ገበታ ውጪ እንደሆኑ "ሴቭ ዘ ችልድረን" የተባለው ዓለም አቀፍ ግብረ ሰናይ ተቋም ገለጸ፡፡

በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍሎች የመልሶ ግንባታ ሥራዎች ባለመጀመራቸው ምክንያት 2.3 ሚሊዮን ገደማ የሚሆኑ ተማሪዎች አሁንም ከትምህርት ገበታ ውጭ መሆናቸውን ድርጅቱ ገልጿል፡፡

የመማሪያ ክፍሎች እንደገና ተከፍተው ተማሪዎችን ያስተናግዱ ዘንድ አስቸኳይ የገንዘብ ድጋፍ ያስፈልጋል ብሏል ተቋሙ።

በመላ ሀገሪቱ ከ 3.5 ሚሊዮን በላይ ህጻናት (ከ16 ህጻናት አንድ) ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን ድርጅቱ አመልክቷል።

ከትምህርት ገበታ ውጪ የሆኑት ህጻናቱ፤ ለጉልበት ብዝበዛ፣ ለጾታዊ ጥቃት እና ላልተፈለገ ጋብቻ ተጋላጭ እንደሚሆኑ ድርጅቱ ስጋቱን ገልጿል።

በጦርነቱ ምክንያት በትግራይ፣ አማራ እና አፋር ክልሎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ከፍተኛ ውድመት አስተናግደዋል።

በትግራይ ክልል 85 በመቶ የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የተጎዱ ሲሆኑ የመንግስት ትምህርት ቤቶች አሁንም ዝግ መሆናቸውን የድርጅቱ መረጃ ያሳያል።

22, ሺህ 500 መምህራን ከሁለት ዓመት በላይ ደመወዝ ሳይከፈላቸው እንደቆዩም ድርጅቱ አስታውሷል።

ምንጭ፦ Save the Children
762 views15:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 23:25:35
በሰሜኑ ጦርነት ጉዳት የደረሰባቸው የትምህርት ተቋማትን ዳግም ሥራ ለማስጀመር ሁሉም አካላት ድጋፍ እንዲያደርጉና እንዲተባበሩ የዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዝዳንቶች ጥሪ አቀረቡ።

በትግራይ ክልል ሥራ ያቆሙ ከቅድመ መደበኛ እስከ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ሥራ ለማስጀመር እንቅስቃሴ ተጀምሯል።

በዚህም መቐለ፣ አክሱም፣ አዲግራት እና ራያ ዩኒቨርሲቲዎችን ዳግም ሥራ ለማስጀመር እንቅስቃሴ መጀመሩን ኢዜአ ያነጋገራቸው የዩኒቨርሲቲዎች የሥራ ኃላፊዎች ገልጸዋል።

ተቋማቱን ሥራ ለማስጀመር ከትምህርት ሚኒስቴር ፈቃድ በተጨማሪ ለመማር ማስተማር አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችን ለማሟላት በጀት ሊመደብ እንደሚገባ ጠቁመዋል።

በመሆኑም ሁሉም አካላት ድጋፍ እንዲያደርጉና እንዲተባበሩ የዩኒቨርሲቲዎቹ ከፍተኛ አመራሮቹ ጥሪ አቅርበዋል።

share share

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
544 viewsedited  20:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-07 19:16:14 በትግራይ ክልል የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎችንና  ትምህርት ቤቶች ትምህርት  ለማስጀመር ሁሉን አቀፍ ዝግጅት እየተደረገ ነው-
.............................................

መጋቢት 29/2015ዓም.(የትምህርት ሚኒስቴር)፦ በትግራይ ክልል የሚገኙ አራት ዩኒቨርሲቲዎችን እና አጠቃላይ መደበኛ ትምህርት ለማስጀመር የስርዓተ ትምህርትና የመምህራን ዝግጅት እየተደረገ ነው።

የትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች፣ የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዝዳንቶችና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች በክልሉ ትምህርት ማስጀመር የሚያስችል ውይይት አድርገዋል።

መንግስትና ህወሃት በፕሪቶሪያ የደረሱትን የሰላም ስምምነት ተከትሎ በትግራይ ክልል ሰብዓዊ ድጋፍ ከማቅረብ ጀምሮ የክልሉን ህዝብ በዘላቂነት ማቋቋም የሚያስችሉ የመልሶ ግንባታና መሰረታዊ አገልግሎቶች እየተሰጡ ነው።

መንግስት በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም፣ የታጠቁ ኃይሎች ትጥቅ ፈትተው ወደ መደበኛ ህይወት እንዲመለሱ፣ መደበኛ የትራንስፖርት አገልግሎት እንዲሰጥ፣ እንዲሁም ትምህርት እንዲጀመር የሰላም ስምምነቱን እየተገበረ ነው።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ በውይይቱ ላይ እንዳሉት፣ በግጭቱ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን የዩኒቨርሲቲዎችና አጠቃላይ መደበኛ ትምህርት ለማስጀመር ጥረት እየተደረገ ነው።

በዚህም የትምህርት ተቋማት የደረሰባቸውን የጉዳት መጠን በማጥናት ትምህርት ለመጀመር የሚያስፈልጉ ጉዳዮችን ለይተን ቅድመ ዝግጅት ጀምረናል ብለዋል።

share share

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
166 viewsedited  16:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ