Get Mystery Box with random crypto!

Ethio University

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiouniversty1 — Ethio University E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiouniversty1 — Ethio University
የሰርጥ አድራሻ: @ethiouniversty1
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.85K
የሰርጥ መግለጫ

ለማንኛውም አይነት የማስታወቂያ ስራ እና ክሮስ(Cross)
💰💰 @Cozboy0 💰💰
ያናግሩን🎫🎟🎪🎪🎪🎪

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2023-03-14 13:02:47
#DebarkUniversity

ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም በተቋሙ ለተመደቡ የአቅም ማሻሻያ (ሪሚዲያል) ፕሮግራም ተማሪዎች የትራንስፖርት አገልግሎት አዘጋጅቷል፡፡

ዩኒቨርሲቲው የአቅም ማሻሻያ ፕሮግራም ተማሪዎች መጋቢት 05 እና 06/2015 ዓ.ም ወደ ተቋሙ እንዲገቡ ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል፡፡

በተጠቀሱት ቀናት ጎንደር ከተማ አዘዞ አይራ መገንጠያ እና መስቀል አደባባይ ላይ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ሰርቪሶች መዘጋጀታቸውን ዩኒቨርሲቲው ገልጿል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
681 viewsedited  10:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 19:16:21
#GambelaUniversity

በ2015 ዓ.ም በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ የአቅም ማሻሻያ ሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ምዝገባ #መጋቢት_8 እና 9/2015 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

፨ዝርዝር መረጃዎችን ከፎቶ ላይ ይመልከቱ።

ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
663 viewsedited  16:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 19:14:38
#ArsiUniversity

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ማለፊያ ውጤት አምጥተው በአርሲ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡ አዲስ ተማሪዎች የመግቢያ ቀን መጋቢት 14 እና 15/2015 ዓ/ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

Social ተማሪዎች በ ቦቆጂ ካምፓስ እንድሁም የ Natural ተማሪዎች በግብርና እና አከባቢ ሳይንስ ኮሌጅ ተመድቧል።

የ Remedial ተማሪዎች ምዝገባ በቅርቡ ያሳውቃል።

ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
602 viewsedited  16:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-13 08:29:00 ከ #አዲሱ_የትምህርትና_ስልጠና_ፖሊሲ የተገኘ መረጃ


➢ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (6ኛ ክፍል) ፈተና በክልል ደረጃ ተዘጋጅቶ እንዲሰጥ ይደረጋል።

➢ የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (8ኛ ክፍል) ፈተና ትምህርት ሚኒስቴር በሚያወጣው ስታንደርድ መሠረት ፈተናውን የማዘጋጀትና የማስተዳደር ሥራ በክልሎች እንዲከናወን ይደረጋል።

➢ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ አገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና በቀለም እና በሙያ ትምህርት ትኩረት መስኮች በሁለት መልክ ተዘጋጅቶ እንዲሰጥ ይደረጋል።

➢ 12ኛ ክፍል አጠናቀው ወደ ሥራው ዓለም መቀላቀል ለሚፈልጉ በ2ኛ ደረጃ መርጠው በተማሩት የሙያ ትምህርት መሠረት የብቃት ምዘና እንዲዘጋጅ ይደረጋል።

➢ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና የብቃት ምዘና በኢንዱስትሪ ውስጥ የሚሰጥ ሲሆን ኢንዱስትሪው ምዘና ሊሰጥ በማይችልበት ሁኔታ የብቃት ምዘናው የክላስተር የምዘና ማዕከላትን፣ ተንቀሳቃሽ የምዘና ማዕከላትንና ሱሙሌሽን በመጠቀም እንዲሰጥ ይደረጋል።


➢ ከአንድ ደረጃ ወደ ሌላ ደረጃ የሚደረገው ሽግግር በተቋም ውስጥ ምዘና የሚረጋገጥ ሲሆን በየትኛውም ደረጃ ወደሥራው አለም መግባት የሚፈልጉ ሠልጣኞች ብቻ አገራዊ የብቃት ምዘና የሚወስዱ ይሆናል።


ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
705 viewsedited  05:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 20:42:41
#ማስታወቂያ

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በ2015 ዓ.ም ሁለተኛ ሴሚስተር በOral and Maxillofacial Surgery ስፔሻሊቲ ስልጠና ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል።

የማመልከቻ መስፈርቶች፡
፨ከታወቀ ከፍተኛ የትምህርት ተቋም በDoctor of Dental Medicine የተመረቀ/የተመረቀች
ሁለት ዓመት የስራ ልምድ ያለው/ያላት
ስፖንሰርሽፕ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል/የምትችል
፨ኦፊሻል ትራንስክሪብት (Official Transcript) ትምህርት ከመጀመሩ በፊት ማስላክ የሚችል/የምትችል
፨ሁለት Recommendation Letter ማቅረብ የሚችል/የምትችል

የማመልከቻ ቦታ፡ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር ቢሮ ቁጥር 41
የማመልከቻ ጊዜ፡ ከመጋቢት 04-13 /2015 ዓ.ም
የመግቢያ ፈተና የሚሰጥበት ቀን፡ መጋቢት 15/2015 ዓ.ም


ሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ሬጅስትራርና አሉሚኒ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት

ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
690 viewsedited  17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 13:55:10
#መልካም ዜና

ለ #መቐለ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እና ለዩኒቨርሲቲዉ ማሕበረሰብ በሙሉ

በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የመቐለ ዩኒቨርሲቲ የመማር ማስተማር ሂደት ወደ ቀድሞ ልሕቀቱ በቅርቡ እንደሚመለስ ከዩንቨርሲቲው የተማሪዎች ህብረት ሰምተናል።

ዩንቨርሲቲው ከመንግስት አስፈላጊው በጀት ተለቆለት በቅርብ ወራት ውስጥ ትምህርት እንደሚጀምርም ለማወቅ ተችሏል።

ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
711 viewsedited  10:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-12 08:12:30
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በ2014 ዓ.ም ሀገር አቀፍ ፈተና ወስደዉ የአቅም ማሻሻያ ትመህርት ለመማር ወደ ዩኒቨርሲቲዉ የተመደቡትን ተማሪዎች ለመቀበል ዝግጅት ማጠናቀቁን ገለፀ፡፡
በ2014 ዓ.ም የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ፈተና ወስደዉ የማለፍያ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ገብተዉ የአቅም ማሻሻያ ትምህርት እንዲማሩ ትምህርት ሚኒስተር ማሳወቁ ይታወሳል፡፡

በመሆኑም መንግስት ያስቀመጠዉን አቅጣጫ መሠረት በማድረግ በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የተመደቡትን ተማሪዎች ለሁለት ተከታታይ ቀናት መጋቢት 4 እና 5 ለመቀበል ዝግጅት ማጠናቀቁን የዩኒቨርሲቲዉ ተማሪዎች አገልግሎት ጉዳይ ዳይሬክተር ፕሮፌሰር ቦሩ በደያ ገልፀዋል፡፡

እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ከሆነ የአቅም ማሻሻያ ትምህርቱን እንዲማሩ የተመደቡት ተማሪዎች ጠቅላላ ብዛታቸዉ 2700 ሲሆኑ ከነዚህም 1346 ሴት ተማሪዎች መሆናቸዉን አሳዉቀዋል፡፡

በመጨረሻም የተመደቡት ተማሪዎች ምንም ዓይነት ስጋት ሳይኖርባቸና ትምህርታቸዉን የሚከታተሉበት ሁኔታ እንደሚመቻች ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡


ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ


ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
171 viewsedited  05:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-11 16:37:12 በአሁኑ ሰዓት English language በጣም አስፈላጊ ቋንቋ ነው ግን ሁሉም ሰው በብዛት አቀላጥፎ መፃፍ እና መናገር አይችልም
እኛ መፍትሔ ይዘን መተናል አሁኑኑ የኛን channel join በማለት
English grammar
spoken English
and other more more
እውነተኛ ለእንግሊዘኛ ቋንቋ ብቻ የተቋቋመ channel ነው

Join
@ethioenglish1
@ethioenglish1
@ethioenglish1
342 views13:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 19:40:24 TENSION
ጭለላ
(ለ 1ኛ አመት ተማሪዎች ይድረስልኝ)

ግቢ ላይ ከሚያጋጥሙን ጥቂት ችግሮች ውስጥ አንዱ ከልክ ያለፈ ጭንቀት ወይም በግቢ ስሙ #Tension ብለን የምንጠራው ነገር ነው።
ይሄ ችግር ብዙውን ጊዜ በአንደኛ አመት ተማሪዎች ላይ በስፋት የሚስተዋል ቢሆንም በሁሉም ዘንድ ማለትም ተመራቂ ተማሪዎችንም ሳይቀር የሚያጦዝ ደስ የሚል ሙድ ያለው ጭለላ ነው።

እኔ ግን ጥሎብኝ የሚሰማኝ ሰው ሳገኝ ብዙ አወራለሁና ዛሬም ከሰማችሁኝ ትንሽ ስለ ግቢ Stress or Tension ባካፍላቹህ ደስ ይለኛል ፤ በተጨማሪም አዲስ ገቢ ተማሪዎች ለቴንሽን አዲስ በመሆናቸውና ከሁሉም በይበልጥ የታላላቆቻቸውን ምክር ስለሚቀበሉ ይቺን ምክር እንድታደርሱልኝ አደራ ማለት እወዳለሁ
አይይ እንግዲህ ብዙ አታቅራራ ፡ ወደ ገደለው ግባ

Tension ብዙውን ጊዜ የሚገጥመን የሆነ ክስተት አንጎላችንን ሲቦጠብጠው እንደሆነ የአንጎል ስፔሻሊስትና የሳይኮሎጂ ሊቅ ለመሆን የሚመኙት Dr abz ይገልፃሉ አስከትለውም ጭንቅላታችን በጣም በሚጨናነቅበት ጊዜ የሚገጥመን failure ነው ይላሉ ።
ስልካችንን አንዳንዴ busy ሲሆን stack እንደሚያደርገው ማለታቸው ነው።

በግቢ ተማሪዎች ሳይኮሎጂ ላይ ከፍተኛ ጥናት ያደረጉት ኢንጂነር ዱባለ እንደጠቀሱት ደግሞ " ግቢ ውስጥ ብዙውን ጊዜ ተማሪዎች በተለይም አንደኛ አመት ተማሪዎች ፈተና በሚቃረብበት ወቅት የሚገጥማቸው ከፍተኛ መጨናነቅ መንስኤው አስቀድመው ተገቢውን ዝግጅት አለማድረጋቸው ነው" በማለት ይጠቅሳሉ ።

እኔም የኢንጂነሩን ጥናት ዋቢ በማድረግ የተወሰኑ ገጠመኞቼን ላካፍላቹህ

*አንደኛ አመት ተማሪ እያለሁ Drawing ኮርስ አጨልሎኝ አድሮ ጥዋት ከፈተና በፊት ካፌ ላይ የተፎገርኩት ፉገራ እስካሁን ሳስታውሰው ያስቀኛል ፤ (አሁን ግን Drawing የለም )

ምን መሰላቹህ pictorial drawing የሚሉት ነገር አልገባህ ብሎኝ እንቅልፍ ባይኔ ሳይዞር ወረቀት ላይ አፍጥጬ ስላደርኩ መሰለኝ ከምላቹህ በላይ ጭልል ብዬ ነበር
እናም ምንም ቁምነገር ሳልይዝ ነጋና ቁርስ መብያ ሰዓት ደርሶ ሁሌም አብሮኝ የሚበላው ጓደኛዬ ጋር በመሆን ወደ ካፌ ሄድን ፡ ስንደርስም ያን ጨርቅ የመሰለ ፊቴን ታጥቤ ወደ ሆድ ሸንቁሬው አዝግ ሰልፍ አመራን ፥ የማይደርስ የለምና ተራችን ደርሶ ባንደኛው እጃችን ትሪና ኩባያ ይዘን በሌላኛው ደግሞ binder( for drawing exam) ይዘን ወደ ጨላፊዎች ተጠጋን ጨላፊዋም ትሪህን አስጠጋ ስትለኝ ትሪዬን' ሰጠኋት ፨ የሚገርማቹህ ትሪ ብዬ ፍርፍሩን የተቀበልኩት በ binderu ነበር እሷም አውቃ ይሁን እንደኔ ጨልላ ባላቅም ጭልፋ ሙሉ ፍርፍር በትሪዬ' ሞላችልኝ kikikikikiki
በBindeሬ ፍርፍር ማስደረጌን ያስተዋልኩት አብሮኝ የነበረው ጓደኛዬ በሳቅ ፍርፍር ብሎ ፍርፍሩ ሲደፋበት ነበር ።
ብዙ ተማሪ እየሳቀብኝ እንደሆነ ሳይ ደግሞ ይብስኑ የምገባበት ጠፋኝ ( ሳሳዝን)
እንዴትም ብዬ ከዛ ደባሪ ሙድ በመውጣት ፍርፍሬን ወደ ትሪዬ ገልብጬ ወደ መቀመጫዬ በመሄድ በእልህ ምግቡን ስበላው እሱም ለካ ቂም ይዞብኝ ነበር አነቀኝ ፡ ባክህ አልሰማህም በሻይ ድራሽህን ነው ማጠፋው ብዬ ወደ ኩባያዬ እጄን ስሰድ አለወትሮዋ ኩባያዋ ቀለለችኝ ምንሼ ነው ብዬ ወደ ኩባያዬ ሾፍ ሳደርግ ሻይም ሳላስቀዳ ነበር የተቀመጥኩት ( አይ drawing)
ድጋሚ ይስቁብኛል ብዬ ባልፈራ ኖሮ ተነስቼ ሻይ አስቀዳ ነበር ግን ምንም ማድረግ አይቻልም ከጓደኛዬ እየተዋስኩ ታሪካዊ ቁርሴን በላሁ ።

ከካፌው ወጣ ብለን እጃችንን በመታጠብ ላይ ሳለን ሳላስበው ጧ ብዬ ሳቅኩ አብሮኝ የነበረው ጓደኛዬ በመገረም " ይሄ ልጅ ዛሬ ምን ነካው" ሲል ባሰብኝ ....
እንዴት ብዬ ልንገረው ገና ት ብዬ ስጀምር ሳቄ ይቀድመኛል እንዴትም ብዬ በምልክት ወደ ትሪው ጠቆምኩት ፥ ደንግጦ ትሪውን ይዞ ወደ ካፌ ሲሮጥ ህዝቤ ፈተናዋን ረስታ ሳቀችበት
ብድር በምድር አሉ ፥ ለካስ freind ከኔው ብሳ ትሪዋን ይዛ ወደ ፈተና ልትገባ ነበር

የሚገርም ግጥምጥሞሽ እያልኩ ፏ ብልጭ ብዬ ተፈተንኩ እላቹሃልው ።
ተረቴን መልሱ አፌን በዳቦ አብሱ*


Final exam ሲቃረብ እንደዚህ አይነት የካፌ comedy መመልከት የተለመደ ነው ምክንያቱ ደግሞ ቅድም ኢንጅነሩ የጠቀሱት ቅድሚያ አለመዘጋጀት ነው።

ፈተና ሲደርስ ከሚስተዋሉ ገጠመኞች ውስጥ ጥቂቶቹ

ካፌ ላይ መፎገር
ስልክን library, class, cafe etc መርሳት ወይም መጣል
Calculator መርሳት / መጣል
PC መርሳት ለዛውም space ( class)
ያነበቡትን መርሳት
ራስን መሳት ( በተለይ ሴቶች)
ወዘተ....

ታድያ ምን ይሻላል

የሚሻለውማ
ፈተና ሳይደርስ ሁሉንም course cover ማድረግ
ከጭንቀታም ጓደኛ መራቅ ( በሰላሙ ሰአት እናንተ ስታነቡ ከማያነበው ማለቴ ነው)
ከጎበዝ ተማሪ ጋር መጎዳኘትና አብሮ ማንበብ
ጥያቄዎችን በgroup መስራት
ስለ ፈተና አወጣጥ ከታላላቆቻችን መጠየቅ ( from seniors)
Information gather ማድረግ
ከበግ ተራ በመራቅ ሴቶችን info መጠየቅ ( affirmative ምናምን ብለው ....)

በተረፈ Tension መጠኑ ይለያይ እንጂ አይቀሬ ነገር በመሆኑ ፈታ በሉ።
እንደኔ እንደውም Tension ምንም የማይዘው ተማሪ ካሮት አምራች ገበሬ ይመስለኛል፤ ምክንያቱም አንብቦ ሳይሆን የሚፈተነው position አስተካክሎ ነው ።

ሲበዛ ነው እንጂ የማይነፋው ተማሪ ካነበበ እስከሚፈተን ድረስ Tension Normal ነው።

ጨርሻለሁ (በ Eng.Muja የተዘጋጀ )

ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
554 viewsedited  16:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-10 17:29:38
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የላቀ ውጤት በማስመዝገብ የውጪ ሀገር የትምህርት ዕድል /Scholarship/ ስለተሰጣቸው ተማሪዎች ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡

በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 3.3 በመቶ ተማሪዎች ብቻ ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚያስገባቸውን ከ50 በመቶ በላይ ውጤት ማስመዝገባቸው ይታወቃል፡፡

ከነዚህም መካከል 263 የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከ600 በላይ ውጤት (ከ700) እንዲሁም 10 የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ከ500 በላይ ውጤት (ከ600) በማምጣት የላቀ ውጤት አስመዝግበዋል፡፡

መንግሥት ለእነዚህ 273 ተማሪዎች የካቲት 21/2015 ዓ.ም የእዉቅና ሽልማት መስጠቱ ይታወሳል፡፡ በዕለቱ ለእነዚህ ተማሪዎች በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ የትምህርት ዕድል /Scholarship/ እንደተሰጣቸውም ተገልጿል፡፡

ተማሪዎቹ ከመስከረም 2016 ዓ.ም ጀምሮ የትምህርት ዕድሉን በመጠቀም እንዲማሩ ሁኔታዎች መመቻቸታቸውም ተመላክቷል፡፡ ወደ ዉጪ እስከሚሄዱ ድረስ ባሉት ግዜያትም የእንግሊዝኛ ቋንቋ ማሻሻያ ትምህርት ይሰጣቸዋል ተብሏል፡፡

የተፈጠረዉ የትምህርት ዕድል አስገዳጅ አለመሆኑ የተገለጸ ሲሆን ሀገር ውስጥ ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች መማር የሚፈልጉ ተማሪዎች የሚገደዱበት ሁኔታ እንደሌለ ተገልጿል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
545 viewsedited  14:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ