Get Mystery Box with random crypto!

Ethio University

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiouniversty1 — Ethio University E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiouniversty1 — Ethio University
የሰርጥ አድራሻ: @ethiouniversty1
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.85K
የሰርጥ መግለጫ

ለማንኛውም አይነት የማስታወቂያ ስራ እና ክሮስ(Cross)
💰💰 @Cozboy0 💰💰
ያናግሩን🎫🎟🎪🎪🎪🎪

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2023-03-04 23:23:36
#በሪሜዲያል_ፕሮግራም ወደ ወለጋ ዩንቨርሲቲ ለተመደባችሁ ተማሪዎች

በወለጋ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ #የሪሜዲያል (#Remedial) #ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ቀን መጋቢት 7 እና 8/ 2015 ዓ.ም መሆኑን ዩንቨርሲቲው አሳውቋል።


ምደባ
1. በተፈጥሮ ሳይንስ የተመደባቡ ሁሉም ተማሪዎች ነቀምቴ ካምፓስ ያመለክታሉ።
2. በማህበራዊ ሳይንስ ሰማችሁ በፊደል ተራ (እንግሊዝኛ) #ከM_Z የሚጀምር ተማሪዎች ነቀምቴ ካምፓስ ታመለክታላችሁ።
3. በማህበራዊ ሳይንስ ሰማችሁ በፊደል ተራ (እንግሊዝኛ) #ከA_L የሚጀምር ተማሪዎች ጊምቢ ካምፓስ ታመለክታላችሁ።

ምንጭ፡ የዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራር


ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
77 viewsedited  20:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 23:04:45 ያለ ፀፀት ነገን ለመኖር ዛሬን በቁም ነገር አሳልፍ

" የሚስጢር ሙዳይ ሁን እንጂ ፤ የእሳት ማንደጃ ወናፍ አትሁን

ሰዎች ሊሰሙህ በሚችሉበት ችሎታቸው ና ፍላጎታቸው መጠን ብቻ ተናገር ፤ ቁጥብ እንጂ ዝርው አትሁን

ለ እውቀት ትጋ ፤ በከፊል በተረዳኸው ነገር ራስህን እንደ አዋቂ አትቁጠር ፤ በከፊል ከማወቅ አለማወቅ ይሻላል።

ስራ ስትሰራ ደግሞ ነገ ትቼው ለምሞተው ወይ ብሰራ የሚጠቀመው ሌላ ነው በሚል ተስፋ ቢስ ሁነህ ሳይሆን ፤ ዘላለም እንደምትኖር ያህል ሁነህ በመትጋት ነው ፤ ትጋት ጥሩ ነው ፤ ችኮላ ግን ውጤት አያመጣም ፤ በችኮላ መስራት ና በፍጥነት መስራት የተለያዩ ናቸው።

ርኩሰት የ ዕውቀት ና የስልጣኔ መገለጫ አይደለምና ፤ ማንነትን ና ሰብአዊ ክብርን ከሚያጎድፉ ተግባራት መታቀብን ገንዘብ እናድርግ

እናም በየእለቱ በኑሮህ ጠንቃቃ ሁን ያለ ፀፀት ነገን ለመኖር ዛሬን በቁም ነገር አሳልፍ። ውሳኔዎችህ ትክክለኛ መሆናቸውን መርምር ፤ ልክ እንደገና ህይወትን የመኖር ዕድል ቢኖርህ ወይም እንደገና የመወለድ ዕድል ቢኖርህ ፤ ደግመህ የምትኖረውን ና ለማከናወን የምትመርጠውን አይነት ህይወት ለመኖር ሞክር "

ከ ዶክተር አለማየሁ ዋሴ እሸቴ ፤ ዝጎራ መፅሐፍ የተወሰደ።

Join us share

@ethiokumnger @ethiokumnger
94 views20:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 20:39:27 EYUEAL እባላለሁ።

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ አመት ተማሪ ነኝ እናም ባንድ ወቅት የገጠመኝን እጅግ ትምህርት የቀሰምኩበትን ነገር እነሆ እላለሁ።ዶርሜ 3ኛ ህንጻ ላይ ነው።አንድ ምሽት ላይ በሶ በጠበጥኩና ጠጣሁ ከዚያ የበጠበጥኩበትን እቃ አጣጥቤ በመስኮት ልደፋ ወደ መስኮቱ ተጠጋሁና ስደፋው ለካ ከታች ዘበኛው እያለፈ ነበር።እናም በራሱ ላይ ለቀኩበት ።በርግጥ በጣም ደንግጫለሁ።ዘበኛውም የዋዛ አልነበረም እታች ሆኖ እየተሳደበም እየተናደደም ዶርሜን በደምብ አየውና ለመምጣት ጉዞ ጀመረ።እኔም ቶሎ ወደ አልጋየ ሄድኩና ተኛሁ ።የኔ ጓደኛ የሆነው አንዱ ግን እያነበበ ነበር።ሌሎቻችን ግን ተኝተናል(እኔ ዘበኛው መምጣቱን ሳውቅ ነው የተኛሁት)።የሚያነበው ልጅ ግን ምን ሰርቸ እንደተኛሁ የሚያውቀውም ሆነ የሚጠረጥረው ነገር የለም።እናም ከደቂቃወች በኋላ ዘበኛ ሆየ ከች አለና ቆረቆረ።ሲያነብ የነበረው ጓደኛየ ማነው በማለት ከፈተለት።እኔም ብርድ ልብሴን ለብሸ እያጮለኩ በማየት ላይ ሳለሁ ልጁ እንደከፈተለት የዘበኛው የመጀመሪያ ስራው በጥፊ መምታት ሆኖ አገኘሁት።ልጁም በማያውቀው ነገር መመታቱ ግራ አጋብቶት ምንድን ነው በማለት ተፋጠጡ እኔ ግን ይህን ሁሉ በLIVE እከታተል ነበር።በመጨረሻም IDውን ቀምቶት ሄደ እና ጧት እኛ ጓደኞቹ በግድ ለምነን እንዲሰጠው አደረግን።አይጥ ባጠፋ ዳዋ ተመታ ይሉሃል እንግድህ ይህ አይደል።ያገኘሁት ትምህርት ደግሞ ይህ ነው“ለካ ንጹሃን ወገኖች የሚሰቃዩት፤የሚቀጡት፤የሚያለቅሱት፤የሚያዝኑትም በተንኮለኞች ሴራ እና ተግባር መሆኑ የዛኔ ግልጥ ብሎ ታየኝ።ልቤ በጣም ቆሰለ የጥፋተኝነት ስሜት አንገበገበኝ ፤ያደረኩት ነገር ትውስ እያለኝ አመመኝ።ከዚያም ሁሉንም ነገር ነግሬ ይቅርታ እንድያደርግልኝ ተማጸንኩት እርሱም ይቅርታ ለማድረግ ጥቂት ጊዜያትን ወሰደበትና አደረገልኝ።እሰይ ተመስገን የዚያን ቀን የተሰማኝን ደስታ ቃላት አይገልጹልኝም።

አመሰግናለሁ ሰላማችሁ ይብዛልኝ።

ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
275 viewsedited  17:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 20:37:29
#OdabultumUniversity

ማስታወቂያ: ለአቅም ማሻሻያ (Remedial Program) ወደ ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ተማሪዎች የመመዝገቢያ ቀን መጋቢት 04-05/2015 መሆኑን ዩኒቨርስቲው አሳውቋል።

Share share
ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
276 viewsedited  17:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 20:34:57
#ArbaminchUniversity

በ2014 የትምህርት ዘመን ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ወስደው ለአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም (Remedial Program) ትምህርት አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቅበላ ቀን የካቲት 29/2015 ዓ/ም፣ የምዝገባ ቀን የካቲት 30 እና መጋቢት 01 ቀን 2015 ዓ.ም፣ ትምህርት የሚጀመርበት ቀን መጋቢት 04 ቀን 2015 ዓ.ም ይሆናል፡፡ ስለሆነም የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም (Remedial Program) ትምህርት አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች በተጠቀሰው ቀን ወደዩኒቨርሲቲው በምትመጡበት ጊዜ፡-

- የ8ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ኦርጂናልና ሁለት የማይመለስ ኮፒ፣
- ከ9ኛ-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ኦርጂናልና ሁለት የማይመለስ ኮፒ፣
- የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት ኦርጂናልና ሁለት የማይመለስ ኮፒ፣
- የፓስፖርት መጠን (Passport Size) የሆነ አራት ጉርድ ፎቶ፣
- አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ የትራስ ጨርቅ እና የስፖርት ትጥቅ

- ዓባያ ካምፓስ የተመደባችሁ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በአርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው የተፈጥሮና ቀመር ሳይንስ ኮሌጅ (ዓባያ ግቢ)፣
- ጫሞ ካምፓስ የተመደባችሁ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በአርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው ጫሞ ካምፓስ፣
- ሳውላ ካምፓስ የተመደባችሁ የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች በጎፋ ዞን ሳውላ ከተማ በሚገኘው ሳውላ ካምፓስ በአካል ቀርባችሁ እንድትመዘገቡ እና የአቅም ማሻሻያ ትምህርት እንድትጀምሩ እናሳስባለን።

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሬጂስትራርና አልሙናይ ዳይሬክቶሬት።


Share share
ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
263 viewsedited  17:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 15:21:13 በአሁኑ ሰዓት English language በጣም አስፈላጊ ቋንቋ ነው ግን ሁሉም ሰው በብዛት አቀላጥፎ መፃፍ እና መናገር አይችልም
እኛ መፍትሔ ይዘን መተናል አሁኑኑ የኛን channel join በማለት
English grammar
spoken English
and other more more
እውነተኛ ለእንግሊዘኛ ቋንቋ ብቻ የተቋቋመ channel ነው

Join
@ethioenglish1
@ethioenglish1
@ethioenglish1
409 views12:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 14:57:12 #JIMMA_UNIVERSITY

አድራሻ

ጅማ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ዋና ከተማ ከሆነችዉ ከአድስ አበባ ደቡብ ምዕራብ በኩል የሚትገኝ ሲሆን ከአድስ አበባ እስከ ጅማ 390 km አከባቢ ነዉ።


የአየር ሁኔታ

ሞቃታማ ፥ ከአዳማ እና ከመሰል ሞቃት ሃገሮች ለሚመጡ ተማሪዎች ሙቀቱ ምንም ዓይነት ተጽእኖ የለውም እንዲያውም ሊበርዳቸው ይችላል፤ በግልባጩ ደግሞ ከብርዳማ አከባቢ ለሚመጡ ተማሪዎች የሙቀቱ መጠን ከፍ ያለ ይሆንባቸዋል ።
ለማንኛውም ቀለል ያሉ ልብሶችን ይዛቹህ ብትሄዱ መልካም ነው።


ስለ ዮኒቨርስቲው

ድሮም ጀምሮ የፍቅር ከተማ ተብሎ በሚጠራዉ በጅማ ከተማ የሚገኝ አንጋፋና ለኑሮም ሆነ ለትምህርት ከየትኛዉም ዩኒቨርሲቲ የተሻለ ነዉ ብለን የሚናስበዉ ዩኒቨርሲቲ ነዉ። ጅማ ታርካዊና አንጋፋ በሆኑ በንጉስ አባጅፋር ታርክ የታወቀች ከተማ ስትሆን ዩኒቨርሲቲዉ ለከተማ ብዙም ሳይርቅ በከተማ ዉስጥ ነዉ ለማለት በሚያስችል ሁኔታ ይገኛል። ሌላዉ እና በጣም ደስ የሚል ታርካዊ ቦታ ቢኖር ንጉስ አባጅፋር ቤተመንግስት የሚገኘዉ ከዋናዉ ግቢ ብዙም ሳይርቅ መገኘቱ ነዉ። ለጉብኝት በፈለጋችሁ ጊዜ ሁለ መዝናናት የሚያስችል ቦታ ነዉ። በጅማ ዩኒቨርሲቲ በጣም የሚያማምሩ ህንፃዎች ከመኖራቸዉ ባሻገር ለመማርም በጣም ምቹ የሆኑ ህንፃዎች ናቸዉ። ጅማ ዩኒቨርሲቲ በጣም በፍጥነት እያደገች ትገኛለች።


የካንፓሶች ብዛት




በጅማ ዩኒቨርሲቲ አራት Campus ያለ ስሆን ከቅርብ ጊዜ በኋላ አንድ አድስ campus ስራ ይጀምራል ተብሎ ይገመታል። የአራቱ campuses ስማቸዉም እንደሚከተለዉ ነዉ፦

# ዋና ጊቢ ( Main campus)..
በዋና ግቢ የሚገኙ ኮሌጆች ፦
# ጤና እንስቲትዩት
# ህግና አስተዳደር ኮሌጅ
# የተፈጥሮ ሳይንስ ኮሌጅ
#ማህበራዊ ሳይንስ ኮሌጅ እና
# ስነ ባህሪ ኮሌጅ ናቸዉ።

ቤኮ ኮሌጅ ( College of business& economics) ከዋናዉ ግቢ ትንሽ የሚርቅና በመካከላቸዉ ትልቅ መንገድ ያለ ስሆን ዋናዉንና ቤኮ ግቢዉን የሚያገናኝ ትልቅ ድልድይ ይገኛል። ከዚህ የተነሳ የዋና ግቢ ተማርዎችም ሆነ የቤኮ ( college of business& economics ) ተማርዎች በድልድዩ በኩል ያለምንም መንገድ ችግር ይመላለሳሉ።


# የቴክኖሎጂ ግቢ የእንጂነርግ ተማሪዎች እና የcomputer science ግቢ ሲሆን ለመማርም ለመኖርም ምቹና በጣም አስደናቂ የሆኑ ህንፃዎች ያሉበት ግቢ ስሆን በመጀመሪያ ጊዜ የህንፃዎችን አሰራር ያዬ ሰዉ እዉነትም ይህ ህንፃ የእንጂነሮች ስራ ነዉ ብሎ ከማድነቅ ወደኋላ አይልም። የቴክኖሎጂ ግቢ ከዋናዉ ግቢ የ 5 ብር መንገድ ስሆን ከጅማ ከተማ ከመርካቶ የ 3 ብር መንገድ ነዉ።


4# የግብርናና እንስሳት ህክምና ኮሌጅ ፦ የሚገኘዉ ከቴክኖሎጂ ግቢና ከዋና ግቢ መሃል ይገኛል። የግብርና እና እንስሳት ህክምና ኮሌጅ

Share share
ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
408 viewsedited  11:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 14:54:45
#Remedial #Extension #SamaraUniversity

ሠመራ ዩኒቨርስቲ በስድስት ኮሌጆች እና በአንድ ትምህርት ቤት ስር የተለያዩ የትምህርት ፕሮግራሞች በ2015 የት/መን #በኤክስቴንሽን መርህ ግብር አዲስ ተማሪዎችን ተቀብሎ በመጀመሪያ ዲግሪ በሚከተሉት የትምህርት ዘርፎች ማስተማር ይፈልጋል::

ሙሉ መረጃውን ከላይ ይመልከቱ

Special Tutorial For Remedial በ Physics እና Chemistry ጀምረናል።

ጥያቄ ና አስተያየት ለመስጠት
  @ethiouniversity1bot

            Share share
ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
366 viewsedited  11:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 14:49:30 የዩኒቨርስቲዎች ጥሪ


#ወልድያዩኒቨርሲቲ

በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የአቅም ማሻሻያ/Remedial Program/ ፕሮግራም ለመከታተል ከትምህርት ሚኒስቴር ወልድያ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ

ከየካቲት 30/2015 ዓ.ም እስከ መጋቢት 01/2015 መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሱት ቀናት በአካል ተገኝታችሁ ምዝገባ እንድታደርጉ ዩንቨርሲቲው አሳውቋል።

#ቦንጋ_ዩኒቨርሲቲ

በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በ2015ዓ.ም በአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም(Remedial Program) የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ቀን መጋቢት 01-02/2015 ዓ.ም መሆኑን ዩንቨርሲቲው አሳውቋል።

#በእንጅባራ_ዩኒቨርሲቲ

የማካካሻ ትምህርት ለመውሰድ በእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ፦

እንጅባራ የካቲት 27 እና 28/2015 ዓ.ም ያደረገው የተማሪዎች ቅበላ 50% እና ከዚያ በላይ ላመጡ በቀጥታ ወደ ዩኒቨርሲቲ ለሚገቡ ተማሪዎች ብቻ ነው።

የማካካሻ ትምህርት ለመውሰድ የተመደባችሁ ተማሪዎች በአሁኑ ጥሪ ያልተካተታችሁ መሆኑን አውቃችሁ ወደ ፊት በማስታወቂያ እስከሚገለጽ ድረስ ባላችሁበት ሆናችሁ በትዕግስት እንድትጠባበቁ ዩኒቨርሲቲው ያሳውቃል።

#ወሎ_ዩኒቨርሲቲ

በ2015 ዓ.ም ወሎ ዩኒቨርሲቲ ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) የተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ የመግቢያ ጊዜ መጋቢት 4 እና 5/2015 ዓ.ም መሆኑን ዩንቨርሲቲው አስውቋል።

#ባህርዳር_ዩኒቨርሲቲ

በ2015 ዓ/ም በባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የ‛Remedial” ፕሮግራም ለመከታተል ለተመደባችሁ ተማሪዎች በሙሉ

በ2015 ዓ/ም የአቅም ማሻሻያ (Remedial) ፕሮግራም ለመከታተል ወደ ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቀናት የካቲት 29 እና 30 ቀን 2015 ዓ/ም መሆኑን ዩንቨርሲቲው ገልጿል።

#HaramayaUniversity

በ2015 ዓ.ም በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ምዝገባ መጋቢት 08, 09 እና 10/2015 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

#DirredawaUniversity

በሬሚድያል ፕሮግራም ወደ ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባቹ የሪድሚያል ፕሮግራም ተማሪዎች የምዝገባ ቀናት መጋቢት 01-02/2015 መሆኑን ዩንቨርሲቲው አሳውቋል።


#SelaleUniversity

በሬሚድያል ፕሮግራም ሰላሌ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባቹ ተማሪዎች የሪድሚያል ፕሮግራም ምዝገባ የካቲት 29-30/2015 መሆኑን ዩንቨርሲቲው አሳውቋል።

#ጅማ_ዩኒቨርስቲ

በ2015ዓ.ም የት/ት ዘመን በጅማ ዩኒቨርስቲ ለተመደባችሁ አዲስ የተመዝገባችሁ የካቲት 29 እና 30/2015ዓ.ም እንደሚካሄድ ዩንቨርሲቲው አሳውቋል።

Share Share

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
376 viewsedited  11:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-04 13:08:52 ዩንቨርሲቲ የመጀመሪያ አመት ተማሪ ነበርኩ አና ከ freshman የማረሳው አጋጣሚ ልንገራቹ

ከዛ በፊት ማሚዎቻችን (proctors) sorry ለናተ ማንበብ የተከለከለ ነው

ዶርማችን ወደ
" የጨሠ kitchn "
የተለወጠበትን ቀን ነዉ
ዶርም ዉስጥ ሰባት ነን አና ቦይለር በሁሉም ፈቃደኘነት (ከየት እንዳመጣነዉ ባላወቅነው ድፋረት ) አስገባን አንድ ቀን ዶርም ውስጥ ማንም አልነበረም ሁሉም library ሄደው ነበር አኔ ና አንድ ጎደኛዬ ብቻ ነበር የቀረነዉ በሶ በጠበጥን ለመጠጣት ስናስብ ግን አስጠላን(በሶ አዝጎን ነበር )
ከዛም አዲስ ሀሳብ መጣልን
የ በጠበጥነውን በሶው በ boiler ማፍላት( )
Boiler ሰክተን ማፋላቱን ተያያዝነዉ ትንሽ ቆይቶ የወነ የተቃጠለ ምግብ መሽተት ጀመረ ቀጥሎም ዶርማችን በጭስ ታፍኖ ጭሡ ከዶርም አልፎ ወደውጪ መውጣት ጀመረ አኔ ና ጎደኛዬ የምንገባበት ጠፍን በቃ ተባረርን(የኛስ ይሁን የቀሩትን dorm mates ስናስብ...... ) ወዲያው ቦይለሩን ነቀልን ሁሉም ነገር ጭስ ሆነ የሁሉም ሰው ብርድልብስ ጭስ ጭስ ይላል በውሀ አቃውን ማጠብ በጨርቅ በ airfresher ጭሱን ለማስለቀቅ እየተጣጣርን አያለ አዷ ልጅ ሸቷት በሀይል በሩን በርግዳ ገብታ "ቂጣጣጣ " ብላ እየጮኸች የታል ስትል አኔና ጎደኛዬ proctor መሥለዉን ክው ብለን የደነዘዝንበትን ቀን መቼም አረሳውም

Share Share

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
441 viewsedited  10:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ