Get Mystery Box with random crypto!

Ethio University

የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiouniversty1 — Ethio University E
የቴሌግራም ቻናል አርማ ethiouniversty1 — Ethio University
የሰርጥ አድራሻ: @ethiouniversty1
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 4.85K
የሰርጥ መግለጫ

ለማንኛውም አይነት የማስታወቂያ ስራ እና ክሮስ(Cross)
💰💰 @Cozboy0 💰💰
ያናግሩን🎫🎟🎪🎪🎪🎪

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-04-07 09:12:40
የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ኃላፊዎች እና የተለያዩ መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች አመራሮች የመቐለ ዩኒቨርሲቲን ጎብኝተዋል።

አመራሮቹ የተፈናቀሉ ዜጎች መቆያ ማዕከላትንም ጎብኝተዋል።

ጉብኝቶቹን ተከትሎ ልዑካኑ በትግራይ ክልል ተቋርጦ የቆየው ጠቅላላ እና ከፍተኛ ትምህርት ያለበትን ሁኔታ ገምግመዋል።

የአመራሮቹ ውይይት ነገ እንደሚቀጥል ተገልጿል።



share share

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
346 viewsedited  06:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 15:25:52
#Update

ጫላ ዋታ (ዶ/ር) ያለ መከሰስ መብታቸው እንደተነሳ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለዋል

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 13ኛ መደበኛ ጉባኤ፤ ያለ መከሰስ መብታቸውን ያነሳባቸው የቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝደንት ጫላ ዋታ (ዶ/ር) በፖሊስ ቁጥጥር ሥር መዋላቸው ታውቋል፡፡

የምክር ቤት አባሉ ያለ መከሰስ መብታቸው የተነሳው ፍትሕ ሚኒስቴር በሙስና ወንጀል ጠርጥሬያቸዋለሁ ብሎ ለምክር ቤቱ ባቀረበው ጥያቄ መሰረት ነው፡፡ አባሉ የመንግሥት ግዥ ሕግ ከሚፈቅደው ሕግ ውጪ፣ በግላቸው ለመሰረቱት ቢ ኤች ዩ ኮንሰልታንስ የተባለ የንግድ ድርጅት በግንባታ አማካሪነት በመቅጠር በቀጥታ ግዥ በመፈጸም በመንግሥት ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል ተብሏል፡፡

በተደረገባቸው ምርመራ ከ23 ሚሊየን ብር በላይ ከዩኒቨርሲቲው አካውንት ወደ ድርጅቱ ያለአግባብ ገቢ መደረጉ የተገለጸ ሲሆን፤ 195 ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ያለ አግባብ ግዥ እንዲፈጸም ማድረጋቸው ተረጋግጧል ተብሏል። በተጨማሪም በ116 ሚሊዮን ብር በግል ተቋራጭ ሥም 14 ተሸከርካሪዎችና ማሽነሪዎች እንዲፈጸም ማድረጋቸው ተጠቁሟል፡፡ በዩኒቨርስቲው ገንዘብ የተገዙ ተሸከርካሪዎችና ማሽነሪዎች ባለቤትነታቸው በግል ድርጅት ሆኖ መገኘቱም ተመላክቷል፡፡

ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳው ጫላ ዋታ (ዶ/ር) ለምክር ቤቱ በሰጡት የመከራከሪያ ሃሳብም፤ ቢ ኤች ዩ ኮንሰልታንስ የዩኒቨርሲቲው የገቢ ማመንጫ ድርጅት ነው ብለዋል።

በዚህም መሰረት ምክር ቤቱ ዛሬ ያካሄደውን 13ኛ መደበኛ ጉባኤ ሲያጠናቅቅ፤ ያለ መከሰስ መብታቸው የተነሳባቸ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝደንት ጫላ ዋታ (ዶ/ር) በፖሊስ ቁጥጥር ሥር መዋላቸው ተሰምቷል።

share share

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
646 viewsedited  12:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 15:23:41
ለወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የ2015 ተመራቂ ተማሪዎች በሙሉ

በ2015 ዓ.ም. በሚሰጠዉ መዉጫ ፈተና (Exit Exam) ዙሪያ ከመደበኛ እና ከተከታታይ ትምህርት ፕሮግራም ተማሪዎች ጋር ሰፊ ዉይይት ተደርጓል፡፡ በዚህ ዉይይት እንደተገለፀዉ እና ትምህርት ሚኒስተር ባሰወቀዉ መሠረት የ2015 ዓ.ም. መዉጫ ፈተና (Exit Exam) የሚሠጠዉ በሐምሌ 15/2015 መሆኑን እየገለፅን ምንጩ ባልታወቀ በተለያየ ማህበራዊ ሚዲያ በሚለጠፈዉ ማስታወቂያ እንዳትዘናጉ እናሳዉቃለን ሲል ዩንቨርሲቲው ገልጿል።


፨ይህ መልዕክት የሌሎች የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎችንም ያጠቃልላል

share share

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
508 viewsedited  12:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-04 15:22:16 የ ቡሌሆራ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ጉዳይ

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የብልጽግና ፓርቲ አባልን ያለመከሰስ መብት አነሳ!

የምክርቤቱ አባሉ ያለመከሰስ መብት የተነሳበት ዝርዝር ጉዳይ በፍትህ ሚኒስቴር ተጣርቶ ቀርቧል። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባከሄደው 13ኛ መደበኛ ጉባኤው የብልጽግና ፓርቲ አባል የሆኑ የምክር ቤቱን አባል ያለመከሰስ መብት አንስቷል።ምክርቤቱ የዶክተር ጫላ ዋታን ያለመከሰስ መብት ነው ያነሳው።የፍትህ ሚኒስቴር የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት የነበሩት ዶክተር ጫላ ዋታ ያለመከሰስ መብታቸውን ያስነሳሉ ያላቸውን ጉዳዮች በማጣራት ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ልኳል።

ኮሚቴውም ጉዳዩን ሲያጣራ ቆይቶ ዛሬ የውሳኔ ሃሳቡን አቅርቦ ምክርቤቱ ያለመከሰስ መብታቸውን አንስቷል። ዶክተር ጫላ ዋታ የቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት በነበሩበት ወቅት፥ የተለያዩ የማማከር ስራዎችን የሚያከናውን ድርጅት አቋቁመው ዩኒቨርሲቲውን ለከፍተኛ ኪሳራ መዳረጋቸው ተገልጿል። ዶክተር ጫላ ቢ ኤች ዩ ኮንሰልታንስ የተባለ ድርጅትን በማቋቋም በተለያዩ የወንጀል ድርጊቶች መሳተፋቸውን የፍትህ ሚኒስቴር ባደረገው ማጣራት ማረጋገጡን ነው የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የገለጹት።

ከ23 ሚሊየን ብር በላይ ከዩኒቨርሲቲው አካውንት ወደ ድርጅቱ ያለአግባብ ገቢ መደረጉን ያነሱት ሰብሳቢዋ፥195 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የተለያዩ የግንባታ ስራዎችን ለ9 ተቋራጮች ከመንግስት የግዥ አዋጅና መመሪያ ውጪ በቀጥታ እንዲፈጸም ማድረጋቸው መረጋገጡንም አብራርተዋል።116 ሚሊየን ብር የሚያወጡና ዋጋቸው እጅግ የተጋነነ 14 ተሽከርካሪዎችና ማሽነሪዎች በግል ተቋራጭ ድርጅት ስም ግዥ ተፈጽሟል የሚለውም በቀረበው የውሳኔ ሃሳብ ላይ ተነስቷል።

ዩኒቨርሲቲው ለካፒታል ወጪ የተመደበለትን በጀት ያለአግባብ መጠቀማቸውን የኦዲት ሪፖርቶች እንደሚያመላክቱም ነው የተጠቆመው።
በባለቤታቸው ስም 10 ሚሊየን ብር የሚያወጣ ህንጻ ገዝተዋል የሚለውም የተነሳው ጉዳይ ነው።ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳው ዶክተር ጫላ ዋታ በሰጡት ምላሽም ቢ ኤች ዩ ኮንሰልታንስ የዩኒቨርሲቲው የገቢ ማመንጫ ድርጅት ነው።

በድርጅቱ በኪል የሚፈጸሙ የገንዘብ ዝውውሮችም የዩኒቨርሲቲው ናቸው የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።አብዛኞቹ የተጠቀሱት ጉዳዮችም በዩኒቨርሲቲው የኦዲት ሪፖርቶች ላይ የተመላከቱ ናቸው በሚል አስተባብለዋል።ይሁን እንጂ የህግና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢዋ የድርጅቱ ስራ አስፈጻሚም ሆነ የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ጫላ ናቸው፤ ፈቃዱም በሳቸው መውጣቱን በምርመራ ስራው ተረጋግጧል ነው ያሉት።የዶክተር ጫላ ዋታ ያለመከሰስ መብት በአንድ ድምጸ ተአቅቦ (በራሳቸው በዶክተር ጫላ) በአብላጫ ድምጽ ጸድቋል።

share share

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
484 viewsedited  12:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-03 20:54:19
በ18 ሺህ የትምህርት ማስረጃዎች ላይ የህጋዊነት ማረጋገጫ ተደርጎ 900 የሚሆኑት ሐሰተኛ ሆነው ተገኙ።

የትምህርት ማስረጃዎቹ ተመሳስለው የተሠሩ፣ ዕውቅና ከሌለው ተቋም የተሰጡ፣ ባልተፈቀደ የሙያ መስክ የሰለጠኑ እንዲሁም የመቁረጫ ነጥብና የብቃት ማረጋገጫ ሳይኖራቸው የሠለጠኑ መሆናቸውን የትምህርትና ስልጠና ባለሥስልጣን አሳውቋል።

የተወሰኑ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከባለሥልጣኑ ዕውቅና ውጪ ካምፓስ አስፋፍተውና ፍቃድ ባላገኙበት የትምህርት ዘርፍ ስልጠና ሲሰጡ መገኘታቸውንም ባለሥስልጣኑ አረጋግጧል።

ባልተፈቀደላቸው የትምህርት መርሃ ግብር እና ከተቀመጠላቸው ቁጥር በላይ ተማሪዎችን ተቀብለው ሲያስተምሩ የነበሩ ተቋማት መገኘታቸውንም የባለሥስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ሽፈራው ሽጉጤ ገልጸዋል።

share share

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
202 viewsedited  17:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 22:44:13
ከተማሪዎች የቤት ሥራ እስከ ፕሬዝዳንቶች ንግግር የሚጽፈው ቻትጂፒቲ
***
ምን ዓይነት መረጃ ይፈልጋሉ? ምን ዓይነት መረጃ ለማግኘት ፈልገው ወደ ኢንተርኔት ደጃፍ ብቅስ ይላሉ?

ከዚህ ቀደም ለጥያቄዎ መልስ ፍለጋ በጉግል መረጃ ማሰሻ ላይ ጽፈው ሰዓታትን አባክነው ከሆነ አሁን ብዙ ነገር ተቀይሯል።

ለጥያቄዎ ፈጣን መረጃ በማቀበል ረገድ ቻትጂፒቲ (ChatGPT ) የትንፋሽዎ ያህል ቅርብ ነው።

ከዚህ በፊት በጉግል የመረጃ ማሰሻ ፈልገው ይማሩት የነበረውን በማሻሻል፣ ክህሎት የሚጠይቀውን ጉዳይ በአጭር ጥያቄ መዳፍዎ ላይ ያስገባል።

ሚሊዮኖች መልዕክቶቻቸውን ለማርቀቅ፣ የዘፈን ግጥሞችን፣ አልፎ ተርፎም የኮምፒውተር ኮዶችን ለመቀመር ይጠቀሙበታል።

ይህ የአርተፊሻል ኢንተለጀንስ (ሰው ሰራሽ አስተውሎት) ለሰፊው ተጠቃሚ ክፍት የሆነው ባለፈው ኅዳር ወር ላይ ነው።

ዝናው ግን የዕድሜውን ያህል አጭር አይደለም።

በኅዳር 2015 ዓ.ም. 2022 ወደ ሥራ የገባው ቻትጂፒቲ (ChatGPT ) በአንድ ሳምንት ውስጥ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ተጠቃሚዎችን አግኝቶ እንደነበር የድርጅቱ ባለቤት ኦፕን ኤአይ በወቅቱ ገልጿል።

ጉግል እና ማይክሮሶፍት ይህንን አርተፊሻል ኢንተለጀንስ አበልጽገው አገልግሎት ላይ ለማዋል እየተጣደፉ ነው።

ማይክሮሶፍት ብቻ በቢሊዮኖች ዶላር መድቦ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ነው። ይህ የወቅቱ የዓለማችን አነጋጋሪ እና አወዛጋቢ ስለሆነው አዲስ ቴክኖሎጂ በቴሌግራም ማናገር ለምትፈልጉ የፈለጋቹትን ነገረ ጠይቁት እንዲውም የአሳይመንት ጥያቄዎችን ጠይቁት መልሰ አለው

@GPT4Telegrambot

share share

@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
687 viewsedited  19:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 22:41:37
በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለተማሪዎች የምግብ አገልግሎት የሚመደበው በጀት ማስተካከያ እንዲደረግበት ተቋማቱ ጠይቀዋል።

እስካሁን ባለው አሰራር ለተማሪዎች ቀለብ በቀን ለአንድ ተማሪ 15 ብር ሲበጀት ቆይቷል፡፡ ዩኒቨርሲቲዎች ግን ለአንድ ተማሪ በቀን እስከ 100 ብር እንደሚያወጡ ይገልጻሉ፡፡

አሁን ባለው የኑሮ ውድነት ምክንያት ለሌላ ሥራ የሚመደበው በጀት ለተማሪ ምገባ እየዋለ መሆኑን አስተያየታቸውን ለኢፕድ የሰጡ የዩኒቨርሲቲ አመራሮች ገልጸዋል፡፡ መንግሥት ወቅታዊ ገበያውን መሠረት ባደረገ መልኩ የዋጋ ማሻሻያ ሊያደርግ ይገባልም ብለዋል፡፡

ለዩኒቨርሲቲዎቹ ለምግብ አገልግሎት የሚመደበውን በጀት ለማስተካከል ትምህርት ሚኒስቴር መመሪያውን የማሻሻል ሥራ እየሠራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር የአስተዳደርና መሠረተ ልማት መሪ ሥራ አስፈጻሚ ሰለሞን አብርሀ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡

በ19 ዩኒቨርሲቲዎች ላይ የተደረገ ጥናትን መሰረት ያደረገ አማካይ የምግብ ዋጋ ለገንዘብ ሚኒስቴር መቅረቡን ሥራ አስፈጻሚው አስረድተዋል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ


@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
554 viewsedited  19:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-30 11:13:51
ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ የ2013 በጀት ዓመት የኦዲት ግኝት ላይ የማስተካከያ እርምጃ መውሰድ መጀመሩን አሳውቋል።

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት ወጪ አስተዳደር እና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲን የ2013 በጀት ዓመት የኦዲት ሪፖርትን መገምገሙ ይታወቃል።

ቋሚ ኮሚቴው ከዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የተገኘውን የሒሳብ ህጋዊነት ኦዲት ሪፖርት መነሻ በማድረግ ለዩኒቨርሲቲው የማስተካከያ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።

ቋሚ ኮሚቴው ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ማስተካከያ ለመውሰድ፤ የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት ግኝቱን ለማረም ከተቋቋመ ግብረ ኃይል ጋር መክሯል።

የፋይናንስ ህግጋትና አሰራሮችን ተከትሎ ከመስራት አኳያ የነበረውን የአሰራር ክፍተት በማረም በቀጣይ ጊዜያት ከኦዲት ግኝት ነጻ ለመሆን ተቀናጅቶ መስራት ተገቢ መሆኑን ማኔጅመንቱ ገምግሟል።

ያለ አግባብ የተከፈሉ ክፍያዎች በፍጥነት ተመላሽ እንዲሆኑ ማኔጅመንቱ ወስኗል።
694 views08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 23:43:36
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ለምክር ቤቱ አባላት ማብራሪየ ሲሰጡ ትምህርትን በተመለከተ ተከታዩን ብለዋል፡-

"በፍኖተ ካርታው በተቀመጠው መሠረት ዩኒቨርሲቲ አናስፋፋም። ታች ጥራት እናስፋፋለን፣ ፈተናን አውቶሜት አናደርጋለን በሚል ላለፋት ሦሥት/አራት ዓመታት ሰፋፊ ሥራ ሲሠራ ቆይቷል። ቅድመ አንደኛ ደረጃን ማስፋት፣ አንደኛ ደረጃን ማስፋት፣ ሁለተኛ ደረጃን ማስፋት፣ በተቻለ መጠን የትምህርት ቤት ምገባን ማስፋት ሙከራዎች እየተደረጉ ነው። አሁንም የትምህርት ጥራት ብዙ ሥራ የሚጠይቅ ስለሆነ በመጻሀፍትም፣ በኢንተርኔትም፣ በተሻሉ መምህራን ገና ሰፋፊ ሥራዎች ይጠበቁብናል። ጅማሮዎቹ የሚታወቁ ናቸው እነዛን አጠናክረን የምንቀጥል ይሆናል።"

ለተጨማሪ መረጃ


@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
75 viewsedited  20:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-28 17:35:48
የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባ ነገ መጋቢት 20/2015 ዓ.ም ይጀመራል፡፡

የመልቀቂያ ፈተናውን ለመውሰድ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች እንደሚመዘገቡ ይጠበቃል፡፡

በበይነ መረብ አማካይነት በሚደረገው ምዝገባ፤ ከመንግስት ትምህርት ቤቶች 850 ሺህ የሚጠጉ እንዲሁም በግል 200 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች እንደሚመዘገቡ ይጠበቃል፡፡

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ምዝገባ ከመጋቢት 20/2015 ዓ.ም እስከ ሚያዚያ 15/2015 ዓ.ም እንደሚከናወን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት መግለጹ ይታወሳል።

ለተጨማሪ መረጃ


@EthioUniversty1 @EthioUniversty1
303 viewsedited  14:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ