Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO-MEREJA®

የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 132.13K
የሰርጥ መግለጫ

Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot ✔

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2024-04-14 09:56:36
ለማዘዝ 0901882392 ይደውሉ

Shine laminated(የሚያብረቀርቅ)።
በውሀ የሚፀዳ እና HD ማራኪ የሆነ!
በቀላሉ ባለው ማንጠልጠያ ሚሰቀል!!
16.9K views06:56
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-14 09:42:43
ኢራን ከ200 በላይ ሚሳኤሎችን ወደ እስራኤል አስወነጨፈች

ለሊቱን ኢራን ከ200 በላይ ገዳይ ድሮኖች፣ ባለስቲክ ሚሳኤሎች እና የክሩዝ ሚሳኤሎችን ወደ እስራኤል ስታስወነጭፍ ማደሯ ተሰምቷል፡፡

ጥቃቱ ከቀናት በፊት በኢራን ቆንስላ ጽ/ቤት ላይ በተፈፀመ የአየር ጥቃት ከፍተኛ የኢራን ጄኔራልን ጨምሮ 13 ሰዎች በመገደላቸው የበቀል እርምጃ መሆኑ ተሰምቷል፡፡

ለሊቱን የእስራኤል ጦር በሰጠው መግለጫ ኢራን ካስወነጨፈቻቸው ሚሳኤሎች ውስጥ አብዛኛውን ማክሸፍ ተችሏል ተብሏል፡፡ ወታደሮች በሁሉም ግንባሮች ተሰማርተውና ተዘጋጅተው የእስራኤልን ግዛት መከላከላቸውን ይቀጥላሉ ሲሉም አስታውቋል፡፡
 
የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ የኢራንን ጥቃት የመከላከል እርምጃዋን እንደምትቀጥል አስገንዝበው የማጥቃት ምላሽ እንደሚሰጡም ተናግረዋል፡፡

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ቢሆኑም ለእስራኤል ያላቸውን ቁርጠኛ ድጋፍ ገልጸው የጂ7 አገራት ቡድን መሪዎችን አስቸኳይ ስብሰባ እንዲቀመጡ ጠይቀዋል፡፡ ይህም የተባበረ ዲፕሎማሲያዊ ምላሽ ለማስተባበር እንደሆነ የኤን ዲቲቪ ዘገባ አመላክቷል፡፡ እንደ እንግሊዝ፣ ፈረንሳይ፣ ሜክሲኮ፣ እና ኔዘርላንድ ያሉ መሰል  የአውሮፓ ሀገራትም የኢራንን ጥቃት አውግዘዋል። የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት ኢራን በእስራኤል ላይ ያደረሰችውን ጥቃት አስመልክቶ ዛሬ አስቸኳይ ስብሰባ ያካሂዳል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

   - ETHIO-MEREJA -
   
T.me/ethio_mereja
18.8K viewsedited  06:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 11:07:37
አሜሪካ ወደ መካከለኛው ምስራቅ ተጨማሪ ኃይል መላኳን አስታወቀች።

አሜሪካ ወደ መካከለኛው ምስራቅ ተጨማሪ ኃይል መላኳን ያስታወቀችው ኢራን በእስራኤል ላይ የበቀል ጥቃት ታደርጋለች የሚለው ስጋት ባየለበት ወቅት ነው።እስራኤል ሳታደርሰው አትቀርም በተባለው ጥቃት በሶሪያ የሚገኘው የኢራን ኢምባሲ መመታቱን ተከትሎ ኢራን እንደምትበቀል በተጋጋሚ ዝታለች።

በዚህ ጥቃት ከፍተኛ የኢራን ሪቮሉሽናሪ ጋርድ አባል የሆነ ወታራዊ ባለስልጣንን ጨምሮ ሰባት ሰዎች ተገድዋል።የኢራኑ መሪ አያቶላህ አሊ ካሚኒ ባለፈው የረመዳን ፆም ማብቂያ ላይ እንደተናገሩት ጥቃት አድራሿ እስራኤል መቀጣት አለባት የሚል ዛቻ ማሰማታቸው ይታወሳል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በኢራን ይደገፉል የሚባለው የሊባኖሱ ታጣቂ ሂዝቦላም፣እሰራኤል በደቡባዊ ሊባኖስ አድርሳዋለች ላለው ጥቃት ምላሽ ለመስጠት የእስራኤልን የከባድ መሳሪያ ይዞታዎች ኢላማ ማድረጉን ገልጿል።የአሜሪካው ፕሬዝደንት ጆ ባይደን አሜሪካ በእስራኤል ጥቃት መሰንዘሯ የማይቀር ነው ሲሉ በትናንትናው እለት አስጠንቅቀዋል።እስራኤል፣ ኢራን ልትቃጣው ለምትችለው ማንኛውም አይነት ጥቃት ለመከላከል ዝግጁ መሆኗን ገልጻለች።

የእስራኤል እና የኢራን ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት ወትሮውንም መልካም የሚባል ባይሆንም፣ ከደማስቆው የኢምባሲ ጥቃት በኋላ ወደ ከፋ ደረጃ ደርሷል።

   - ETHIO-MEREJA -
   
T.me/ethio_mereja
13.4K viewsedited  08:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 09:01:39
አሁን ነው ቤት መግዛት
               
               09-02-57-79-57
ከካስማ ሪል እስቴት በጊዜ የሚረከቡት አፓርትመንት ቤቶችን በሽያጭ ላይ ነን።

የግንባታ ደረጃቸው ከ 60% በላይ የደረሱ የከርሰምድር ውሃ ያላቸው አፓርታማ ቤቶችን
በሙሉ ግንባታ(Full Finished)  በጎተራ ማሳለጫ ላይ ይዘን መተናል።

በ 30% ቅድሚያ ክፍያ የቤት ባለቤት ይሁኑ።

  ባለ ሶስት መኝታ = 2 መታጠቢያ ቤት

     117 ካሬ          124 ካሬ
      118 ካሬ          140 ካሬ
      120 ካሬ          147 ካሬ

በህንጻችን ላይ ያሉ ተጨማሪ አገልግሎቶች
24/7 back up ጀነሬተር
የከርሰ ምድር ውሀ
የ24 ሰአት የካሜራ አገልግሎት(CCTV Service )
2 ወለል(Floor) ለመኪና ማቆሚያ
1ሺ ካሬ ሜትር ላይ ያረፈ የተንጣለለ ቴራስ
በአንድ ፍሎር 3 አባዎራ ብቻ

ይምጡ የቤት ባለቤት ይሁኑ!
  ለበለጠ   መረጃ ይደውሉልን!!!
       0902577957
http://tiktok.com/@asset8888homes
https://t.me/+laRkhRKMCHJhZjlk
https://wa.me/251902577957
14.2K views06:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 07:00:17
Are you interested in becoming an AI engineer?

Join the Kifiya AI Mastery Training Program (Kifiya AIM 1) by Kifiya Financial Technology and 10 Academy. It's a 3-month intensive course beginning on April 29, 2024, focusing on Machine Learning and Data Engineering. Gain fast career advancement in AI and data science through industry-led projects, expert sessions, and explore fintech career opportunities in Addis Ababa, Ethiopia. Special consideration for women and vulnerable groups.

Eligibility criteria:

- Undergraduates (preferred) aged 22-34

- Has legal right to work in Ethiopia.

- Fluent in English (B1 CEFR level), with some background in Python, SQL, and Statistics.

- Ready to commit 30-40 hours weekly, with a strong work ethic and community spirit.

Submit your application by the deadline of April 17, 2024.

Application link: https://apply.10academy.org/login

Learn more about the program: https://10academy.org/kifiya/learn-more

For any question, contact us at kifiya_ai@10academy.org
13.9K views04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 21:48:48
በፖለቲከኛ በቴ ኡርጌሳ ግድያ የተጠረጠሩ 13ሰዎች ታሰሩ!
 
በኦሮሞ ነጻነት ግንባር የፖለቲካ ኦፊሰር አቶ በቴ ኡርጌሳ ግድያ የተጠረጠሩ 13 ሰዎችን ፖሊስ ማሰሩ ተዘገበ ።

አቶ በቴ የተገደሉበት መቂ የሚገኝበት የምሥራቅ ሸዋ ዞን ፖሊስ በአቶ በቴ ግድያ የተጠረጠሩ 13 ሰዎችን ማሰሩን የኦሮምያ ብሮድካስቲንግ ኔት ዎርክ ትናንት ማምሻውን በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል። ስለ ተጠርጣሪዎቹ ማንነት የወጣ ዝርዝር መረጃ የለም።

አቶ በቴ ማክሰኞ ምሽት በመንግሥት ኃይሎች በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ አስከሬናቸው በትውልድ ከተማቸው መቂ ከተማ ውስጥ እሮብ ጠዋት መንገድ ዳር ተጥሎ መገኘቱን የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ኦነግ አስታውቋል። የ41 ዓመቱ አቶ በቴ በየካቲት ወር ከፈረንሳዊው ጋዜጠኛ አንትዋን ጋሊንዶ ጋር ከታሰሩ በኋላ ባለፈው ወር ነበር በዋስ ከእስር የተለቀቁት።

ሆኖም በዚህ ሳምንት ማክሰኞ ምሽት ከአዲስ አበባ በስተደቡብ 150 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው በትውልድ ከተማቸው በመቂ ካረፉበት ሆቴል በመንግሥት ኃይሎች ታስረው መወሰዳቸውን የኦነግ ቃል አቀባይ ለሚ ገመቹ ለፈረንሳይ ዜና አገልግሎት AFP ተናግረዋል። አቶ በቴ በዚያኑ ወቅት በከተማዋ ወደሚገኝ ማቆያ ማዕከል መወሰዳቸውን ለሚ ገልጸዋል። የአቶ በቴ ስርዓተ ቀብር ትናንት በትውልድ ስፍራቸው በመቂ ተፈጽሟል።

   - ETHIO-MEREJA -
   
T.me/ethio_mereja
15.8K viewsedited  18:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 16:55:51
መንግስት በሳዑዲ አረብያ እስር ቤቶች የነበሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ስራ ጀመረ!

በሳዑዲ አረብያ እስር ቤቶች እና ማቆያ ማዕከላት ውስጥ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገር ውስጥ የመመለስ ስራ በይፋ መጀመሩን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

መንግስት በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ 70 ሺህ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው እንደሚመልስ መግለጹ ይታወሳል።ይህንን ተከትሎም ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ስራ በይፋ የተጀመረ ሲሆን፤ በዛሬው ዕለት በሁለት በረራዎች 842 ኢትዮጵያዊያን ከሳኡዲ አረቢያ ወደ አገር ቤት መግባታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነብዩ ተድላ እንደገለፁት መንግሰት በቀጣይ አራት ወራት በሳኡዲ አረቢያ በእስር ላይ የሚገኙ ከ70 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንን ወደ አገር ቤት ለማስመለስ እቅድ ይዞ እየሰራ ነው።ስራውን ለማስጀመር 16 የመንግስት ተቋማትን በአባልነት ያቀፈ ብሄራዊ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን የማስመለስ ሂደቱን ለማስጀመር ኮሚቴው ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ወደ ሳኡዲ በመጎዝ ከሃገሪቱ መንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር የዝግጅት ስራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል።

በተያዘው እቅድ መሰረት ዜጎችን ለመመለስ በሳምንት 12 በረረዎችን በቀጣይ አራት ወራት በተከታታይ የሚደረግ መሆኑም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።በውጭ ጉጋይ በሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ የተመራ የመንግስት የልዑካን ቡድን ወደ ሳዑዲ አረቢያ በማቅናት ከጅዳ አስተዳደሮች ጋር ውይይት በማድረግ በእስር ቤትና ማቆያ ጣብያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን መጎብኘቱ ይታወሳል።

   - ETHIO-MEREJA -
   
T.me/ethio_mereja
17.9K viewsedited  13:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 15:12:25
#ቦሌ

የአዲስ አበባ ፖሊስ “የሽበር ጥቃት ለመፈፀም ተልዕኮ ይዘው ሲንቀሳቀሱ” ነበር ባላቸው “የፋኖ አመራርና አባላት ላይ እርምጃ ወሰድኩ” አለ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ፖሊስ ኮሚሽን ዛሬ ሚያዚያ 4 ቀን 2016 ዓ.ም ቀትር ላይ ባወጣው መግለጫ “በፅንፈኛው #የፋኖ አመራርና አባላት ላይ እርምጃ ተወሰድኩ” ሲል አስታውቋል።

“የፅንፈኛው አመራርና አንድ የቡድኑ አባል ሲገደሉ አንደኛው በቁጥጥር ስር ውሏል” ብላል።

ናሁሰናይ አንድአርጌ ታረቀኝ፣ አቤኔዜር ጋሻው አባተ እና ሀብታሙ አንድአርጌ ተሰማ የተባሉት “የፅንፈኛው ፋኖ ቡድን አባላት” በመዲናዋ የሽበር ጥቃት ለመፈፀም ተልዕኮ ይዘው እየተንቃሰቀሱ መሆኑን የፀጥታ አካላት ባደረጉ ክትትል ደርሰውበታል ሲል የፖሊስ መግለጫ አስታውቋል።

ሂደቱን አስመልክቶ የፖሊስ መግለጫ እንዳመላከተው ተጠርጣሪዎቹ እንቅስቃሴ እያደረጉ ባለበት ሁኔታ ሚያዚያ 4 ቀን 2016 ዓ/ም ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው ሚሊኒዬም አዳራሽ አካባቢ የፖሊስ አባላት እጃቸውን እንዲሰጡ ቢጠየቁም ፍቃደኛ አልሆኑም ብሏል።

በዚህም በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2C 14373 አ/አ አይነቷ ሱዙኪ ዲዛዬር መኪናን በመጠቀም ከፖሊስ አባላት ጋር ቶክስ በመክፈታቸው “ናሁሰናይ አንዳርጌ ታረቀኝ” ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ ሲሞት ሌላኛው “ሀብታሙ አንዳርጌ ተሰማ” የተባለው ደግሞ በተኩስ ልውውጡ መሃል መገደሉን ጠቁሟል።

“አቤኔዘር ጋሻው አባት” የተባለው የቡድኑ አባል ሳይቆስል በቁጥጥር ስር መዋሉን አዲስ አበባ ፖሊስ በመግለጫው አስታውቋል፡፡2 የፖሊስ አባላቱ ሳጅን አራርሳ ተሾመ እና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ መቁሰላቸውን የጠቆመው ፖሊስ “አቶ እንዳሻው ጌትነት” የተባሉ ግለሰብ በፅንፈኛው አባላት ተገድለዋል ብሏል።

   - ETHIO-MEREJA -
   
T.me/ethio_mereja
18.1K viewsedited  12:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 13:13:12
Are you interested in becoming an AI engineer?

Join the Kifiya AI Mastery Training Program (Kifiya AIM 1) by Kifiya Financial Technology and 10 Academy. It's a 3-month intensive course beginning on April 29, 2024, focusing on Machine Learning and Data Engineering. Gain fast career advancement in AI and data science through industry-led projects, expert sessions, and explore fintech career opportunities in Addis Ababa, Ethiopia. Special consideration for women and vulnerable groups.

Eligibility criteria:

- Undergraduates (preferred) aged 22-34

- Has legal right to work in Ethiopia.

- Fluent in English (B1 CEFR level), with some background in Python, SQL, and Statistics.

- Ready to commit 30-40 hours weekly, with a strong work ethic and community spirit.

Submit your application by the deadline of April 17, 2024.

Application link: https://apply.10academy.org/login

Learn more about the program: https://10academy.org/kifiya/learn-more

For any question, contact us at kifiya_ai@10academy.org
16.7K views10:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 12:52:44
ኬንያ በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል ያለውን ውጥረት ለማርገብ ቀጠናዊ የባህር ስምምነት ሃሳብ አቀረበች!

ኬንያ በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል ያለውን ውጥረት ለማርገብ ቀጠናዊ የባህር ላይ ስምምነት ሃሳብ ማቅረቧን ሮይተርስ የዜና ምንጭ ዘግቧል።

ኬንያ ፤ከጅቡቲ እና ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት ድርጅት ኢጋድ ጋር በመመካከር ያቀረበችው ይህ ስምምነት ወደብ የሌላቸው ሀገራት በንግድ እንዴት ወደብ መጠቀም እንደሚችሉ የሚገዛ መሆኑን የኬንያ የውጭ ጉዳይ ዋና ጸሃፊ ኮሪር ሲንግኦኢ ለሮይተርስ ተናግረዋል።የቀጠናው ሀገራትን የሚያገናኘው ኢጋድ የባህር ሃብትን ለመጋራት የሚያስችል ስምምነት መፍጠር እንደሚችልም የኬንያው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ተናግረዋል።

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ በትናትናው ዕለት ከኬንያ አቻቸው ዊሊያም ሩቶ ጋር በኬንያ ዋና ከተማ ለውዝግቡ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ተወያይተዋል።በውይይቱ መጨረሻም « ቀጠናው የተረጋጋ እንዲሆን ለማድረግ ከሁሉም አካላት ጋር መገናኘታችንን እንቀጥላለን» ሲሉ ሲንግኦይ መናገራቸውን የሮይተርስ ዘገባ ያሳያል።የናይሮቢ መፍትሄ ተቀባይነት ካገኘ ኢትዮጵያ «የተረጋጋ እና ተገማች የባህር ሀብት ተደራሽነት»ን ስለሚሰጥ የንግድ ስራዋን ያለምንም እንቅፋት እንድትፈጽም እና የሶማሊያን የግዛት አንድነት እንደሚያከብርም አክለዋል።

እንደ ሮፕተርስ ዘገባ ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ ሃሳቡን እያጤኑበት ነው ያሉት ዳይሬክተሩ፥ መሪዎቻቸው ሂደቱን ወደፊት ለማራመድ ተገናኝተው እንዲመክሩበት ተጠይቀዋል።
.
15.8K views09:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ