Get Mystery Box with random crypto!

Amhara Sport

የቴሌግራም ቻናል አርማ amharasport — Amhara Sport A
የቴሌግራም ቻናል አርማ amharasport — Amhara Sport
የሰርጥ አድራሻ: @amharasport
ምድቦች: ስፖርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 16.27K
የሰርጥ መግለጫ

የሚዲያ ሽፋን የተነፈገውን የኢትዮጵያ ስፖርት ለማሳደግ ከሰፈር እስከ ጠፈር በትኩረት እንዘግባለን !!

Ratings & Reviews

2.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 23

2022-07-10 20:47:23
የአጥቂው ምንይሉ ወንድሙ ቀጣይ ማረፊያ ?

መከላከያ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ የተጨዋቹን ፊርማ ለማግኘት ተፋጠዋል።ወላይታ ድቻ ውሉን ለማራዘም ድርድር ጀምሯል፣እስካሁን ግን ስምምነት ላይ አልደረሱም።

የቀድሞው የባህርዳር ከነማ ፣ መከላከያ ፣ መቀሌ 70 እንደርታና ወላይታ ድቻ አጥቂ የነበረው ምንይሉ ወንድሙ ከወላይታ ድቻ ጋር የነበረው ኮንትራት መጠናቀቁን ተከትሎ የበርካታ ክለቦች አይን ማረፊያ ሁኗል።

በአሰልጣኝ ፋሲል ተካልኝ የሚመራው መከላከያ እና የክፍሌ ቦልተና ኢትዮ ኤሌክትሪክ አጥቂውን ምንይሉ ወንድሙ የክለባቸው የመጀመሪያ አዲስ ፈራሚ ለማድረግ ጥረት እያደረጉ ነው።

ወላይታ ድቻዎች በበኩላቸው አሁንም የአጥቂያቸውን ኮንትራት ለማራዘም ድርድር መጀመራቸው እርግጥ ሁኗል ።

በወላይታ ድቻ የነበረውን ኮንትራት ያጠናቀቀው አጥቂ ምንይሉ ወንድሙ ቀጣይ ማረፊያ መከላከያ ፣ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ወይስ ወላይታ ድቻ የሚለው ከወዲሁ ተጠባቂ ሁኗል።

የአጥቂው ቀጣይ ማረፊያ የቀድሞ ክለቡ መከላከያ ሊሆን እንደሚችል የበርካቶች ግምት ሁኗል።

ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ገፃችን ይቀላቀሉ
https://t.me/AmharaSport

@AmharaSport
3.4K views17:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 17:40:35
ከድር ኩሊባሊ ከአፄዎቹ ጋር ይቆያል !!

የአፄዎቹ አምበል ያሬድ ባየ ወደ ባህርዳር ከነማ ማቅናቱን ተከትሎ አጣማሪው ከድር ኩሊባሊም እንደሚያመራ ተደርጎ የሚሰራጨው መረጃ መሰረተ ቢስ ነው።

ባለፈው አመት ከድር ኩሊባሊ በአፄዎቹ ቤት ሁለት ዓመት የሚያቆየውን ኮንትራት መፈረሙ የሚታወስ ሲሆን ተጨዋቹ አሁን ላይ ከፋሲል ከነማ ጋር የሚያቆየው የአንድ ዓመት ውል ይቀረዋል።ይሄን ተከትሎ ተጨዋቹ ወደየትኛውም ክለብ የሚሄድበት ዕድል የለም።

የጣናው ሞገዶች የኩሊባሊ ፈላጊ መሆናቸው እርግጥ ቢሆንም በመጪው ዓመት የአስቻለው ታመነ አጣማሪ ሆኖ በአፄዎቹ ቤት ይቆያል።

ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ገፃችን ይቀላቀሉ
https://t.me/AmharaSport

@AmharaSport
3.5K viewsedited  14:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-10 11:22:30
ባህርዳር ከነማ ያሬድ ባዮን አስፈረመ

የፋሲል ከነማው አምበል ያሬድ ባየ በይፋ የጣናው ሞገድ ባህርዳር ከነማ የመጀመሪያ አዲስ ፈራሚ ሆኖ ሞገዶቹን ተቀላቅሏል።

የአፄዎቹና የዋሊያዎቹ ግዙፉ ተከላካይ ያሬድ ባየ በፋሲል ከነማ ቤት ለመቆየት ውሉን እንደሚያራዝም ሲጠበቅ ውሃ ሰማያዊውን ባህርዳር ከነማ በይፋ ተቀላቅሏል።

ባህርዳር ከነማዎች የቀድሞውን የአፄዎቹን አምበል ያሬድ ባየን በሁለት አመት ኮንትራት ውል የዝውውር መስኮቱ የመጀመሪያ አዲስ ፈራሚ በማድረግ የተከላካይ ክፍላቸውን የበለጠ ያጠናከሩበትን ምርጥ ዝውውር አጠናቀዋል ።

በበርካታ የአፄዎቹ ደጋፊዎች ተወዳጅ የሆነው ያሬድ ባየ ወደ ባህርዳር ከነማ ማምራቱ ለፋሲላውያን አስደንጋጭ ዜና ቢሆንም በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ላለመውረድ ለተጫዎቱት የጣና ሞገዶቹ ደጋፊዎች ልብን በደስታ የሚያሞቅ የዝውውር መረጃ ነው።

ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ገፃችን ይቀላቀሉ
https://t.me/AmharaSport


@AmharaSport
4.4K views08:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 22:05:08
ኢትዮጵያ ቡና ሁለት ተጫዋቾችን አስፈርሟል

የውድድር አመቱን በ42 ነጥቦች 6ኛ ደረጃን ይዘው ያጠናቀቁት ቡናማዎቹ በዝውውር መስኮቱ የመጀመሪያ ቀን ሁለት ተጫዋቾችን ከሰበታ ከተማ ማስፈረማቸውን ይፋ አድርገዋል ።

ሁለቱ ተጫዋቾች በሰበታ ከተማ መልካም እንቅስቃሴ ሲያደርጉ የነበሩት የግራ መስመር ተከላካዩ ኃይለሚካኤል አደፍርስ እና አማካኙ አብዱልሀፊዝ ቶፊቅ ሲሆኑ በቡናማዎቹ ቤት ለሶስት አመታት የሚያቆያቸውን ኮንትራት ፈርመዋል ።

ኃይለሚካኤል አደፍርስ ከ2011 ጀምሮ እከተጠናቀቀው የውድድር አመት መጨረሻ ድረስ በሰበታ ከተማ መጫወት የቻለ ሲሆን በተለያዩ የዕድሜ ዕርከኖች እና በዋናው ብሄራዊ ቡድንም መመረጥ ችሎ ነበር ። ተጫዋቹ በውድድር አመቱ 25 ጨዋታዎችን አድርጎ አንድ ግብ ማስቆጠር ችሏል ።

አብዱልሀፊዝ ቶፊቅ በደደቢት የታዳጊ ቡድኖች እና ዋናው ቡድን ተጫውቶ በ2013 ዓ.ም ሰበታ ከተማን መቀላቀል ችሏል ። በክለቡም ጥሩ ሁለት አመታትን ማሳለፍ የቻለ ሲሆን በ2013 ባህርዳር ላይ ተዘጋጅቶ በነበረው የሴካፋ ውድድር ላይ የብሔራዊ ቡድኑ አባል ነበር ። ተጫዋቹ በውድድር አመቱ በሰበታ ከተማ 26 ጨዋታዎችን በማድረግ አንድ ግብ ማስቆጠር ችሏል።

Hatrick Sport

ቴሌግራም https://t.me/AmharaSport
4.2K views19:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 21:51:14
የተረጋገጠ !!

ባህርዳር ከነማ እና ፋሲል ከነማ የአሰልጣኝ ለውጥ አያደርጉም።

ባህርዳር ከነማ ከአሰልጣኝ አብረሃም መብራቱ ጋር የሚቀጥል መሆኑንና ለአሰልጣኙ የክለቡ ቦርደሰ እንዳረጋገጡለት አማራ ስፖርት ከታማኝ ምንጭ አረጋግጧል።

ፋሲሎች ከኢትዮጵያ ቡና ጋር መለያየቱ እርግጥ ከሆነው አሰልጣኝ ካሳየ አራጌ ጋር ንግግር መጀመራቸው እየተነገረ ቢሆንም መረጃው ትክክል አለመሆኑንና ፋሲል ከነማ
በአሰልጣኝ ኃይሉ ነጋሺ (ቲጋና) ጋር እንደሚቀጥል የክለቡ የቦርድ አባል አረጋግጠውልናል።

የቴሌግራም ገፃችን ይቀላቀሉ !!

https://t.me/+Tzw0up1zbYUolfG8

@AmharaSport
4.3K views18:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-09 12:04:20 https://t.me/+Tzw0up1zbYUolfG8
4.6K views09:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 21:32:50
ፋሲል ከነማ ለኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሎግ አ.ማ ደብዳቤ ፅፏል።
10.0K views18:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 21:31:51
ፋሲል ከነማ ከሜዳ ምደባ ጋር ተያይዞ ቅሬታዉን አቅርቧል !!

የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ2014 የዉድድር ዘመን ሊገባደድ የቀናት እድሜ ብቻ እንደቀሩት ይታወሳል። ከዚህ ጋር ተያይዞ የ30ኛ ሳምንት ጨዋታዎችን በተለይ የዋንጫ ባለቤቱን እና ቀሪ ወራጅ የሆነዉ ቡድን ለመለየት ሳኝነት ያላቸውን ጨዋታዎች በተመሳሳይ ሰዓት በሶስት ስታዲየሞች ለማካሄድ የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አክሲዮን ማህበር ፕሮግራም ማዉጣቱ ይታወሳል። በዚህም ክለቦች ጨዋታዎቻቸውን እንዲያካሂዱ የተመደበላቸው ስታዲየም አግባብነት የጎደለዉ ስለመሆኑ እና አክሲዮን ማህበሩ በዚህ ጉዳይ ማብራሪያ እንዲሰጥ ሲሉ ጠይቀዋል። ሙሉ ደብዳቤው ከታች በምስሉ ተያይዟል።
8.6K views18:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 15:03:57
የዛሬዉ ጨዋታ የጎሎቹ ባለቤቶች !

* ሁለገቡ ተጫዋች ሙጅብ ቃሲም በፊት መስመር አጥቂነት በተሰለፈባቸዉ ሶስት ጨዋታዎች 5ኛ ግቡን ማስቆጠር ችሏል።

* አማካዩ ሱራፌል ዳኛቸዉ ደግሞ ከሁለት አመታት በኋላ በዛሬዉ ዕለት ኳስ እና መረብን ማገናኘት ችሏል።

@Alphasportet
7.7K viewsedited  12:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 14:57:42
ተጠናቀቀ | ፋሲል ከነማ 3 - 0 ኢትዮጵያ ቡና

ሙጂብ ቃሲም
ሱራፌል ዳኛቸው

√ አፄዎች የቅዱስ ጊዮርጊስ ጨዋታ ውጤት እስኪታወቅ ድረስ የሊጉን መሪነት ተረክበዋል ።

@Alphasportet
6.8K views11:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ