Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO-MEREJA®

የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 132.13K
የሰርጥ መግለጫ

Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot ✔

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2024-04-08 16:02:42
ባህርዳር

በአማራ ክልል መዲና በባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 14 ትላንት መጋቢት 29 የመግሪብ ሰላት ሰግደው ሲመለሱ የነበሩ አባት ከ3 ልጆቹ እንዲሁም አንድ ጎረቤታቸውን ጨምሮ አጠቃላይ 5 ሰዎች በተከፈተባቸው የጥይት እሩምታ መገደላቸው ተነግሯል።

ትላንትና ምሽት በግፍ የተገደሉት ፥ አቶ ሙሄ ፣ ልጃቸው አበባዉ ሙሄ ፣ ሽኩር ሙሄ ፣ ሙላት ሙሄ እና ጎረቤታቸው አቶ እንድሪስ የተባሉ ሲሆኑ ስርዓት ቀብራቸው በዛሬው ዕለት ተፈፅሟል።

እስካሁን ገዳዮች ስለመያዛቸው የተባለ ነገር የለም።

በከተማዋ ከተገደሉት ሰዎች ባሻገር ባህርዳር ከተማ አባይ ማዶ የሚገኘው መስጂድ ከፍተኛ የመሳሪያ ድብደባ እንደተፈፀመበት ተገልጿል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዛሬ የባህር ዳር ሙስሊሞች በክልሉ በሙስሊሞች ላይ አነጣጥረዋል ያሉትን ግድያ እና እገታ በመቃወም ሰልፍ ማድረጋቸውን " ሀሩን ሚዲያ " ዘግቧል።እስካሁን በአማራ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤትም ሆነ በኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የተሰጠ አስተያየት የለም።

    ETHIO-MEREJA
   
T.me/ethio_mereja
16.8K viewsedited  13:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 13:07:48
ኢትዮጵያ የአለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የሚያግዛትን 5ኛ ዙር ድርድር በግንቦት ወር ታካሂዳለች - የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር

ኢትዮጵያ #የአለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የሚያግዛትን 5ኛ ዙር ድርድር በግንቦት ወር እንደምታካሂድ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ገብረ መስቀል ጫላ ገለፁ።

ኢትዮጵያ ከ20 ዓመታት በፊት የዓለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን እንቅስቃሴ ብትጀምርም በኮቪድ-19 ወረርሽኝና በሌሎች ምክንያቶች ድርድሩ ተቋርጦ እንደነበር ይታወሳል።

ኢትዮጵያ የአለም የንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የጀመረችውን ጥረት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ከቆመበት ለማስቀጠል የተለያዩ ተግባራት እያከናወነች ነው ሲሉ አቶ ገብረ-መስቀል ጫላ መናገራቸውን ከኢዜአ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ከተከናወኑ ተግባራት መካከልም የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን በሐምሌ 2015 ዓ.ም ወደ ጄኔቫ አቅንተው ከድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ጋር በጉዳዩ ዙሪያ ውይይት ማድረጋቸውን ጠቅሰዋል፤ በውይይቱም ኢትዮጵያ በሶስት ዓመት ጊዜ ውስጥ የድርድር ሂደቱ እንዲጠናቀቅና የድርጅቱ አባል እንድትሆን ከሥምምነት ላይ መደረሱን አስታውቀዋል።

በዚህም ከኢትዮጵያ ጋር ድርድር ለማድረግ ፍላጎት ካላቸው ከአባል አገራቱ 180 የሚጠጉ ጥያቄዎችና 9 ሰነዶች መቅረባቸውን ተናግረዋል።በቅርብ ጊዜ ውስጥ ድርጅቱ በሚያመቻቸው መድረክ ድርድሩ እንደሚጀመር ሚኒስትሩ ጠቁመዋል።

    ETHIO-MEREJA
   
T.me/ethio_mereja
16.3K viewsedited  10:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 11:58:57
ዋው የሚያስብሉ የግድግዳ ምስሎች

Shine laminated(የሚያብረቀርቅ)ናቸው።
በውሀ የሚፀዳ እና HD ማራኪ ናቸው!
በቀላሉ ባለው ማንጠልጠያ ሚሰቀል!!

     በትዛዝ በ3ቀን እናደርሳለን።

  ዋጋ :-  1.50*80 - 3500ብር
  ዋጋ :-  1.20*60 - 3000ብር

አድራሻ 4killo/ቀበና #ቤሊየር አልዘይን ህንፃ 207ቁ

     0901882392 /
     0931448106

ተጨማሪ T.me/Dinkwallarts
ON HAND - የጌታ እራት አለ።
14.6K views08:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 11:13:14
የቦይንግ አውሮፕላን የሞተር ሽፋን በበረራ ላይ ተገንጥሎ መውደቁን ተገለጸ

የአሜሪካው የሳውዝዌስት አየር መንገድ ንብረት የሆነው ቦይንግ 737-800 አውሮፕላን በበረራ ላይ እያለ የሞተሩ ሽፋን ተገንጥሎ መውደቁ ተነገረ።

ወደ አሜሪካዋ ሁስቶን በረራ ላይ የነበረው አውሮፕላ ቸግሩ ማገገሙን ተከትሎ ዴንቨር ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ለማረፍ መገደዱ ተነግሯል።135 መንገደኞችንና 6 የበረራ አባላት ያሳፈረው አውሮፕላን ዴንቨር ለማረፍ ከመደገጉ በፊት 10 ሺህ 300 ጨማ ከፍታ ላይ እየበረረ እንደነበረም ነው የተገለጸው።ችግሩ ማጋጠሙን ተከትሎ የአሜሪካ የአየር መንግድ ተቆጣጣሪዎች አፋጣኝ ምርመራ እያደረጉ መሆኑም ተነግሯል።

የአሜሪካው የሳውዝዌስት አየር መንገድ በቦይንግ ቦይንግ 737-800 አውሮፕላን ላይ ያጋጠመውን ችግር የአየር መንገዱ የጥገና ቡድን እንደሚመረምረው አስታውቀዋል።አየር መንገዱ ለእንደዚህ አይነት ክፍሎች ጥገና ኃላፊነት እንዳለበት አረጋግጧል።ቦይንግ 737-800 አውሮፕላን የተመረተው በፈረንጆቹ በ2015 መሆኑን የፌዴራል አቪዬሽን አስተዳደር (ኤፍኤኤ) መረጃ ያመለክታል።

ቦይንግ ኩባንያ የአሜሪካው የሳውዝዌስት አየር መንገድ በቦይንግ ቦይንግ 737-800 አውሮፕላን ላይ ባጋጠመው ችግር ዙሪያ እስካሁን አስተያየት አልሰጠም።

ኩባንያው በቦይንግ 737 ማክስ 9 አውሮፕላን ምርቶች ላይ ካከናወናቸው 89 የጥራት ምርመራዎች ላይ በ33ቱ ጉድለት እንደተገኘበት መገለጹም ይታወሳል።

    ETHIO-MEREJA
   
T.me/ethio_mereja
14.6K viewsedited  08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-08 09:57:09
YANGOን የጉዞ ምርጫዎ ያድርጉ

ኪሶን ሳይጎዱ ከተማዋን ይንሸራሸሩ! ከYango ጋር፣ ከ72 ብር ጀምሮ ከምቾት እና ከቁጠባ ጋር ይጓዙ!

Yangoን ከApp Store ወይም ከPlay Store ያውርዱ፤ ወይም ወደ 8610 ይደውሉ።

መተግበሪያወን በማውረድ ከመጀመሪያዎ 3 ጉዞዎች ላይ 30% ቅናሽ ያግኙ!
14.9K views06:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-07 14:45:20
በፓሪስ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ!

በፓሪስ በተካሄደ የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንድም በሴትም አሸንፈዋል፡፡

መስታወት ፍቅር 02:20፡45 በመግባት የሴቶቹን ውድድር ስታሸንፍ፤ በወንዶች ሙሉጌታ ኡማ 02፡05፡33 በመግባት ውድድሩን በቀዳሚነት አሸንፏል፡፡ አትሌት እናት ጥሩሰው በ02፡20፡47 በሴቶች ሁለተኛ በመውጣት ውድድሩን አጠናቅቃለች፡፡

በስፔን ማድሪድ ከተማ በተካሄደ በሴቶች ግማሽ ማራቶን አበራሽ አንደኛ ሆናለች።

በሌላ ዜና ደቡብ ኮሪያ ዴጉ ማራቶን በሁለቱም ጾታ ኢትዮጵያ 1ኛ ወጣለች።

በተመሳሳይ በበርሊን ግማሽ ማራቶን በሴቶች አንደኛ እና ሁለተኛ ሆነው ውድድሩን ማሸነፋቸውን የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

    ETHIO-MEREJA
   
T.me/ethio_mereja
17.9K viewsedited  11:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 12:23:18
የደብረብርሃን- ደሴ መንገድ ከአንድ ወር መዘጋት በኋላ ከዛሬ ጀምሮ እንደሚከፈት ተገለጸ

ከአንድ ወር በላይ ተዘግቶ የቆየው የደብር ብርሃን - ደሴ መንገድ ከዛሬ መጋቢት 28 ቀን 2016 ጀምሮ የሚከፈት መሆኑን የማዕከላዊ ሸዋ ኮማንድ ፖስት ገለጸ።

የካቲት 16 ቀን 2016 ጀምሮ “ላልተወሰነ ጊዜ” የሰውና የንብረት እንቅስቃሴ እገዳ እንደተጣለ አዲስ ማለዳ መዝገቧ ይታወሳል።

እገዳው የተጣለው ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ በሚወስደው የአስፋልት መንገድ ላይ “በንፁሀን መንገደኞች ላይ ግድያ፣ እገታ፣ ዘረፋና መሰል አሰቃቂ ወንጀሎች በታጣቂዎች እየተፈጸመ በመሆኑና ጠንካራ የህግ ማስከበር ኦፕሬሽን ስራ እየተሰራ” በመሆኑ ነው ሲል ኮማንድ ፖስቱ አስታውቆም ነበር።

አዲስ ማለዳ ከኮማንድ ፖስቱ ዛሬ ባገኘችው መረጃ መንገዱ እንዲከፈት የተወሰነው በአካባቢው ያለው የሰላም ሁኔታ በመሻሻሉ እና ኅብረሰተሰቡ ባቀረበው ጥያቄ መሠረት መሆኑ ታውቋል።

ይህ ዋና መንገድ ከዚህ ቀደም በተከሰቱ ጥቃቶች፣ ግጭቶች፣ እገታዎችና “ያለአግባብ” በጸጥታ ኃይሎች በሚደረጉ የኬላ ፍተሻዎች ምክንያት ሲዘጋና ሲከፈት መቆየቱ ይታወቃል። የመንገዱ መዘጋት ከአዲስ አበባ ወደ አማራ ክልል የሚደረጉ በርካታ እንቅስቃሴዎችን ገድቦ ቆይቷል።

      - ETHIO-MEREJA -
      
T.me/ethio_mereja
13.1K viewsedited  09:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-06 09:38:59
Samsung  Galaxy  note  3
አዲስ  አንደታሸገ 
32  gb
3 gb ram
ዋጋ 4000  ብር በማከፋፈያ ዋጋ
Call me
0909255008
0912739699
ተጨማሪ ስልኮችን  ለመመልከት
አና ስልክ ለመሽጥ ከፈለጉ ቤተሰብ ይውኑ
https://t.me/used_phone_ethiopian
13.3K views06:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-05 17:46:28 በአዲስ አበባ በነገው ዕለት የለውጡን ዓመታት የሚደግፍ ነው የተባለው ሰልፍ ሊካሄድ ነው!!

በአዲስ አበባ ከተማ በነገው ዕለት ለሚካሄደው የድጋፍ ሰልፍ ቅድመ ዝግጅት ማድረጉን የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ሃይል አስታወቀ።

በሰልፉ ምክንያት የሚዘጉ መንገዶችንም ግብረ ኃይሉ ይፋ አድርጓል። በዚህም ነገ ቅዳሜ መጋቢት 28 ቀን 2016 ከንጋቱ 11 ሰዓት ጀምሮ
• ከቴዎድሮስ አደባባይ በብሄራዊ ቴአትር ወደ ወደ መስቀል አደባባይ ሚወስደው መንገድ ቴዎድሮስ አደባባይ፡፡
•  ከኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል አደባባይ ላይ
•  ከቦሌ አቅጣጫ  ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ
•  ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ ላይ
•  ከጎተራ ማሳለጫ ወደ መስቀል አደባባይ አጎና  ሲኒማ
•  ከቅ/ቂርቆስ ቤ/ክርስቲያን በአዲሱ መንገድ  ወደ መስቀል አደባባይ ለሚሄዱ ለገሀር መብራት ፡፡
•  ከሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ ቴሌ   ለሚጓዙ ለገሀር መብራት ፡፡
•  ከጌጃ ሰፈር አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ሰንጋተራ ትራፊክ መብራት ላይ
• ከሃራምቤ  መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ  መብራት ላይ
•  ከብሔራዊ ቤተ መንግስት  ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ  ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ
•  ከካዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ እንዲሁም
• ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ

አካባቢዎች ዝግ ስለሚሆኑ አማራጭ መንገድ መጠቀም አስፈላጊ ነው ተብሏል። በእነዚህ አካባቢውችም ከዛሬ ምሽት 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ ሰልፉ ፍፃሜ ድረስ ተሽከርካሪ ማቆም እና ማሳደር ተከልክሏል።

      - ETHIO-MEREJA -
      
T.me/ethio_mereja
17.4K viewsedited  14:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-05 16:32:43
Adjustable Laptop & Tablet Stand
High Quality(ብረት የሆነ)

የቀሩት ጥቂት ናቸው!

ላፕቶፕ ጭን ላይ አስቀምጠው መጠቀም ለከፋ ጉዳት እንደሚያጋልጥ የጤና ባለሙያዎች ይናገራሉ ፤ ለዚህ ሁሉ መፍትሄ ተጣጣፊ የላፕቶፕ ፣ ታብሌት Holder በተመጣጣኝ ዋጋ ገዝተዉ ጤንነቶን ይጠብቁ።

ዋጋ፦  1200 ብር! Free delivery

  0901882392    0931448106
16.3K views13:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ