Get Mystery Box with random crypto!

ETHIO-MEREJA®

የሰርጥ አድራሻ: @ethio_mereja
ምድቦች: ዜና
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 131.93K
የሰርጥ መግለጫ

Addisababa, Ethiopia🇪🇹
News & Media Company®
.
USA : Washington
.
.
.
ለጥቆማ እና ማስታወቂያ ለማሰራት
ከታች ያለውን ሊንክ ይጠቀሙ!!
👉 @ethio_merejabot ✔

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 11

2024-04-12 21:48:48
በፖለቲከኛ በቴ ኡርጌሳ ግድያ የተጠረጠሩ 13ሰዎች ታሰሩ!
 
በኦሮሞ ነጻነት ግንባር የፖለቲካ ኦፊሰር አቶ በቴ ኡርጌሳ ግድያ የተጠረጠሩ 13 ሰዎችን ፖሊስ ማሰሩ ተዘገበ ።

አቶ በቴ የተገደሉበት መቂ የሚገኝበት የምሥራቅ ሸዋ ዞን ፖሊስ በአቶ በቴ ግድያ የተጠረጠሩ 13 ሰዎችን ማሰሩን የኦሮምያ ብሮድካስቲንግ ኔት ዎርክ ትናንት ማምሻውን በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል። ስለ ተጠርጣሪዎቹ ማንነት የወጣ ዝርዝር መረጃ የለም።

አቶ በቴ ማክሰኞ ምሽት በመንግሥት ኃይሎች በቁጥጥር ስር ከዋሉ በኋላ አስከሬናቸው በትውልድ ከተማቸው መቂ ከተማ ውስጥ እሮብ ጠዋት መንገድ ዳር ተጥሎ መገኘቱን የኦሮሞ ነጻነት ግንባር ኦነግ አስታውቋል። የ41 ዓመቱ አቶ በቴ በየካቲት ወር ከፈረንሳዊው ጋዜጠኛ አንትዋን ጋሊንዶ ጋር ከታሰሩ በኋላ ባለፈው ወር ነበር በዋስ ከእስር የተለቀቁት።

ሆኖም በዚህ ሳምንት ማክሰኞ ምሽት ከአዲስ አበባ በስተደቡብ 150 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው በትውልድ ከተማቸው በመቂ ካረፉበት ሆቴል በመንግሥት ኃይሎች ታስረው መወሰዳቸውን የኦነግ ቃል አቀባይ ለሚ ገመቹ ለፈረንሳይ ዜና አገልግሎት AFP ተናግረዋል። አቶ በቴ በዚያኑ ወቅት በከተማዋ ወደሚገኝ ማቆያ ማዕከል መወሰዳቸውን ለሚ ገልጸዋል። የአቶ በቴ ስርዓተ ቀብር ትናንት በትውልድ ስፍራቸው በመቂ ተፈጽሟል።

   - ETHIO-MEREJA -
   
T.me/ethio_mereja
15.8K viewsedited  18:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 16:55:51
መንግስት በሳዑዲ አረብያ እስር ቤቶች የነበሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ስራ ጀመረ!

በሳዑዲ አረብያ እስር ቤቶች እና ማቆያ ማዕከላት ውስጥ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገር ውስጥ የመመለስ ስራ በይፋ መጀመሩን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።

መንግስት በሳዑዲ አረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ 70 ሺህ ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው እንደሚመልስ መግለጹ ይታወሳል።ይህንን ተከትሎም ዜጎችን ወደ ሀገር ቤት የመመለስ ስራ በይፋ የተጀመረ ሲሆን፤ በዛሬው ዕለት በሁለት በረራዎች 842 ኢትዮጵያዊያን ከሳኡዲ አረቢያ ወደ አገር ቤት መግባታቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነብዩ ተድላ እንደገለፁት መንግሰት በቀጣይ አራት ወራት በሳኡዲ አረቢያ በእስር ላይ የሚገኙ ከ70 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያንን ወደ አገር ቤት ለማስመለስ እቅድ ይዞ እየሰራ ነው።ስራውን ለማስጀመር 16 የመንግስት ተቋማትን በአባልነት ያቀፈ ብሄራዊ ኮሚቴ የተዋቀረ ሲሆን የማስመለስ ሂደቱን ለማስጀመር ኮሚቴው ካለፈው ሳምንት ጀምሮ ወደ ሳኡዲ በመጎዝ ከሃገሪቱ መንግስት ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር የዝግጅት ስራዎችን ሲያከናውን ቆይቷል።

በተያዘው እቅድ መሰረት ዜጎችን ለመመለስ በሳምንት 12 በረረዎችን በቀጣይ አራት ወራት በተከታታይ የሚደረግ መሆኑም የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።በውጭ ጉጋይ በሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርቱካን አያኖ የተመራ የመንግስት የልዑካን ቡድን ወደ ሳዑዲ አረቢያ በማቅናት ከጅዳ አስተዳደሮች ጋር ውይይት በማድረግ በእስር ቤትና ማቆያ ጣብያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን መጎብኘቱ ይታወሳል።

   - ETHIO-MEREJA -
   
T.me/ethio_mereja
17.9K viewsedited  13:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 15:12:25
#ቦሌ

የአዲስ አበባ ፖሊስ “የሽበር ጥቃት ለመፈፀም ተልዕኮ ይዘው ሲንቀሳቀሱ” ነበር ባላቸው “የፋኖ አመራርና አባላት ላይ እርምጃ ወሰድኩ” አለ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ፖሊስ ኮሚሽን ዛሬ ሚያዚያ 4 ቀን 2016 ዓ.ም ቀትር ላይ ባወጣው መግለጫ “በፅንፈኛው #የፋኖ አመራርና አባላት ላይ እርምጃ ተወሰድኩ” ሲል አስታውቋል።

“የፅንፈኛው አመራርና አንድ የቡድኑ አባል ሲገደሉ አንደኛው በቁጥጥር ስር ውሏል” ብላል።

ናሁሰናይ አንድአርጌ ታረቀኝ፣ አቤኔዜር ጋሻው አባተ እና ሀብታሙ አንድአርጌ ተሰማ የተባሉት “የፅንፈኛው ፋኖ ቡድን አባላት” በመዲናዋ የሽበር ጥቃት ለመፈፀም ተልዕኮ ይዘው እየተንቃሰቀሱ መሆኑን የፀጥታ አካላት ባደረጉ ክትትል ደርሰውበታል ሲል የፖሊስ መግለጫ አስታውቋል።

ሂደቱን አስመልክቶ የፖሊስ መግለጫ እንዳመላከተው ተጠርጣሪዎቹ እንቅስቃሴ እያደረጉ ባለበት ሁኔታ ሚያዚያ 4 ቀን 2016 ዓ/ም ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው ሚሊኒዬም አዳራሽ አካባቢ የፖሊስ አባላት እጃቸውን እንዲሰጡ ቢጠየቁም ፍቃደኛ አልሆኑም ብሏል።

በዚህም በሰሌዳ ቁጥር ኮድ 2C 14373 አ/አ አይነቷ ሱዙኪ ዲዛዬር መኪናን በመጠቀም ከፖሊስ አባላት ጋር ቶክስ በመክፈታቸው “ናሁሰናይ አንዳርጌ ታረቀኝ” ቆስሎ ወደ ህክምና ከተላከ በኋላ ሲሞት ሌላኛው “ሀብታሙ አንዳርጌ ተሰማ” የተባለው ደግሞ በተኩስ ልውውጡ መሃል መገደሉን ጠቁሟል።

“አቤኔዘር ጋሻው አባት” የተባለው የቡድኑ አባል ሳይቆስል በቁጥጥር ስር መዋሉን አዲስ አበባ ፖሊስ በመግለጫው አስታውቋል፡፡2 የፖሊስ አባላቱ ሳጅን አራርሳ ተሾመ እና ኮንስታብል ማቲያስ ጴጥሮስ መቁሰላቸውን የጠቆመው ፖሊስ “አቶ እንዳሻው ጌትነት” የተባሉ ግለሰብ በፅንፈኛው አባላት ተገድለዋል ብሏል።

   - ETHIO-MEREJA -
   
T.me/ethio_mereja
18.1K viewsedited  12:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 13:13:12
Are you interested in becoming an AI engineer?

Join the Kifiya AI Mastery Training Program (Kifiya AIM 1) by Kifiya Financial Technology and 10 Academy. It's a 3-month intensive course beginning on April 29, 2024, focusing on Machine Learning and Data Engineering. Gain fast career advancement in AI and data science through industry-led projects, expert sessions, and explore fintech career opportunities in Addis Ababa, Ethiopia. Special consideration for women and vulnerable groups.

Eligibility criteria:

- Undergraduates (preferred) aged 22-34

- Has legal right to work in Ethiopia.

- Fluent in English (B1 CEFR level), with some background in Python, SQL, and Statistics.

- Ready to commit 30-40 hours weekly, with a strong work ethic and community spirit.

Submit your application by the deadline of April 17, 2024.

Application link: https://apply.10academy.org/login

Learn more about the program: https://10academy.org/kifiya/learn-more

For any question, contact us at kifiya_ai@10academy.org
16.7K views10:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 12:52:44
ኬንያ በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል ያለውን ውጥረት ለማርገብ ቀጠናዊ የባህር ስምምነት ሃሳብ አቀረበች!

ኬንያ በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል ያለውን ውጥረት ለማርገብ ቀጠናዊ የባህር ላይ ስምምነት ሃሳብ ማቅረቧን ሮይተርስ የዜና ምንጭ ዘግቧል።

ኬንያ ፤ከጅቡቲ እና ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት ድርጅት ኢጋድ ጋር በመመካከር ያቀረበችው ይህ ስምምነት ወደብ የሌላቸው ሀገራት በንግድ እንዴት ወደብ መጠቀም እንደሚችሉ የሚገዛ መሆኑን የኬንያ የውጭ ጉዳይ ዋና ጸሃፊ ኮሪር ሲንግኦኢ ለሮይተርስ ተናግረዋል።የቀጠናው ሀገራትን የሚያገናኘው ኢጋድ የባህር ሃብትን ለመጋራት የሚያስችል ስምምነት መፍጠር እንደሚችልም የኬንያው የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ተናግረዋል።

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ በትናትናው ዕለት ከኬንያ አቻቸው ዊሊያም ሩቶ ጋር በኬንያ ዋና ከተማ ለውዝግቡ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ ለማምጣት በሚደረገው ጥረት ተወያይተዋል።በውይይቱ መጨረሻም « ቀጠናው የተረጋጋ እንዲሆን ለማድረግ ከሁሉም አካላት ጋር መገናኘታችንን እንቀጥላለን» ሲሉ ሲንግኦይ መናገራቸውን የሮይተርስ ዘገባ ያሳያል።የናይሮቢ መፍትሄ ተቀባይነት ካገኘ ኢትዮጵያ «የተረጋጋ እና ተገማች የባህር ሀብት ተደራሽነት»ን ስለሚሰጥ የንግድ ስራዋን ያለምንም እንቅፋት እንድትፈጽም እና የሶማሊያን የግዛት አንድነት እንደሚያከብርም አክለዋል።

እንደ ሮፕተርስ ዘገባ ሶማሊያ እና ኢትዮጵያ ሃሳቡን እያጤኑበት ነው ያሉት ዳይሬክተሩ፥ መሪዎቻቸው ሂደቱን ወደፊት ለማራመድ ተገናኝተው እንዲመክሩበት ተጠይቀዋል።
.
15.8K views09:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 11:51:39 ዘመኑ የቴክኖሎጂ ነው የፈለጉትን እቃ
ከቤትዎ ሆነው በቅናሽ ይዘዙ! ይገብዩ!

በቴሌግራም ሚፈልጉት ካለ ይምረጡ*
https://t.me/AddisEka1
https://t.me/AddisEka1

በዘመናዊ እቃዎች፣ ሂዎትዎን ያቅሉ፣ ጊዜዎን ይቆጥቡ!

ከAmazon ፣ ከAlibaba ከመሳሰሉት የሚመጡ!
ልዩ ልዩ የቤት መገልገያ እቃዎች!
ሂወት የሚያቀሉ ከዱባይ ሚገቡ ምርቶች
የውበት መጠበቂያ፣ ቤትዎን ማስዋቢያና ሌሎችም

0901882392 0931448106

አድራሻ ፣ 4ኪሎ-ቀበና ቤሊየር ጋር አልዘይን ህንፃ 207ቁ
  
https://t.me/AddisEka1
16.1K views08:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 07:00:13
Did you miss our February edition EdTech Mondays radio show? No worries, all you have to do is click on the below link and access the full show where we highlight Ethiopia's Digital Education Strategy and Implementation Plan. Join our community and explore the innovative pathways transforming education in Ethiopia. Be part of the conversation!

#EdTechMondays #EdTechMondaysEthiopia #Ethiopia #Africa #Education #EdTech #Tech #AddisAbaba #ICT #Infrastructure #Digital #DigitalLiteracy #Shega #mastercardfoundation

Check out the full video at

17.2K views04:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-11 19:02:11
44 ቢሊየን ዶላር ያጭበረበረችው ቬትናማዊት ቱጃር በሞት እንድትቀጣ ተወሰነ

44 ቢሊየን ዶላር ያጭበረበረችው ቬትናማዊት ቢሊየነር በሞት እንድትቀጣ የሀገሪቱ ፍርድ ቤት ውሳኔ አሳለፈ፡፡

ትሩኦንግ ማይ የተባለችው የ67 ዓመት ቬትናማዊት ቱጃር ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት በሀገሪቱ ከሚገኘው ሳይጎን የንግድ ባንክ ለ11 ዓመታት ያህል ዘረፋ ስትፈፅም እንደነበር ተገልጿል፡፡

ግለሰቧ ከመዘበረችው ገንዘብ ውስጥ 27 ቢሊየን ያህል ዶላር ተመላሽ እንድታደርግ ብይን ቢሰጥም፤ ዐቃቤ ህግ ግለሰቧ ገንዘቡን መመለስ እንደማትችል በማረጋገጡ የሞት ቅጣቱ እንደተላለፈባት ተመላክቷል፡፡

ግለሰቧ የፈፀመችው ወንጀል ውስብስብ የወንጀል ድርጊት ሲሆን በአጠቃላይ 44 ቢሊዮን ዶላር ወይም 35 ቢሊዮን ዩሮ በመመዝበር የሞት ፍርድ የተፈረደባት የመጀምሪያዋ ቬትናማዊት ሆናለች ነው የተባለው፡፡

ቢሊየነሯ ትሩኦንግ ማይ በተለያዩ ሚስጢራዊ ኩባንያዎቿ የሸሸገችውን ሀብት በመጠቀም የወሰደችውን ገንዘብ የምትመልስ ከሆነ የሞት ፍርዱ ሊቀርላት እንደሚችል ተነግሯል።

በግለሰቧ የክስ ሂደቱ 10 አቃቤ ህጎች እና 200 ጠበቆች መሳተፋቸው የተገለፀ ሲሆን 2 ሺህ 700 ምስክሮች ቃላቸውን እንዲሰጡ የጥሪ ወረቀት እንደደረሳቸውና ከ5 ሺህ 400 ኪሎግራም በላይ የሚመዝኑ የሰነድ ማስረጃዎች በ104 ሳጥኖች መቅረባቸውም ተገልጿል።

በቬትናም ታይቶ አይታወቅም በተባለው ግዙፍ የፍርድ ሂደት ከቢሊየነሯ ጋር 85 ሰዎችም ክስ ቀርቦባቸዋል መባሉን የዘጋርዲያን እና ቢቢሲ ዘገባዎች አመልክተዋል።

   - ETHIO-MEREJA -
   
T.me/ethio_mereja
19.9K viewsedited  16:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-11 12:00:17
Did you miss our February edition EdTech Mondays radio show? No worries, all you have to do is click on the below link and access the full show where we highlight Ethiopia's Digital Education Strategy and Implementation Plan. Join our community and explore the innovative pathways transforming education in Ethiopia. Be part of the conversation!

#EdTechMondays #EdTechMondaysEthiopia #Ethiopia #Africa #Education #EdTech #Tech #AddisAbaba #ICT #Infrastructure #Digital #DigitalLiteracy #Shega #mastercardfoundation

Check out the full video at

13.2K views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-10 14:57:23
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) የከፍተኛ አመራሩን ጃል በቴ ኡርጌሳን ግድያ በማውገዝ አፋጣኝ ነጻ፣ ገለልተኛ እና አድሏዊ ያልሆነ ምርመራ እንዲደረግ ጠየቀ።

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) የከፍተኛ አመራሩን ጃል በቴ ኡርጌሳን ግድያ አስመልክቶ መግለጫ አውጥቷል።

በመግለጫው ፤ የፓርቲው አባል እና የፖለቲካ ኦፊሰር ጃል በቴ ኡርጌሳ ዘግናኝ እና አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ መገደላቸውን አመልክቶ የተሰማውን ሀዘን ገልጿል።

"በነቁ የኦሮሞ ፖለቲከኞች እና በታዋቂ ሰዎች ላይ የሚደረገው ግድያ ቀጥሏል " ያለው ኦነግ የታወቂውና ተወዳጁ አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ሳይረሳ እና ቤተሰቦቹ እስካሁን ፍትህ ሳያገኙ የበቴን ኡርጌሳን ግድያ መስማት እጅግ አሳዛኝ ነው ብሏል።

ጃል በቴ በተወለዱበት መቂ ከተማ #በጥይት ተደብድበው መገደላቸውን በመግለጫው ላይ አመልክቷል። "ምንም እንኳን ሁኔታው ​​​​ለሁላችን እጅግ በጣም ከባድ ቢሆንም በግድያው ላይ ተጨማሪ ምርመራ እያደረግን ነው " ሲል ገልጿል። "ሁሉም የሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች እና ሰላም ወዳድ ህዝቦች አፋጣኝ ነጻ፣ ገለልተኛ እና አድሏዊ ያልሆነ ምርመራ እንዲያደርጉ " ጥሪ አቅርቧል።

   - ETHIO-MEREJA -
   
T.me/ethio_mereja
18.3K viewsedited  11:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ