Get Mystery Box with random crypto!

Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ D
የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
የሰርጥ አድራሻ: @debre_markos_university
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.90K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የቴሌግራም ገጽ ነው። የዩኒቨርሲቲያችን ወቅታዊ መረጃዎች፣ ልዩ ልዩ ሁነቶች እና የስራ እና የትምህርት ማስታወቂያዎች ይተላለፉበታል። አሁንኑ ቤተሰብ ለመሆን ይቀላቀሉ!!
This is Our Official Telegram Channel. We Provide up-to-date Information about our University.
Join Us Now!🙏

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 2

2023-07-02 14:22:05
4.7K views11:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-01 22:29:04
#አስደሳች_መረጃ !!

በቅድሚያ መምህር ካሳሁን ጀምበሩ እንኳን ደስ አለህ !!

በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የሜካኒካል ምህንድስና ትምህርት ክፍል መምህርና ተመራማሪ ካሳሁን ጀምበሩ (ረ/ፕሮፌሰር) የብሩህ ኢትዮጵያ 2015 የንግድ ፈጠራ ሀሳብ ውድድር ላይ በመሳተፍ አሸናፊ በመሆናቸው የ260 ሺህ ብር ተሸላሚ ሆነዋል።

መላው የዩኒቨርሲቲያችንማህበረሰብ እንኳን ደስ አላችሁ !!

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የእውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ!

==========
ለአዳዲስ መረጃዎች


#ቴሌግራም፡ https://bit.ly/3HbDPCB

# ፌስቡክ፡ https://bit.ly/3mYfnNW

#ዩቲዩብ፡ https://bit.ly/3L73hu3

#ድህረ ገጽ፡ www.dmu.edu.et
5.9K views19:29
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 17:09:04
#Announcement !
9.6K views14:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 16:17:29 Management members of Debre Markos University visited the College of Medicine and Health Sciences.

Debre Markos University | May 10/2023 G.C.|
| Directorate of Public Relations and Communication | Management members of Debre Markos University visited the campus of the College of Medicine and Health Sciences.

In the visit program, libraries, classrooms, laboratories including; Anatomy lab, Histology lab, Nursing lab, Demonstration rooms for Pediatrics, Health informatics store, Mid wifery, lab room, maternity and RH Class, human nutrition, student dining hall , they also visited the garden vegetables grown in the courtyard, cabbage, lettuce, red root, tomato, carrot, etc.



Debre Markos University

Grow Wiser at the Water Tower!

=============

Follow Us on


Telegram ፡ https://bit.ly/3HbDPCB

Facebook፡ https://bit.ly/3mYfnNW

YouToube፡ https://bit.ly/3L73hu3

Website: www.dmu.edu.et
3.6K viewsedited  13:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 16:17:16
3.3K views13:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-10 16:17:12
3.4K views13:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 18:08:09 ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ባሻገር የአካባቢውን ማህበረሰብ ችግር የሚፈቱ ፣ ለትውልድ የሚተላለፉ ፣ ሊታዩና ሊጨበጡ የሚችሉ የተለያዩ ማህበረሰብ አቀፍ ፕሮጅክቶችን እየሰራ እንደሚገኝ ተገለፀ

=========

ደብረ ማርቆስ ዩንቨርሲቲ ሚያዝያ 21/2015 ዓ.ም |ህዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት| ዩንቨርሲቲው ከመማር ማስተማሩ ስራ ባሻገር የማህበረሰቡን ችግሮች ሊፈቱ የሚችሉ ፕሮጀክቶች ላይም በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡

በዛሬው ዕለትም በሸበል በረንታ የተቀናጀ የማህበረሰብ አቀፍ ልማት ፕሮጀክት በተከናወኑ ተግባራት፣ ባጋጠሙ ችግሮች እና ወደ ፊት በሚከናወኑ እቅዶች ዙሪያ የዩኒቨርሲቲው የፕሮጀክቱ አባላት ፣ የአግሪሰርቪስ ኢትዮጵያ ሰራተኞች ፣ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮች ፣ ከጠቅላላ አገልግሎት ፣ከፋይናንስ ፣ከግዥናኦዲት ባለሙያዎች በተገኙበት የአንድ ዓመት የስራ እንቅስቃሴ ግምገማ ተካሂዷል ፡፡

የምርምርና ማህበረሰብ አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት አስካለማርያም አዳሙ (ዶ.ር ) እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ባሻገር የአካባቢውን ማህበረሰብ ችግር የሚፈቱ ፣ለትውልድ የሚተላለፉ፣ ሊታዩና ሊጨበጡ የሚችሉ የተለያዩ ማህበረሰብ አቀፍ ፕሮጅክቶችን እየሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

ከደብረ ማርቆስ ዩቨርሲቲ የፕሮጀክቱ አስተባባሪ መብራቴ በላቸው ( ዶ.ር ) ፕሮጀክቱ በ2015 ዓ.ም ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ዓመታት የሚተገበር እንደሆነ ጠቁመው የማህበረሰቡን ህይወት ማሻሻልና መቀየር ዓላማ እንዳደረገ ገልፀዋል፡፡ አያይዘውም ይህ ፕሮጀክት በሸበል በረንታ ወረዳ ዘጠኝ ቀበሌዎች እንደሚተገበርና ከዩኒቨርሲቲው ከምህንድስና ፣ ከግብርናና ተፈጥሮ ሃብት ፣ ከጤና ሳይንስ ፣ ከስነ - ባህሪ ተቋማትና ኮሌጆች የተውጣጡ ምሁራን እንደተሳፋበት ጨምረው ገልፀዋል ፡፡

በአግሪ ሰርቪስ ኢትዮጵያ የሚሰሩ ፕሮጀክቶች አስተባባሪ አቶ ተመስጌን ወንድይፍራው በበኩላቸው እንደገለፁት ፕሮጀክቱ የማህበረሰቡን ንቃተ ህሌና የሚያጎለብቱ የስልጠናና የምክክር መድረክ በማመቻቸት እና የምግብ ዋስትናን ለማስጠበቅ በተለያዩ የገቢ ማስገኛ ዘርፎች ተሳታፊ የሚያደርጉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆናቸውን ጠቅሰው ከእነዚህም ውስጥ በተፈጥሮ ሃብት ልማት ዘርፍ የተሸረሸሩና የተራቆቱ መሬቶችን መልሶ በማልማት የአፈር ለምነትን ማስጠበቅ ፤ የውሃ ፕሮጀክቶችን በተመለከተ ግድቦችን መስራት፣ ለወጣቱ የስራ ዕድል መፍጠር ፣ ጎጅ ልማዳዊ ድርጊቶችን በማስቀረት ዙሪያ የተከናወኑ መሆናቸውን ጨምረው አብራርተዋል፡፡

በፕሮጀክቱ በቀጥታ ተጠቃሚ የሚሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎችም በጠቅላላው 5 ሺህ ሰባት መቶ ቤተሰቦች እንደሆኑ የተገለፀ ሲሆን ከነዚህ ውስጥም 2 ሺህ አራት የሚሆኑት ሴቶች መሆናቸውን ገልፀዋል ፡፡

በስራው ሂደት ያጋጠሙ ችግሮችም በዝርዝር የተዳሰሱ ሲሆን የፕሮጀክቱ የስምምነት ሂደት መጓተት ፣ የአጋሮች አብሮ ለመስራት ቁርጠኛ አለመሆንና ወደ ተግባር አለመግባት፣ የግንባታ ቁሳቁሶች በቀላሉ አለማግኘት የሚሉትን ዋናዋና ችግሮች መሆናቸውን አንስተዋል ፡፡

በማጠቃለያ ፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው ሀሳባቸውን የሰጡት የዩኒቨርሲቲያችን ፕሬዚደንት ታፈረ መላኩ ( ዶ.ር ) የተሰሩት ስራዎች ጥሩና ለማህበረሰቡ እጅግ አስፈላጊ መሆናቸውን ገልፀው ይህ ውይይት የሚመለከታቸው አካላት በተገኙበት መካሄዱ ያለፈውን ሂደትና የመጣውን ውጤት አመዛዝኖ ለወደፊቱ ይበልጥ ለስራ መነሳሳትን ይፈጥራል ብለዋል ። በተጨማሪም የተሰጡ አስተያየቶችን ተቀብሎ በማሰተካከል እና ያጋጠሙ ችግሮችን በመፍታት ከዚህ የበለጠ መስራት ተገቢ መሆኑን አሳስበዋል ፡፡

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ!

=============

ለተጨማሪ እና አዳዲስ መረጃዎች


#ቴሌግራም፡ https://bit.ly/3HbDPCB

#ፌስቡክ፡ https://bit.ly/3mYfnNW

#ዩቱዩብ፡ https://bit.ly/3L73hu3

#ዌብሳይት www.dmu.edu.et
2.0K views15:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 18:08:04
2.0K views15:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 15:20:33 በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ሀገር አቀፍ የአምሳለ ችሎት ውድድር በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ተገለፀ

=============

ደብረ ማርቆስ ዩንቨርሲቲ | ሚያዚያ 21 /2015 ዓ.ም | ህዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት|
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በ2015 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የምስለ ችሎት ውድድር እንዲያካሂድ በመመረጡ በሀገሪቱ ካሉ 12 ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ ተወዳዳሪ ተማሪዎች ከሚያዝያ 20 ጀምሮ በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ በወድድሩ እተሳተፉ ይገኛሉ ፡፡


በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ህግ ትቤት ዲን አቶ አማረ ስጦታው ለተወዳዳሪዎች የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ካቀረቡ በኋላ የምስለ ፍ/ቤት ውድድር መካሄድ የተጀመረው በ2008 ዓ.ም ሲሆን በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ሲካሄድ ቆይቶ በ2015 ዓ.ም 7ኛው ዙር በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

ይህንን ዓይነት ውድድር ማካሄድ የትምህርት ጥራትን ማስጠበቂያ አንደኛው መንገድ ቢሆንም ከዚህ በተጨማሪ በሀገራችን ያሉ የተለያዩ ባህሎች ፣ አካባቢዎች፣ታሪካዊ ቦታዎችን እንድናውቅና እርስ በርስ እንድንተዋወቅ ሰፊ ዕድል እንደሚፈጥር የጠቆሙት አቶ አማረ ውድድሩ መሸናነፍን መሰረት ያደረገ ሳይሆን ወንድማማችነትንና አንዳችን ከአንዳችን የምንማማርበት እንደሚሆን ምኞታቸው መሆኑን ጨምረው ገልፀዋል፡፡

በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ.ር በለጠ ያዕቆብ እውነተኛ ፍትህን ለማስፈን በሙያው የተካኑ ፣ ቁርጠኛ ፣ሚዛናዊ ለእውነት ያደሩ ፣ ህሌናቸውን ዳኛ ያደረጉ ወጣቶች እንደሚያስፈልጉ ጠቅሰው እንደዚህ ዓይነት ዳኞችን ፣ ዐቃቢ ህጎችን፣ የፍትህ ሰዎችን ለማግኘት ደግሞ ይህን መሰል ሀገራዊ የውድድር መድረኮች እንደሚያስፈልጉ እና ይህን አጠናክሮ መቀጠል ተገቢ ነው ሱሉም አክለዋል፡፡

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ!

===========

ለተጨማሪ እና አዳዲስ መረጃዎች


#ቴሌግራም፡ https://bit.ly/3HbDPCB

#ፌስቡክ፡ https://bit.ly/3mYfnNW

#ዩቱዩብ፡ https://bit.ly/3L73hu3

#ዌብሳይት www.dmu.edu.et
2.6K views12:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-29 15:20:17
2.6K views12:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ