Get Mystery Box with random crypto!

Ethio University

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiouniversty1 — Ethio University E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiouniversty1 — Ethio University
የሰርጥ አድራሻ: @ethiouniversty1
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.85K
የሰርጥ መግለጫ

ለማንኛውም አይነት የማስታወቂያ ስራ እና ክሮስ(Cross)
💰💰 @Cozboy0 💰💰
ያናግሩን🎫🎟🎪🎪🎪🎪

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-03-09 23:55:59 የሬሚዳል ፕሮግራምን ለመከታተል የመመዝገቢያ ነጥብ በመንግስት እና በግል ዩኒቨርሲቲዎች ይለያያል?


ትምህርት ሚኒስቴር ከ50 በመቶ በታች ያመጡ የ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የሬሚዳል ፕሮግራምን በተለያዩ አማራጮች እንዲከታተሉ የመቁረጫ ነጥብ ይፋ ማድረጉ አይዘነጋም።

የመቁረጫ ነጥቡ በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 30% ከመቶ እና ከዚያ በላይ ማለትም (210 ከ 700፣  180 ከ 600 እና 150 ከ 500) መሆኑን ማሳወቁም የሚታወስ ነው።

በዚህ የሬሚዳል መቁረጫ ነጥብ መሰረት ባደረግነው ምልከታ ከተቀመጠው ነጥብ #በታች ያመጡ ተማሪዎችን የሚመዘግቡ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መሆራቸውን አይተናል።
ምዝገባውን እያከናወነ ላለው ዩኒቨርሲቲ እና ኮሎጁ ትምህርት ሚኒስቴር ካስቀመጠው ነጥብ በታች ያመጡ ተማሪዎችን ለምን መዘገባችሁ? በሚል ላቀረብንላቸው ጥያቄ መንግሥት ይፋ ያደረገው ለመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች እንጂ ለግል ተቋማት አይደለም ሲሉ ምላሽ ሰጥተውናል።

አል ዓይን ይህን ጥያቄ ይዞ ትምህርት ሚኒስቴርን የጠየቀ ሲሆን የሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙንኬሽን ሀላፊ ወይዘሮ አመለወርቅ እዝቅኤል፥ "ለሬሚዳል ፕሮግራምም ይሁን ከ50 በመቶ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች መመዝገቢያ ነጥብ ለመንግሥትም ይሁን ለግል ዩኒቨርሲቲ ተመሳሳይ ነው" ሲሉ ተናግረዋል ።

ከዚህ በፊት የነበረው ለግል እና ለመንግሥት ዩኒቨርስቲዎች የተማሪዎች መመዝገቢያ ነጥብ ይለያይ ነበር ያሉት ሀላፊዋ፥ ከ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና በኋላ ተመሳሳይ እንዲሆን መወሰኑን አክለዋል።
በዚህም መሰረት ትምህርት ሚኒስቴር ካስቀመጠው የሬሚዳል ፕሮግራም መመዝገቢያ ነጥብ ውጪ የሚመዘግቡ ዩኒቨርስቲዎች እና ኮሌጆች ህግ እየጣሱ መሆኑንና እርምጃም እንደሚወሰድባቸው ነው ያብራሩት።


ምንጭ፡አልዓይን

ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
120 viewsedited  20:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 16:51:17
ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ የሪሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ በአካል በመገኘት መጋቢት 8 እና 9 /2015ዓ.ም. እንድትመዝገቡ እንገልፃለን።

፨ምዝገባ የምታካሂዱባቸው ግቢዎች

1ኛ. በማህበራዊ ሳይንስ (Social Science) የትምህርት መስክ ለተመደባችሁ ተማሪዎች በሚዛን አማን ከተማ በሚገኘው ዋናው ግቢ ፣

2ኛ. በተፈጥሮ ሳይንስ (Natural Science) ትምህርት መስክ ለተመደባችሁ ተማሪዎች ደግሞ ቴፒ ከተማ በሚገኘው ቴፒ ግቢ

፨ለምዝገባ የሚያስፈልጉ የትምህርት ማስረጃዎች እና የግል መገልገያ ቁሳቁሶች

1ኛ. የ10ኛ እና 12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ውጤት እንዲሁም ከ9ኛ --12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ኦሪጅናልና ሁለት ኮፒ ፣

2ኛ. አምስት የቅርብ ጊዜ ሦስት በአራት (3*4) ጉርድ ፎቶ ፣

3ኛ. ብርድልብስ፣አንሶላና የትራስ ጨርቅ መያዝ እንደሚጠበቅባችሁ እናሳውቃለን።

ሚዛን-ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር ዳይሬክቶሬት

ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
524 viewsedited  13:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 09:34:58
#BoranaUniversity

በ2015 ዓ.ም በቦረና ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የአቅም ማሻሻያ ሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ምዝገባ #መጋቢት_11 እና 12/2015 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ዝርዝር መረጃዎችን ከፎቶ ላይ ይመልከቱ

ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
470 viewsedited  06:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 21:35:57
#DillaUniversity

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ለአቅም ማሻሻያ ሪሚዲያል የትምህርት ፕሮግራም በተቋሙ ለተመደቡ ተማሪዎች በቅርቡ ጥሪ እንደሚያደርግ ግልጿል፡፡

ተቋሙ እያደረገ ያለውን ዝግጅት በቅርቡ እንዳጠናቀቀ በይፋ በመገናኛ ብዙሃን እና በማህበራዊ የሚዲያ ገጾቹ እንዲሁም በዩኒቨርሲቲው ድረ ገጽ www.du.edu.et ጥሪ የሚያደርግ መሆኑን አመልክቷል፡፡

ጥሪ እስከሚደረግ ድረስ በተቋሙ የተመደባችሁ ተማሪዎች በትዕግስት እንድትጠብቁ ዩኒቨርሲቲው ጠይቋል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
540 viewsedited  18:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 18:46:13
የተወለዱበትን ወር በመንካት ኮከቦን(Zodiac), ባህሪዎን ይመልከቱ
531 views15:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 18:29:19
በ2015 ሠመራ ዩኒቨርሲቲ የ"Remedial" ፕሮግራም ለመከታተል የተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ

በ2015 የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ለመከታተል ወደ ሠመራ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቀን ከመጋቢት 4-5/2015 ሲሆን ምዝገባ የሚካሄድበት ቀን ከመጋቢት 7-8/2015 እንዲሁም ትምህርት የሚጀመርበት ቀን መጋቢት 11/2015 መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሱት ቀናት ተገኝታችሁ እንዲትመዘገቡ እየገለፅን በምዝገባ ወቅት:-

1. የ8ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሠርቲፊኬት ዋናውንና ፎቶ ኮፒ
2. የ10ኛ እና የ12ኛ ክፍል ሠርቲፊኬት ዋናውንና ፎቶ ኮፒ
3. ከ9-12 ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውንና ፎቶ ኮፒ
4. ስምንት 3/4 የሆነ ጉርድ ፎቶ ግራፍ
5. የግል መገልገያ ቁሳቁሶች ማለትም፡- አንሶላ፤የትራስ ልብስ፣የስፖርት ትጥቅ አሟልታችሁ እንዲትገኙ እናሳውቃለን።

ማሳሰቢያ፡-
ከተጠቀሱት ቀናት ቀድሞም ሆነ ዘግይቶ የሚመጣን ተማሪ ዩኒቨርሲቲው የማያስተናግድ መሆኑን፣ ለተጨማሪ መረጃ በዩኒቨርሲቲው ማህበራዊ ድህረ-ገፅ(www.su.edu.et የምናሳውቅ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

የሠመራ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት

ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
497 viewsedited  15:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 18:28:18
#UniversityofGonder

ጎንደር ዩኒቨርስቲ ለተመደባችሁ አዲስ ተማሪዎች እና አቅም ማሻሻያ ተማሪዎች በሙሉ ወደ ግቢ መግቢያ ቀን መጋቢት11 እና 12 መሆኑን እናሳውቃለን፡

1.የአቅም ማሻሻያ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፋሲል ግቢ

2.የተፈትሮ ሳይንስ መደበኛ ተማሪዎች ቴድሮስ ግቢ

3.የማህበራዊ ሳይንስ ሁሉም ማራኪ ግቢ የተመደባችሁ መሆኑን እንገልጻለን፡፡መረጃ ስትፈልጉ የህብረቱን ቴሌግራም ቻናል በመቀላቀል ፤በቀጥታ በመደወል እና በቅርቡ የምትገኙ ቢሮ ድረስ በአካል በመምጣት መጠየቅ የምችሉ መሆኑን እንገልጻለን ፡፡

ጥያቄ ና አስተያየት ለመስጠት

ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
473 viewsedited  15:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 18:26:58 በአሁኑ ሰዓት English language በጣም አስፈላጊ ቋንቋ ነው ግን ሁሉም ሰው በብዛት አቀላጥፎ መፃፍ እና መናገር አይችልም
እኛ መፍትሔ ይዘን መተናል አሁኑኑ የኛን channel join በማለት
English grammar
spoken English
and other more more
እውነተኛ ለእንግሊዘኛ ቋንቋ ብቻ የተቋቋመ channel ነው

Join
@ethioenglish1
@ethioenglish1
@ethioenglish1
459 views15:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 13:08:40
#አምቦዩኒቨርሲቲ

አምቦ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም የተመደቡ የሪሜዲያል (የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም) ተማሪዎችን የሚቀበልበት የመግቢያ ቀን መጋቢት 07 እና 08 2015 ዓ.ም በመሆኑ በተጠቀሰው ቀናት ብቻ በማህበራዊ ሳይንስ መስክ የተመደባችሁ በዋና ካምፓስ ፤ በተፈጥሮ ሳይንስ የተመደባችሁ አምቦ ከተማ ሃጫሉ ሁንደሳ ካምፓስ በአካል በመገኘት እንድትመዘገቡ ጥሪ እያደረገ ከተጠቀሰው ቀን ቀድሞ ሆነ ዘግይቶ የሚመጣን ተማሪ ዩኒቨረሲቲው የማያስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

ማሳሰቢያ፡-
ሁሉም ተማሪዎች ለምዝገባ ስትመጡ ልትይዟቸው የሚገቡ፡-
- ከ8 –12ኛ ክፍል ያሉ የትምህርት ማስረጃ ዋናውና ኮፒ፡
- የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሳርትፍኬት ዋናውና ኮፒ፡
- 3x4 ጉርድ ፎቶግራፍ ብዛት 8:
- አንሶላ፡ ብርድልብስ፡ ትራስልብስ እና የስፖርት ትጥቅ::

ሬጅስትራር ዳይሬክቶሬት

ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
540 viewsedited  10:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 08:43:22
#AmboUniversity #Fake

አምቦ ዩኒቨርስቲ ለ Remedial ተማሪዎችን ጠርቷል እየተባለ ይሄ መረጃ እየተሰራጨ ይገኛል። ነገር ግን Ambo ዩኒቨርስቲ በ Official የሶሻል ሚዲያ ገፃቸው ምንም አይነት ማስታወቂያ አላወጣም።

ዩኒቨርስቲው ማስታወቂያ ሳያወጣ ወሬውን የሰሙ ሰዎች ፅፈውት ይሆናል። ዛሬ ትክክለኛውን ማስታወቂያ እንጠብቅ።

ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
560 viewsedited  05:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ