Get Mystery Box with random crypto!

Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ D
የቴሌግራም ቻናል አርማ debre_markos_university — Debre Markos University /ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ
የሰርጥ አድራሻ: @debre_markos_university
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 24.90K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የቴሌግራም ገጽ ነው። የዩኒቨርሲቲያችን ወቅታዊ መረጃዎች፣ ልዩ ልዩ ሁነቶች እና የስራ እና የትምህርት ማስታወቂያዎች ይተላለፉበታል። አሁንኑ ቤተሰብ ለመሆን ይቀላቀሉ!!
This is Our Official Telegram Channel. We Provide up-to-date Information about our University.
Join Us Now!🙏

Ratings & Reviews

4.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

2

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-03-03 12:27:13
1.4K views09:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 21:00:06 የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች ፣ወጣቶች እና ኤች.አይ.ቪ/ኤድስ ዳይሬክቶሬት ለሴት መምህራን ስለ ፕሮጀክት ቀረጻ አጻጻፍ ስልጠና ሰጠ

================

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ፥ የካቲት 22/2015 ዓ.ም ( ህዝብ ግንኙነትና ኮምንኬሽን ዳይሬክቶሬት ) በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች ፣ወጣቶች እና ኤች. አይ.ቪ /ኤድስ ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት በዩኒቨርሲቲው በማስተማር ላይ ለሚገኙ 30 ሴት መምህራን ስለ ፕሮጀክት ቀረጻና አጻጻፍ የካቲት 21 ና 22/2015 ዓ.ም ለሁለት ተከታታይ ቀናት ስልጠና ተሰጧል ፡፡

በስልጠና ፕሮግራሙ ላይ ተገኝተው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ዶ/ር ይኸይስ አረጉ እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው እንዲህ ያሉ ስልጠናዎች ለሴት ምህራን ሲሰጥ የቆየ ቢሆንም ተግባር ላይ ከማዋል አንጻር ግን ውስንነት እንዳለ ጠቁመው ሴትነት አሸናፊነት ነው ፤ ሴትነት ጀግንነት ነው ፤ ሴትነት ታላቅነት ነው ፤ ሴትነት ስኬት ነው ፤ ሴትነት ውጤታማነትና መሪነት ነው ፤ ስለዚህ ይህን ስልጠና በአግባቡ በመከታተልና ወደ ተግባር በመግባት ተጨባጭ ለውጥ ለማምጣት ራሳችውን ማዘጋጀት እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል ፡፡


የስልጠናውን ዓላማ በተመለከተ ሀሳባቸውን የሰጡት በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የፕሮጀክት ቀረጻ ትብብር ዳይሬክቶሬት ዶ/ር አበበ በላይና በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ግብርናና ተፈጥሮ ሃብት መምህር ዶ/ር አማረ ተስፋው የፕሮጀክት ቀረጻና አጻጻፍ ፡- ዓለማቀፍ ፕሮጀክቶችን እንዴት ማሸነፍ እንደሚቻል ፣ አንድ ፕሮጀክት ምን ምን ነገሮችን ማሟላት እንዳለበት ፣ ፕሮጀክቱን ለማሸነፍ የትኞቹ አጋር አካላት መካተት እንዳለባቸው ግንዛቤ ለማስጨበጥና ተነሳሽነት በመፍጠር እንስት መምህራን ወደ ፕሮጀክት ቀረጻ ስራ እንዲገቡ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልፀዋል ፡፡


በስልጠና መረሃ ግብሩ ላይ ሲሳተፉ ያገኘናቸው በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የባዮ ቴክኖሎጂ ትምህርት ክፍል መምህርት ብርቱካን ሲሳይና በግብርናና ተፈጥሮ ሃብት ኮሌጅ የዕጽዋት ሳይንስ ትምህርት ክፍል መምህርት አለምነሽ እስከዚያ እንደገለጹት ይህ ስልጠና በጣም አስፈላጊና በጉጉት ሲጠብቁት እንደነበር ጠቁመው ከስልጠናውም ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ ማህበረሰብን ተጠቃሚ ለማድረግ የሚያስችል ግንዛቤ ማግኘታቸውን ገልፀዋል።

ከተለያዬ የሙያ መስክ መሰባሰባቸው ደግሞ መረጃ ለመለዋወጥ ፣ልምድ ለመካፈልና በጋራ ለመስራት ዕድል እንደፈጠረላቸውም ጨምረው ተናግረዋል።

ከዚህ ስልጠና በኋላም በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ሀገሮች ፕሮጀክቶች ላይ ለመሳተፍና ፕሮጀክቶችን ለማዘጋጀት ከፍተኛ ተነሳሽነት ተፈጥሮብናል በማለት ገልፀዋል። በመጨረሻም ይህን ስልጠና ላመቻቸላቸው ለደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ሴቶች፣ ወጣቶች፣እና ኤች.አይ.ቪ /ኤድስ ዳይሬክቶሬት ምስጋና አቅርበዋል ፡፡

=============
ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ


ለተጨማሪ መረጃዎች



#ዌብሳይት www.dmu.edu.et

#ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu

#ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University

#ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q
1.7K views18:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 20:59:51
1.6K views17:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 19:22:31 ለአዲስም ሆነ ለነባር መምህራን አጫጭር የሙያ ላይ ስልጠናዎች በየጊዜው ቢሰጡ ብቁ ዜጋ ለማፍራት እንደሚያስችል መምህራን ገለፁ

ደብረ ማርቆስ ዩንቨርሲቲ፡- የካቲት 22/2015 ዓ.ም (ህዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት) ዩንቨርሲቲው በመምህርነት ሙያ ሳይመረቁ ወደ መምህርነት ሙያ ለሚሰማሩ አዲስ ለተቀጠሩና በዝውውር ለመጡ መምህራን አጫጭር የሙያ ላይ ሥልጠናዎችን ሰጥቷል፡፡

አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ይኼይስ አረጉ (ዶ/ር) የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በመጀመሪያ ባለሙያዎችን ማብቃት ወሳኝ በመሆኑ አጫጭር ስልጠናዎችን መስጠት አስፈላጊ መሆኑን ገልፀው የማስተማር ሙያ ሣይንስን መግለፅ፣ ብቃትን ማሳየትና ልምድን ማካፈል በመሆኑ ዕውቀት በወረቀት ተጀምሮ በወረቀት የሚያልቅ ሳይሆን ህይወታችንን የሚነካና ተግባር ላይ የሚውል መሆን እንዳለበት ጠቁመዋል፡፡ መምህራን ትውልድ የመቅረፅ ትልቅ አደራ ስላለባቸው ኃላፊነታቸውን ባግባቡ መወጣት እንደሚገባቸውም አሳስበዋል፡፡

የስልጠናው ተሳታፊ መምህር በዕውቀቱ አየለ የሙያ ላይ ስልጠናው መሰጠቱ እንዳስደሰታቸውና ሰው ሙሉ ስላልሆነ በየጊዜው ተከታታይ ስልጠናዎች ቢሰጡ የተሻለ ትውልድ ለመቅረፅ እንደሚያስችላቸው ገልፀዋል፡፡

ሌላው አስተያየታቸውን የሰጡን መምህር ዮሀንስ መንግስት ከዚህ በፊት የመምህርነት ሙያን ባለመሰልጠናቸውና ለሙያው አዲስ በመሆናቸው ወደ ስራ ለመግባት ተቸግረው እንደነበርና ስልጠናው በመሰጠቱ ክፍተታቸውን እንደሞላላቸው አንስተዋል፡፡
ይህንን ስልጠና ላመቻቸላቸው ዩንቨርሲቲውና ስልጠናውን ለሰጡት መምህራንም ምስጋናቸውን አቅርበው ከስልጠናው በተጨማሪ የማስተማርያ ግብዓቶች እንዲሟሉላቸው አሳስበዋል፡፡

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ

ለተጨማሪ መረጃዎች



#ዌብሳይት www.dmu.edu.et

#ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu

#ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University

#ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q
2.1K viewsedited  16:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 19:22:20
1.9K views16:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 19:17:01 ለአዲስ ገቢ መደበኛ ተማሪዎች አጠቃላይ ገለፃ ተሰጠ

ደብረ ማርቆስ ዩንቨርሲቲ ፡- የካቲት 22/2015 ዓ.ም (ህዝብ ግንኙነትና ኮምኒኬሽን ዳይሬክቶሬት) በ2015 ዓ.ም በተሰጠው የ12ኛ ክፍል ፈተና ከ50% በላይ በማስመዝግብ ዩንቨርሲቲያችንን መርጠው ለገቡ አዲስ መደበኛ ተማሪዎች ስለመማር ማስተማሩ፣በዩንቨርሲቲው ውስጥ ስለሚያገኟቸው አገልግሎቶች፣ ማክበር ስለሚገባቸው ህግና ደንቦች በሚመለከት የአካዳሚክ አመራሮች ዝርዝር ገለፃ ተሰጠ፡፡

በዩንቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮች ኤክስክዩቲቭ ዳይሬክተር በለጠ ያዕቆብ (ዶ/ር) ተማሪዎችን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት በዩንቨርሲቲ ቆይታቸው በስነምግባር የታነፁ፣ ጠንካራና ለዓላማቸው ቁርጠኛ በመሆን ለስኬት መብቃት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡በተጨማሪም የተቋሙን ህገ ደንብ በማክበር፣ ተቻችለው፣ተከባብረውና ተረዳድተው መኖር እንዳለባቸው ጠቁመው መልካም የትምህርት ዘመን እንዲሆንላቸው ተመኝተዋል፡፡

የተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት ተማሪ ጌጤነህ ሸገን እስካሁን በዩንቨርሲቲ ቆይታው ስለዩንቨርሲቲው፣ስለመምህራንና አካባቢው ማህበረሰብ የተመለከተውን ምስክርነት በመስጠት የተማሪዎች ህብረት ስለሚያከናውናቸው ተግባራትና አዲስ ተማሪዎችን ለማብቃት እገዛ እንደሚያደርጉ ተናግሯል፡፡

የአስተዳደርና ተማሪዎች ጉዳይ ኤክስክዩቲቭ ዳይሬክተር ጥላሁን ድረስ ( ረ/ፕሮፌሰር ) በበኩላቸው በዩንቨርሲቲ ውስጥ ትምህርት ብቻ ሳይሆን መልካም ስነምግባርም ወሳኝነት እንዳለው ገልፀው ስለሚያገኟቸው አገልግሎቶችና ማክበር ስላለባቸው ግዴታዎች ዝርዝር ማብራሪያዎችን ሰጥተዋል፡፡ ባጠቃላይ ከተማሪዎች ጋር በስፋት የሚገናኙ የስራክፍሎች ሁሉም የየራሳቸውን ገለፃ አድርገዋል፡፡

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ

የዕውቀት አውድማ ከጮቄ ማማ

ለተጨማሪ መረጃዎች



#ዌብሳይት www.dmu.edu.et

#ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu

#ቴሌግራም https://t.me/Debre_Markos_University

#ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q
1.8K views16:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 19:16:42
1.8K views16:16
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 12:10:06
#የሐዘን-መግለጫ
2.0K views09:10
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 10:49:50
ለተጨማሪ መረጃዎች ከታች የተቀመጡትን ማስፈንጠሪያዎች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ!

ዌብሳይት www.dmu.edu.et

#ቴሌግራም
https://t.me/Debre_Markos_University

#ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu

#ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q
2.4K views07:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-03-01 08:43:59 ታሪክ ለመስራት ምንም የሚያግደን ነገር የለም ፤ ታሪክ መስራት ከአባቶቻችን የወረስነው ተፈጥሯዊ ፀጋችን ነው" ( ዶ/ር ይኸይስ አረጉ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚደንት)

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ፦ ( ህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት)

የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ህዝባዊ ተሳትፎ አስተባባሪ ብሔራዊ ም/ቤት ጽ/ቤት እና የኢትዮጵያ ታሪክ ባህል ቅርስ አድን ድርጅት በጋራ የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች፣ መምህራን እና ሰራተኞች በተገኙበት ታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን በተመለከተ ህዝባዊ የንቅናቄ መድረክ ተካሄደ ።

የመድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚደንት ዶ/ር ይኸይስ ሀረጉ ሲሆኑ በንግግራቸውም
"ታሪክ ለመስራት ምንም የሚያግደን ነገር የለም ታሪክ መስራት ከአባቶቻችን የወረስነው ተፈጥሯዊ ጸጋችን ነው ፤ ዛሬም ወደ ፊትም ታሪክ እየሰራን እንቀጥላለን" ሲሉ ገልፀዋል።

አባቶቻችን የአድዋ ድልን በማስመዝገብ ፣ የአክሱም ሃውልትን በማቆም ፣ የላሊበላ ውቅር አቢያተ ክርስቲያናትን በማነጽ እና ሌሎችንም አስደናቂ የታሪክ ቱርፋቶችን ሰርተውልን አልፈዋል።

ታላቁ የህዳሴ ግድብ ደግሞ የነገው ትውልድ እኛን የሚያከብርበት ፣ የሚዘክርበት እና ልማት የሚረጋጥበት የዚህ ትውልድ አሻራ ነው የሚል እምነት እንዳላቸው ጠቁመዋል።

ይህንን የንቅናቄ ጉዞም እንደ ተቋም በአድናቆት እንደሚንቀበሉት እና የሚጠበቅባቸውን ሁሉ እንደሚያደርጉም ቃል ገብተዋል፡፡

ኢንጅነር ነጮ ወርቁ የኢትዮጵያ ታሪክ ባህል ቅርስ አድን ድርጅት ፕሮጀክት ማናጀር እና የጉዞው አስተባባሪ እንደገለፁት የኢትዮጵያ ታሪክ ባህል ቅርጽ አድን በጎ አድራጎት ድርጅት ከታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ጋር በታላቁ ህዳሴ ግድብ ዙሪያ ህዝባዊ ንቅናቄን በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በመንቀሳቀስ ቅስቀሳዎችን በማድረግ ፣ የህዳሴ ግድቡ ግንባታ የደረሰበትን ደረጃ መረጃ የመስጠትና ገቢም የማሰባሰብ ተግባር እንደሚያከናውን ጠቁመዋል።

በመሆኑም የተጀመረውን ለመጨርስ እና ግንባታውን ለማፋጠን ኢትዮጵያውያን እንደዚህ ቀደሙ በቦንድ ግዥ አና "በ8100A" አስተዋፅኦ እንዲያበረክት ጥሪ አቅርበዋል፡፡
==========
ለተጨማሪ መረጃዎች ከታች የተቀመጡትን ማስፈንጠሪያዎች በመጫን ቤተሰብ ይሁኑ!

ዌብሳይት www.dmu.edu.et

#ቴሌግራም
https://t.me/Debre_Markos_University

#ፌስቡክ https://www.facebook.com/dmu.edu

#ዩቱዩብ https://www.youtube.com/channel/UCqQDHEyYDen3aybySpYsF_Q
2.5K views05:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ