Get Mystery Box with random crypto!

Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ D
የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
የሰርጥ አድራሻ: @debre_markos_university
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.90K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የቴሌግራም ገጽ ነው። የዩኒቨርሲቲያችን ወቅታዊ መረጃዎች፣ ልዩ ልዩ ሁነቶች እና የስራ እና የትምህርት ማስታወቂያዎች ይተላለፉበታል። አሁንኑ ቤተሰብ ለመሆን ይቀላቀሉ!!
This is Our Official Telegram Channel. We Provide up-to-date Information about our University.
Join Us Now!🙏

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-03-15 12:05:29 A workshop is being held regarding women's land ownership rights

==============

Debre Markos University | Ethiopia | March,15/2023 | (Public Relations and Communication Directorate) Debre Markos University Institute of Land administration in collaboration with the University of Natural Resources and Life Sciences Vienna (BOKU) held a 4 day workshop regarding women's land ownership rights. Three scientists from Boku University, senior leaders and teachers of Debre Markos University are taking part in the the workshop.

Dr. Ayelech Kide, a teacher at Debra Markos University's Institute of Land Administration, said the project will last for two years, and the Institute of Land Administration and the School of Law will work together to identify what loopholes and other challenges the law has on women's land ownership in order to include women in the land registration system and provide equal benefits.

Sayeh Kassaw (PhD), Associate professor and Researcher at the Institute of Land Administration, in his part, stated that the relationship between the two universities was established through a private educational opportunity. He mentioned that modernizing the education, digitizing the teaching and learning and supplementing the teaching materials are the activities carried out and are being carried out by the two universities' project.

Debre Markos University

Grow Wiser at the Water Tower!

Join us


https://www.facebook.com/dmu.edu

https://t.me/Debre_Markos_University
https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q
3.2K views09:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-15 12:05:00
3.2K views09:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-14 09:39:11
#አዲስ
1.2K views06:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 17:04:25 “እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ ” በሚል መሪ ቃል የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ተከበረ

=================

ደብረ ማርቆስ ዩንቨርሲቲ | የካቲት 30/2015 ዓ.ም | ህዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት |
በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ112ኛ ጊዜ፣ በሀገራችን ለ47ኛ ጊዜ የተከበረውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (March 8 ) “እኔ የእህቴ ጠባቂ ነኝ ” በሚል መሪ ቃል የካቲት 29/2015 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲያችንም በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተከብሮ ውሏል፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ወጣቶች እና ኤች አይቪ ኤድስ መከላከል ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (March 8) የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ መምህራንና ሰራተኞች፣ ተማሪዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር እንግዶች በተገኙበት ተከብሯል፡፡

በጉባዔው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ታፈረ መላኩ (ዶ/ር) ሴቶችን ወደ ኃላፊነት በማምጣቱ ረገድ እንደ ተቋም ምቹ ሁኔታዎችን መሻሻሎች እንዳሉ ጠቁመው እንደ ሀገር ፍትህና ሰላም እንዲሰፍን የሴቶችን የነቃ ተሳትፎና አበርክቶ ከፍ እንዲል ማስቻል ያስፈልጋል ሲሉ ገልፀዋል። በዚህ ረገድ ደግሞ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ ያሉ ሴቶች ሁለንተናዊ በሆነ መንገድ የተሻለ ንቃተ ህሊና አላቸው ተብሎ ስለሚታሰብ ሀገርንም፣ ተቋምንም፣ መሞገት የሚችሉ ሴቶችን መፍጠር ብንችል መልካም ነው ሲሉም አክለዋል፡፡

በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ማህበራዊና ስነ-ሰብ ኮሌጅ ሶሾሎጅ ትምህርት ክፍል መምህር አቶ ደግ አረገ ዋለ "የሴቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት በምስራቅና ምዕራብ ጎጃም ዞን ተተኩሪነት" በሚል ርዕስ መነሻ ጽሁፍ አቅርበው የመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች ሀሳብና አስተያየት ሰጥተዋል፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የሴቶችና ወጣቶች እና ኤች አይቪ ኤድስ መከላከል ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላም መክብብ በበኩላቸው ሴቶችን እኩል ተሳታፊ ማድረግ ተገቢ እንደሆነ ገልፀው ፍትሃዊነት ላይ ጠንክሮ መስራትና ሴቶች በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ኋላ የሚቀሩባቸው ተፈጥሯዊም ሆነ ማህበረሰባዊ ችግሮች እንዳሉባቸውም አንስተዋል።

የደብረ ማርቆስ ከተማ ሲቢኤም ኢትዮጵያ ደርጅት ሃላፊ አቶ ገረመው አቅሌሳ እንደተናገሩት ድርጅታቸው በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ስራ ከጀመረ ጀምሮ ብዙ ስራዎችን ያከናወነ መሆኑን ጠቅሰው ዛሬ የሚከበረውን ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን (March-8) ምክንያት በማድረግ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ 3 ሴት ተማሪዎች ድርጅቱ የገንዘብ ሽልማት እንዳዘጋጀም ገልፀዋል ፡፡

በዚህም መሠረት፦
1ኛ. ከኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል ተማሪ ፋሲካ ካሳሁን 3.99 ውጤት በማምጣት 4200 ብር ፣
2ኛ. ከአካውንቲንግና ፋይናንስ ትምህርት ክፍል ተማሪ ትዕግስት ታረቀኝ 3.96 ውጤት በማምጣት 3700 ብር
3ኛ. ከኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል ተማሪ ስንዴ ክንዴ 3.92 ውጤት በማምጣት 3200 ብር ተሸልመዋል።

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ

=============

ለተጨማሪና አዳዲስ መረጃዎች


#ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu

#ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University

#ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q

#ዌብሳይት www.dmu.edu.et
1.6K views14:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-09 17:04:20
1.5K views14:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 21:49:56 ተማሪዎቻችን እንኳን ደህና መጣችሁ!

የአቅም ማሻሻያ ተጠቃሚ ተማሪዎች ወደ ግቢ በመግባት ላይ ይገኛሉ

============
ደብረ ማርቆስ ዩንቨርሲቲ | የካቲት 29/2015 ዓ.ም |ህዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት |
የትምህርት ሚኒስቴር በ2014 ዓ.ም የ12ኛ ከፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው ውጤታቸው ከግማሽ በታች የሆነባቸው ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ገብተው የአቅም ማሻሻያ/ ሪሚዲያል ተጠቀሚ እንዲሆኑ በወሰነው መሰረት ዩኒቨርሲቲያችን 3 ሺህ 91 ተማሪዎችን #በዋናው_ግቢ ፣ #በጤና እና #በቡሬ ካምፓሶች በመቀበል ላይ ይገኛል፡፡

የእነዚህ ተማሪዎች የመጨረሻ መግቢያ ቀን ነገ በ30/2015 ዓ.ም እንደሚጠናቀቅ የሬጂስትራር ዳይሬክቶሬት ቀደም ሲል ማሳወቁ ይታወቃል።

===========

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ

=============

ለተጨማሪ አዳዲስ መረጃዎች



#ዌብሳይት www.dmu.edu.et

#ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu

#ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University

#ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q
3.3K views18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 21:49:49
3.0K views18:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 21:34:08 በፈተና ንድፍ አዘገጃጀት (Test Blue Print Preparation ) ላይ ትኩረት ያደረገ ስልጠና ለመምህራን ተሰጠ

=================

ደብረ ማርቆስ ዩንቨርሲቲ | የካቲት 29/2015 ዓ.ም | ህዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት | በያዝነው አመት ለሁም የዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች የሚሠጠውን የመውጫ ፈተና ውጤታማ ለማድረግ ዩኒቨርሲቲያችን የተለያዩ ዝግጅቶችን በማድረግ ላይ ይገኛል።

በዛሬው ዕለም የፈተና ንድፍ አዘገጃጀት ላይ (Exam Blue Print Preparation) በተቋማዊ ጥራት ማረጋገጫ ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ለመምህራን ስልጠና ተሰጥቷል፡፡

በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚደንት ይሄይስ አረጉ (ዶ/ር) ምንም እንኳ በሀገራችን የተለያዩ ችግሮች ቢለዋወጡም ብቁ ትውልድ በማፍራት ታላቋን ኢትዮጵያ ለመፍጠር ሙያዊ ኃላፊነታችንን መወጣት አለብን ብለዋል፡፡

የተቋማዊ ጥራት ማረጋገጫ ዳይሬክተር አባትሁን አለኸኝ (ዶ/ር) የሚወጣው ፈተና መምህራን ከሚያስተምሩት የትምህርት ዓይነት ዓላማና ግብ ጋር መጣጣሙን ለመለካት የፈተና ንድፍ ማዘጋጀት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው መምህራን የሚመሩበትን የፈተና ንድፍ ማዘጋጀት እንዲችሉ በመጀመሪያ ስልጠና መስጠት አስፈላጊ እንደሆነ ገልፀዋል::

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ

=============

ለተጨማሪ አዳዲስ መረጃዎች


#ዌብሳይት www.dmu.edu.et

#ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu

#ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University

#ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q
3.0K viewsedited  18:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-08 21:33:58
2.7K views18:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-07 22:02:42 የመውጫ ፈተና (Exit Exam ) የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በተመለከተ ከትምህርት ሚኒስቴር ከመጡ የስራ ኃላፊዎች ጋር ወይይት ተካሄደ ተካሄደ

===================

ደብረ ማርቆስ ዩንቨርሲቲ | የካቲት 28/2015 ዓ.ም |ህዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት | በ2015 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና ውጤታማ ለማድረግ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ለተመራቂ ተማሪዎች በቂ ግንዛቤ ከመፍጠር ጀምሮ ግብዓቶችን እስከማሟላት ድረስ ሰፊ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡

በዛሬው ዕለትም ከትምህርት ሚኒስቴር የመጡ የስራ ኃላፊዎች አጠቃላይ ዝግጅቱ ምን እንደሚመስል ግምገማ አካሂደዋል፡፡ በትምህርት ሚኒስቴር የዩንቨርሲቲ ኢንዱስትሪ እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክተር አቶ ተሾመ ዳንኤል የመውጫ ፈተና የትምህርት ጥራት የሚለካበት ተማሪዎች ብቁና ተወዳዳሪ መሆናቸው የሚለይበት ዋነኛው መንገድ እንደሆነ በመግለፅ በዚህ ዓመት በዩንቨርሲቲዎችገልፀው የአይሲቲ መዋቅር ፣ ኤሌክትሪክሲቲ አቅርቦት ፣ ኢንተርኔት ፣ የሰው ኃይልና የተማሪዎች ዝግጅት በስፋት የሚሰራባቸው ጉዳዮች እንደሆኑ አንስተዋል፡፡

አያይዘውም በትምህርት ሚኒስትር በኩል በተለያዩ የመንግስትና የግል ሚዲያዎች ግንዛቤ የማስጨበጥ፣የህግ ማዕቀፍ (የአሰራር ስርዓት መመሪያ የማዘጋጀትና ለተመረጡ የትምህርት ዓይነቶች የፈተና ንድፍ አዘጋጅቶ ለዩንቨርሲቲዎች ተደራሽ የማድረግ ስራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል። በዩንቨርሲቲዎች የተደረጉ ዝግጅቶችን በመገምገም አስፈላጊ ድጋፎችን ለማድረግ በተለያዩ ዩንቨርሲቲዎች እየተዘዋወሩ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ታፈረ መላኩ (ዶ/ር) የመውጫ ፈተና የእውቀትና የክህሎት ክፍተቶችን ለመሙላትና በተቋማት በኩልም የተወዳዳሪነት መንፈስን ለመፍጠር በመሆኑ ትኩረት ሰጥተን እየሰራን ነው ብለዋል፡፡ ከግብዓት መሟላት አንፃር አንዳንድ ጉድለቶች እንዳሉ የገለፁት ፕሬዚደንቱ ተማሪዎችን ከማዘጋጀት አንፃር ከሰኔ 2014 ዓ.ም ጀምሮ በስነ ልቦናና በእውቀት ዝግጁ እንዲሆኑ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል። ለፈተናው መሟላት የሚገባቸው ቁሳቁሶች ተሟልተው በጥራት ለመስራት ትልቅ ወጭ ስለሚጠይቅ ትምህርት ሚኒስቴር የበጀት ሁኔታንም ትኩረት እንዲሰጠው አሳስበዋል፡፡

አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ይሄይስ ሐረጉ (ዶ/ር/ በበኩላቸው መውጫ ፈተና እንደሚሰጥ አቅጣጫ ከተቀመጠ ጀምሮ ተማሪዎችን በማነቃቃትና በማዘጋጀት ረገድ ኮሚቴ ተዋቅሮ እየተሰራ መሆኑንና መምህራን ተማሪዎችን ውጤታማ ለማድረግ ቲቶሪያል እየሰጡ እንደሚገኙ ገልፀዋል፡፡

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ

=============

ለተጨማሪ እና አዳዲስ መረጃዎች



#ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu

#ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University

#ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q

#ዌብሳይት www.dmu.edu.et
1.4K viewsedited  19:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ