Get Mystery Box with random crypto!

Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ D
የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
የሰርጥ አድራሻ: @debre_markos_university
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.90K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የቴሌግራም ገጽ ነው። የዩኒቨርሲቲያችን ወቅታዊ መረጃዎች፣ ልዩ ልዩ ሁነቶች እና የስራ እና የትምህርት ማስታወቂያዎች ይተላለፉበታል። አሁንኑ ቤተሰብ ለመሆን ይቀላቀሉ!!
This is Our Official Telegram Channel. We Provide up-to-date Information about our University.
Join Us Now!🙏

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2023-03-23 17:19:25
2.5K views14:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-23 17:19:08 ለመሆኑ የተማሪ አምባሳደርነት ምንድነው?

ለተጨማሪ አዳዲስ መረጃዎች

#ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University

#ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu

#ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q

#ዌብሳይት www.dmu.edu.et
2.5K views14:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-23 12:40:29 #ደረሰ ... !!#ደረሰ ... !! #ደረሰ ... !!



ውድ ተማሪዎቻችን እንኳን ደስ አላችሁ!!

በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በየዓመቱ የሚደረገው "የተማሪዎች አምባሳደርነት" እውቅናና ሽልማት መርሐ ግብር ደረሰ!!

በ2015 ዓ.ም ለሚደረገው 4ኛ ዙር የእውቅናና ሽልማት መርሐ ግብር የተመረጡ ተማሪዎች ከታች በፎቶ የተዘረዘሩት መሆናቸውን እየገለፅን የእውቅናና ሽልማት ፕሮግራሙ ቅዳሜ መጋቢት 16/2015 ዓ.ም በዋናው ግቢ ሐዲስ ዓለማየሁ የጉባዔ አዳራሽ እና እሁድ መጋቢት 17/2015 ዓ.ም በቡሬ ካምፓስ ከጥዋቱ 2:00 ጀምሮ እንደሚከናወን እናሳስባለን።

መምህራን፣ ተማሪዎች እና ሰራተኞች ሁላችሁም የመርሐ ግብሩ ታዳሚዎች እንድትሆኑ በአክብሮት ተጋብዛችኋል።

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ

==========

#ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University

#ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu

#ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q

#ዌብሳይት www.dmu.edu.et
858 viewsedited  09:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-23 12:40:27
848 views09:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-22 08:23:51 ለደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ እና አካባቢው ማህበረሰብ 97.7 ሬዲዮ ጣቢያ ጋዜጠኞች ስልጠና ተሰጠ

================
ደብረ ማርቆስ ዩንቨርሲቲ | መጋቢት 13/2015 ዓ.ም | ህዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት |
በስልጠናው የዩኒቨርሲቲያችን የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚደንት ይኸይስ አረጉ ዶ/ር የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲና አካባቢው ማህበረሰብ ኤፍ ኤም 97.7 ሬድዮ ጣቢያ የቦርድ አባላት በተገኙበት "FOJO" በተባለ የሚዲያ ተቋም ከመጋቢት 12 እና 13/2015 ዓ.ም ለሁለት ቀናት ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።

ስልጠናው ትኩረት ያደረገባቸው ርዕሰ ጎዳዮች *የማህበረሰብ ሬዲዮ እና ዘለቄታዊነት ፤
*የምርምራ ጋዜጠኝነት ምንነትና አተገባበር እና
የመጽሔት ፕሮግራም ቅጽ አዘገጃጀት የሚሉ ሲሆኑ
ስልጠናውን የሚሰጡትም W. Jacob Ntshangase, "Head Wits Radio Academy Wits center for Journalism እና ረዳት ፕሮፌሰር ዘላለም ተስፋዬ በባህርዳር ዩኒቨርስቲ የጋዜጠኝነት እና ተግባቦት ትምህርት ክፍል መምህር ናቸው።

የማህበረሰብ ሬድዮን ዘላቂ ለማድረግ የተነሱ ነጥቦች
*ጠንካራ አቅም ያለው አስተዳደር ማዋቀር፤
*የራሱን ገቢ እንዲያመነጭ ማስቻል፤
የማህበረሰብ የሬዲዮ ጣቢያን ሚናና ተግባር በግልጽ ለይቶ ማስቀመጥና የመሳሰሉት ሲሆኑ

የማህበረሰብ ሬድዪ ጣቢያ ዘላቂ እንዳይሆን የሚያደርጉ ተግዳሮቶች :-
* የጋዜጠኝነት ሙያ በትክክል አለመረዳት፤
*በሙያው በቂ የሆነ እውቀት እና ክዕሎት አለመኖር የሚሉት ነጥቦች ተጠቅሰዋል።

በሁለተኛው ርዕሰ ጉዳይ በምርመራ ጋዜጠኝነት ምንነትና አተገባበሩ ላይ የተነሱ ነጥቦች :-
*የምርመራ ጋዜጠኝነት ተግዳሮቶች፤
*የምርመራ ጋዜጠኝነት ደረጃዎች ፤
*በመርመራ ጋዜጠኝነት ዙርያ ለሚሰሩ ጋዜጠኞች ሊደረግ የሚገባ ጥበቃ እና ደህንነት ፤
*የምርመራ ጋዜጠኝነት መሰረታዊ ኳሊቲዎች፤
*የምርመራ ጋዜጠኝነት በኢትዮጵያ ያሉ ፈተናዎች፤
*የምርመራ ጋዜጠኝነት ሙያ ሊተገበሩ የሚገቡ ነገሮች የሚሉት አንኳር ጉዳዮች ተነስተዋል።

ስልጠናው ዛሬም የሬዲዮ መጽሔት ፕሮግራም ቅጽ አዘገጃጀት ላይ ትኩረት እንደሚያደርግም ተጠቁሟል።

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ

ለተጨማሪና ወቅታዊ መረጃዎች



https://t.me/Debre_Markos_University

https://www.facebook.com/dmu.edu

#ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q

#ዌብሳይት www.dmu.edu.et
2.2K views05:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-22 08:23:43
2.1K views05:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 19:16:05 ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትን ለማስፋት በህግ ተማሪዎች መካከል ትምህርታዊ ክርክር ተካሄደ

==================

ደብረ ማርቆስ ዩንቨርሲቲ | መጋቢት 09/2015 ዓ.ም | ህዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት |
| ደብረ ማርቆስ ዩንቨርሲቲ ህግ ት/ቤት ከኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ጋር በመተባበር ከኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ማዕከል፣ ከምስራቅ ጎጃም ዞን ፍትህ መምሪያ፣ ከከፍተኛ ፍ/ቤት የመጡ የስራ ኃላፊዎች ፣ የዩንቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና መምህራን እንዲሁም ተማሪዎች በተገኙበት የህዝብን ደህንነት ለማስጠበቅ የበይነ መረብ መዘጋት ተገቢ ነው? ወይስ አይደለም? በሚል በተማሪዎች መካከል ትምህርታዊ ክርክር ተካሂዷል፡፡

የደብረ ማርቆስ ዩንቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ይሄይስ አረጉ(ዶ/ር) ህግ ት/ቤት ትውልድን ከማነፅ አንፃር በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ እና አሁንም ለተማሪዎች የነፃ ሀሳብ መግለጫ መድረክ መመቻቸቱ ሀገራችን ካለችበት ሁኔታ አንፃር ወቅታዊ፣ ወሳኝና በሳል ሀሳብ መሆኑን ገልፀዋል፡፡

በዩንቨርሲቲው የህግ ት/ቤት ዲን መምህር አማረ ስጦታው በበኩላቸው ህግ ት/ቤት በትምህርት ጥራት፣በማህበረሰብ አገልግሎትና በምርምሩ ዘርፍ በርካታ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀው የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ከሚጠቀሙባቸውና ልምድ ከሚለዋወጡባቸው ፕሮግራሞች መካከልም ትምህርታዊ የክርክር መድረክ አንዱ መሆኑን አንስተዋል፡፡ በ2014 ዓ.ም የሰብአዊ መብቶች ክበብ ከተቋቋመ ጀምሮ ስልጠናዎችን በማመቻቸት፣ ማህበረሰቡ ለሰብአዊ መብቶች ያለው ግንዛቤ እንዲዳብርና ለሰብአዊ መብቶች መከበር የድርሻውን እንዲወጣ በትጋት እየሰሩ እንደሚገኙም ጠቅሰዋል፡፡

በኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች ማዕከል የሰብአዊ መብት ጥበቃና ምርምር ኦፊሰር አቶ ኖህ የሱፍ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል የሰው ልጅ መብቶች የማክበር ባህል እንዲዳብር በተለይም ወጣቶች የሌሎችን ሰብአዊ መብቶች በማክበር እንዲታነፁ ለማድረግ ስልጠና በመስጠትና ድጋፍ በማድረግ እስካሁን ከ10 በላይ በሚሆኑ ዩንቨርሲቲዎች ክበባትን በማቋቋም እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ ለተማሪዎች የክርክር መድረክ መፈጠሩም በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ግንዛቤ ለማስጨበጥ፣ ሀሳባቸውን በነፃነት የመግለፅ ክህሎታቸውን አዳብረው ፣ መብታቸውን አክብረው የሌሎችን መብት እንዲያስከብሩ እና በሀሳብ የበላይነት እንዲያምኑ ያስችላል ብለዋል፡፡

አያይዘውም ክበቡን ከማቋቋም ጀምሮ ለፕሮግራሙ መሳካት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የዩንቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች፣ለህግ ት/ቤት ዲንና መምህራን እንዲሁም ተማሪዎች ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

ክርክሩን ካካሄዱት ተማሪዎች መካከል የ4ኛ ዓመት የህግ ት/ቤት ተማሪ ያሬድ ሙሌ በዚህ ክርክር ላይ ስንሳተፍ በንድፈ ሃሳብ የምናውቀውን ትምህርት በተግባር ለማሳየት፣ የተለያዩ ጉዳዮችን በማንሳት ለማህበረሰቡ ግንዛቤ ለመፍጠር፣በራስ መተማመንን ለማዳበርና በትምህርት ህይወታችን በደንብ ታንፀን ስለምንወጣ ህጉን በትክክል ተግባራዊ ለማድረግ ያስችለናል ሲል ተናግሯል፡፡

ተማሪ ሀይማኖት ይበልጣል በበኩሏ ሀሳባችንን በታዳሚዎች ፊት በነፃነት ስንገልፅ የንግግር ክህሎታችንን ለማዳበርና የተለያዩ ጉዳዮችን ከተለያዩ ሀሳቦች አንፃር የመተንተን ክህሎታችንን እንድናዳብር ይረዳናል ብላለች፡፡

በክርክሩ የተሳተፉ ተማሪዎች ለወደፊት ቀጣይነት እንዲኖረዉና ሁሉንም ተማሪዎች ያሳተፈ ሊሆን እንደሚገባው አሳስበው ይህን መድረክ ላዘጋጁላቸው አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

በመጨረሻም ክበቡ ከተቋቋመ ጀምሮ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ 2 የህግ ት/ቤት መምህራን የክበቡ አባላት የሰዓት ሽልማት አበርክተዋል፡፡እንዲሁም የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ለፕሮግራሙ መሳካት የገንዘብ ድጋፍ በማድረግ እንድሁም ክርክሩን ለተሳተፉ 4 ተማሪዎች በአጠቃላይ የ10,000ብር የገንዘብ ሽልማት በማበርከት ፕሮግራሙ ተጠናቋል፡፡

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ

==========

ለተጨማሪና አዳዲስ መረጃዎች


#ቴሌግራም
https://t.me/Debre_Markos_University

#ፌስቡክ
https://www.facebook.com/dmu.edu

#ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q
1.6K views16:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 19:15:45
1.5K views16:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 19:15:41
1.5K views16:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-18 17:14:28
The Student Ambassador program aims to encourage and recognize students who have achieved academic excellence. To be considered for this prestigious honor, a student must have a minimum GPA of 3.75 and above.

Debre Markos University

Grow Wiser at the Water Tower!

===============

Join us


#facebook
https://www.facebook.com/dmu.edu

https://t.me/Debre_Markos_University

#Youtube https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q

#Website www.dmu.edu.et

#Twitter https://twitter.com/dmu_ethiopia

#Instagram https://www.instagram.com/dmu_ethiopia/

#LinkedIn https://www.linkedin.com/in/dmu-ethiopia/
2.1K views14:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ