Get Mystery Box with random crypto!

ዘሪሁን ገሠሠ

የቴሌግራም ቻናል አርማ zerihunkocha — ዘሪሁን ገሠሠ
የቴሌግራም ቻናል አርማ zerihunkocha — ዘሪሁን ገሠሠ
የሰርጥ አድራሻ: @zerihunkocha
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 13.77K
የሰርጥ መግለጫ

በመረጃ እንቀራረብ! በመረጃ እንተሳሰር!

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 41

2022-10-08 18:23:19
ለአብይ አህመድና ለሽመልስ አብዲሳ  የምስጋናና የውዳሴ ስነ-ስርአት አዘጋጅተው ፦

<< እናንት ወንድሞቻችን ሆይ! እንቅፋት እንዳይመታን የምትጠብቁን ፥ በፍርሀታችን የማታስጠቁን ፥ እስከአፍንጫችን የምታስታጥቁን ፥ በመላው ኦሮሚያ እየተስፋፋን ነውና ጭፍጨፋችንን አጠናክረን እንድንቀጥል ፥ የእናንተ መኖር ዋስትናችን ነው፡፡  ትእዛዛዝና አላማችንን  በሚገባ ለመፈፀም ፥  የጎደለን ድሮንና ታንክ ነውና እሱንም እንደምታሟሉልን ተስፋ እናደርጋለን! እናንተ የእኛ እኛም የእናንተ ነንና! በዋና ማዘዣ ጣቢያችን  ፣ በአራት ኪሎ  ቤተ-መንግስት ረዥም እድሜ ሰጥቷችሁ እስከዘላለሙ ኑሩልን! ገለቶማ >>

የሚሉ ነውኮ የሚመስሉት!
2.7K views15:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 17:34:08
ክቡር የሆነውን የሠው ልጅ ከነህይወቱ ቤት ዘግተው የሚያቃጥሉ አውሬዎች መኪና ቢያቃጥሉ ላይገርም ይችላል!
2.8K views14:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-08 16:50:25
በገዛ ሀገሩ ባይተዋር የሆነው አማራ.....!

ይህ ከወለጋ ሰሞኑን ከሞት ለማምለጥ ለቆ በመውጣት ላይ ያለ ወገንህ ነው!
2.9K views13:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 20:36:12 በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን አመያ ወረዳ የሚገኙ ነዋሪዎች ከፍተኛ የህልውና ስጋት ውስጥ መውደቃቸውን ገለፁ!

ሙሉ ወለጋን ጧት ማታ በንፁሃን ደም የሚያጥበው አሸባሪው ኦነግ ፥ ከወለጋ አልፎ በተለያዩ ጊዜያት ጥቃት ካደረሰባቸው ብሎም ግልፅ በሚባል ደረጃ ታጣቂዎችን ከሚመለምልባቸው አካባቢዎች መካከል የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ግንባር ቀደም ተጠቃሹ ነው፡፡

ይህ ጨፍጫፊ ቡድን ከሰሞኑ ያስመረቃቸውን ጨምሮ እጅግ በርካታ ቁጥር ያላቸው ጨፍጫፊዎቹን ከወለጋ አጓጉዞ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን አመያ ወረዳ ዳሊ-ዳክ የተባለ ቀበሌ ላይ በሚገኝ ጫካ አስፍሮ እንደሚገኝ ነዋሪዎቹ ገልፀዋል፡፡

ለጨፍጫፊው ቡድን ከአካባቢው ተመልምለው አብረው የመጡ የቡድኑ አባላት "አወጡት" በተባለውና በአካባቢው ነዋሪዎች ለጥንቃቄ በተላለፈው መልዕክት መሠረት ፦ ቡድኑ በቀጣይ ቀናት ፥ በርካታ ቁጥር ያላቸው የአማራ ብሄር ተወላጆች የሚኖሩበትን አመያ ወረዳ በማፅዳት ፥ በአበሽጌ ወረዳ በሚገኘው ጊቤ በረሀ ጫካ አልፎ የሽብር ተግባሩን ወደደቡብ ክልል የማስፋፋት ተልእኮ ተሰጥቶት ወደስፍራው እንደመጣ ተገልፇል፡፡

"መንግስት ከዚህ ቀደም የተፈፀሙ ጥቃቶችንና ግድያዎችን ከመፈፀማቸው በፊት የድረሱልን ጥሪ ብናስተላልፍም በዳተኝነት ከፍተኛ ዋጋ አስከፍሎናል" የሚሉት የአካባቢው ነዋሪዎች ፥ አሁንም የከፋ ፍጅት ከመፈፀሙ በፊት በስፍራው የፀጥታ አካላትን በበቂ ሁኔታ አሰማርቶ ዜጎችን የመጠበቅ ሀላፊነቱን እንዲወጣ አሳስበዋል !

#ሼር በማድረግ መረጃውን ተደራሽ ያድርጉ!
2.2K views17:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 19:46:45
ቅምጥሉ የቤት ልጅ ፥ ህፃናትና ሴቶችን የሚያርደው አረመኔውና ፈሪው ኦነግ ፥ መኪና ፥ አምቡላንስ ፣ ፋብሪካ ፥ ...ወዘተ እንደዳመራ አቃጥሎ እየሞቀ ፥ "አያና መስቀላ በጋ ጌሴኒ!" ይባባልሃል!
2.4K views16:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-07 17:12:45
ፕሬዝደንት ኡህሩ ኬኒያታ - በደቡብ አፍሪካ ሊደረግ ከነበረው የትህነግና የመንግሥት አደራዳሪነት ራሳቸውን ማግለላቸው ታውቋል፡፡ በሌላ ዜና ድርድሩም "በሎጂስቲክ አለመሟላት " በሚል ሰበብ መቅረቱ ተነግሯል!

ከዚህ በፊት በነበሩት የድርድር ሂደቶች ፥ ነፍሰበላዋ ትህነግ " ወደ ዝርዝር የድርድር ሂደት ከመግባታችን በፊት 'አሸባሪ' ብሎ የሰየመኝ ፓርላማ በይፋ ይቅርታ ጠይቆ ውሳኔውን ይሻር!" የምትለው ነገር " የብብቴን ፀጉር አበጥሩልኝ!" ከማለት አይተናነስም!

በነገራችን ላይ አሸባሪው ትህነግ ከነሀሴ 24/2014 ዓ.ም በኃላ በነበሩት ጊዜያት እንኳ በአሜሪካ አዛዥነት ሮቢላ ተልኮላቸው ፈልሰስ ብለው ጅቡቲ ላይ ተደራድረው ነበር! "ተኩስ አቁም ተስማምተናል!" እስከማለትም ደርሰው ነበር!

በርግጥ ጦርነት እየተካሄደ እንኳ "ድርድር" መደረጉ ያለ ፣ የነበረና የሚኖርም ነው፡፡ ነገርግን በየትኛውም አለም ከአሸባሪዎች ጋር ሀገረ-መንግስታዊና አለማቀፋዊ እውቅና የተሰጠው ድርድር ተደርጎ አያውቅም ፥ አይደረግም ፥ ሊደረግም አይገባም!

ሲቀጥል የዚች ሀገር የመከራና ስቃይ ጠንሳሹ ነፍሰበላ ከሀዲ ቡድን ፥ ከነአስተሳሰቡ ተቀብሮ ፥ አርማ ምልክቱን መጠቀም በህግ የሚያስጠይቅበት ዘመን እስካልመጣ ድረስ ፥ ኢትዮጵያ ረፍት አልባ ሆና ትቀጥላለች! በተለይም የአማራ ህዝብ " ከአጋም እንደተጠጋ ቁልቋል" ሆኖ መቀጠሉ ሳይታለም የተፈታ ነው! ስለዚህ አጋሙን ነቅሎና መንጥሮ መጣል ብቸኛው መፍትሔ ነው!

ድርድር አጋሙ እሾሆቹን ለማሳደግ የሚጠቀመው ጊዜ የመግዣ ስልት ብቻ ነው!

PP ግን ለህዝብ ቀርቶ ለራሱም የማይታመን ስለሆነ ምናልባት ከነቃ ፥ ህዝቡ ይንቃ!
977 views14:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-06 18:54:07 ስለምን "ሀገር የመሆን" ጉዳይ ሲነሳ ፥ ከአማራ ብሔርተኛ ነኝ ባዩ ውስጥ ሳይቀር "ብርድ ብርድ ፥ ፍረሀት ፍረት" የሚለው ሀይል እንመለከታለን ?

ይህ የብሔርተኝነት ፅንሰ ሀሳብን በሚገባ ካለመረዳት የሚመነጭ ችግር ነው!

ብዙ ጊዜ " የአማራ ብሔርተኝነት የሀሳብ ጥራት ችግር አለበት!" እላለሁ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ አብዘሀኛው ብሔርተኛ ሀይል ብቻውን ተቀምጦ " ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ" እያለ ሲያጨበጭብ ፥ ሀገር የተዋቀረችበት አማራ ጠል ከሆነ ትርክት የተወለደው የፅንፈኞች ብሔርተኝነት ፥ አድጎና ጎልምሶ ብሎም መንግስታዊ ስልጣን ጭምር ይዞ ፥ ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ሊያጠፋው ከጫፍ ሲደርስና የተጋረጠበት የህልውና አደጋ አፍጥጦ ሲመጣበት ፥ ግልፅና የጠራ የሀሳብ መስመር ሳያበጅ ፥ "በእውር ድንብርብር ራሱን ለማዳን ተገዶ የገባበት የማታገያ ስልት" ስለሆነ ብቻ ነው፡፡

ከሁለተኛው የአለም ጦርነት በኃላ ብሔርተኝነት/nationalism የፖለቲካ ማደራጃ ሆኖ መስፋፋት ከመጀመሩ ጋር ተያይዞ በርካታ አዳዲስ ሀገራት ተወልደዋል፡፡ የብሔርተኝነት ፈርጆች በርካታ ቢሆኑም ፥ በማንኛውም አይነት የብሔርተኝነት እንቅስቃሴ ፥ ፖለቲካዊ ትግል የጀመረ "የጋራ ማንነት ወይም መገለጫ አለኝ" ብሎ የተደራጀ የፖለቲካ ማህበረሰብ ፥ የትግሉ ማጠንጠኛዎች ፦ ከማንኛውም ውጫዊ ሀይል ጣልቃ ገብነት ነፃ መሆንን ፥ ራስን በራስ የማስተዳደርና የራስ አስተዳደራዊ ግዛት (ሀገር) መፍጠርን ፥ …ሊያልፋቸው የማይችሉ ግልፅ መስፈርቶቹ አድርጎ ነው፡፡

ከዚህ አኳያ ማንኛውም የአማራ ብሔርተኛ " የአማራ ድንበሩ/ወሰኑ የት ነው?" ሲባል በቀጥታ የሚመልሰው መልስ ሊኖረው ግድ ይላል፡፡ ቅዠትም በሉት ህልም ይህን ጥያቄ የኦሮሞ አለያም የትግራይ ብሔርተኞችን ስጠይቋቸው ያለማመንታት የሚመልሱት ፖለቲካዊ መልስ አላቸው፡፡ የአማራን ብሔርተኛ ስጠይቁት ደግሞ " የአማራ ድንበሩ ኢትዮጵያ ናት!" የሚል ረብ የለሽና እንደውም ፅንፈኞቹ "አሀዳዊያን ፥ ደፍጣጭ ፣ …ወዘተ" እያሉ ለሚከሱት ክስ ዋቢ የሚሆን መልስ ይመልሱልሀል፡፡

ይህ የብሔርተኝነቱ የሀሳብ ጥራት/ideal clarity ችግር የወለደው ነው፡፡ ይህ የአማራን ህዝብ ስርአታዊና መዋቅራዊ በሆነ መልኩ መከራ እያዘነበበት ያለው የሴራ ፌደራሊዝም ስርአት በዚሁ ከቀጠለና የአማራ ህዝብ የሚዘንብበት የመከራ ዶፍ "ሀገር አልባ" እስከማስባል በደረሰ ደረጃ እያዋረደው ከቀጠለ ፥ የአማራ ህዝብ መደራደሪያ የሚሆነው አለያም የመጨረሻ ውሳኔ የሚወስንበት ሁለተኛ አማራጩ "ሀገር" መሆን ነው፡፡

ይህን አስገዳጅ መስፈርት ሳያሰምሩ ልፍስፍስና ደካማ የብሔርተኝነት እንቅስቃሴ ማድረጉ ከጥቅሙ ጉዳቱ የሚያመዝንና የመከራውን ዶፍ አባብሶ የሚያስቀጥል ይሆናል፡፡

እናም ኢትዮጵያ አማራው የግፍ ዶፍ ተሸክሞ እየተጨፈጨፈ ካለቀ በኃላ የሚወርሳት ጀነት ወይም መንግስተ ሰማያት አለመሆኗን የምታረጋግጥበት የሀሳብ መስመር ማስመር ግዴታ እንጂ ውዴታ አይደለም!

ይህ ከኢትዮጵያዊነት ማፈንገጥ ወይም ፅንፈኛ የመሆን አለያም የመጥበብ ጉዳይ ሳይሆን በማንኛውም አማራጭ የሀገር ባለቤትነትን የማረጋገጫ መሠረታዊ የፖለቲካ ነጥብ ነው!

ይኸው ነው!
1.4K views15:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 17:05:23
ትህነግን ማመን ወይም ለትህነግ መዘናጋት ከመቃብሩ ላይ ቆመህ ነው!

ለተደጋጋሚ ወረራ የተዳረገው ህዝባችን ፣ የደረሰበትን ሁለንተናዊ ስብራት መጠገን ቢከብድም ቢያንስ እነዚያ አስከፊ ጭፍሮች ከፊቱ ገለል ብለውለት ያለስጋት ወጥቶ መግባቱም ትልቅ እፎይታ ነው!

ነገርግን  ዜናውን በመልካምነቱ ከመቀበል ባሻገር አንዳች የሚያስደልቀንና የሚያስፎክረን ጉዳይ አይኖርም! ይሄ የቤቱ ጣራ ሳይቀር እየተነቀለ የተዘረፈበትና ራቅቱን የቀረ ህዝብ ፥ ሀዘኑንም ስቃዩንም የኢኮኖሚና የስነ-ልቦና ስብራቱንም መጠገን የሚቻለው "ትህነግ" የተባለ ቡድን ከነአስተሳሰቡ ጭምር እስከወዲያኛው ሲቀበር ብቻ ነው!

አሁን ያለው ነባራዊ ሁኔታም ፥ እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ ትህነግን ዋጃ ላይ ጥምር ጦሩን ቆቦ ላይ አስቀምጦ ማዶ ለማዶ እየተያዩ "ህዝቡን መጡ ሄዱ ፥ ጀመሩ አልጀመሩ" በሚል ስጋት ውስጥ እንዲቀጥል ከሆነ ፥ የትናንትናው የትህነግ ለቆ መውጣትን ሌላ ትርጓሜ እንዲይዝ ያደርገዋል!
2.6K views14:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-03 13:55:01
የአምናው ጭፍጨፋ

"…እኒህ የምታዩዋቸው ቤተሰቦች እዚያው ምዕራብ ወለጋ ሆሮ ጉዱሩ ጃርዴጋ ጃርቲ ወረዳ ኮቲቻ ቀበሌ ይኖሩ የነበሩ ዐማሮች ነበሩ። ከቀን ጎዶሎ ቀን የኦነግ ታጣቂዎች በኮቲቻ ቀበሌ ገብተው ለወራት ምልክት ሲያደርጉባቸው በከረሙት የዐማራ ቤቶችን በድንገት ወርረው ተቆጣጠሩ። ታህሳስ 18/2014 ዓም።

"…ከወረራው በፊት የዞኑ አስተዳደር ከሚኒሻዎቹ እጅ የሚገኘውን መሳሪያ በሙሉ ነጠቀ። መከላከያውም አካባቢውን ለቆ እንዲሄድ ተደረገ። የኦሮሚያ ልዩ ኃይልም ድራሹ ጠፋ። የአካባቢው ኦሮሞዎችም ሰፈሩን ለቀው እንዲሄዱ ተደረገ። እናም ዐማራ አፅጂው ማሽን ያለምንም ከልካይ ገባ። ወሮ ፍሬህይወትም በፍጥነት ስልክና ኢንተርኔቱን ከአዲስ አበባ ዘጋች።

"…ከዚያማ ምኑ ይጠየቃል። ኦነግ ጠያቂ፣ ጠበቃ፣ አጋዥ በሌለው የምስኪን ዐማራ ገበሬ ቤተሰብ ላይ ዘመተ። ጭለማ ስለሆነ ከቤቱ የወጣ የለም። ቀን ከአፈር ጋር ሲታገል የዋሉትም፣ ሁላቸውም ደክሟቸው በጎጆአቸው ተሰብስበዋል። ቆይቶ ቀበሌዋ በተኩስ ተናወጠች። ተኳሾቹም እዚህ ቤት ሰብረው ገቡ። እንደገቡም የተኙ ህጻናትን በተኙበት። የነቁትን በተቀመጡበት ረሸኗቸው። በዚህም መሰረት እኒህ ከዚህ በታች በስም የተዘረዘሩት የ አንድ ቤተሰብ አባላት በሙሉ ለዘር ሳያስቀሩ ፈጇቸው። ሟች ታራጆቹም።

1 ይብሬ አድማሱ (አባት)
2 በለጠች ጎባው (ሚስት)
3 ሃሚድ  ይብሬ (ልጅ)
4 መካ ይብሬ (ልጅ)
5 ፋጡማ ይብሬ (ልጅ)
6  አህመድ ይብሬ (ልጅ) 
7 ሙሳ አድማሱ የይብሬ  አድማሱ  ወንድም ነው። ሃሚድ ይብሬ በጨለማው ኩራዝ እያጠና ነበር። እዚያው ተስፋው ላይ ነው ያለርህራሄ የረሸኑት።

"…እነሆ በዓመቱ እዚያው ሆሮ ጉዱሩ ጃርዴጋ ጃርቲ ሰሞኑን ከ200 በላይ ዐማሮች በዚህ መልክ ተጨፍጭፈዋል!

@ዘመድኩን በቀለ

"…ነፍስ ይማር…!!
7.1K views10:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-10-02 20:14:54
አሽከርነትና አጋርነት!

" አሽከርነት አጋርነት አይደለም! " - የሱፍ ኢብራሒም

አስተማማኝ ወገንና ተገን የሌለው እንዲሁም ራሱን ችሎ የማይቆም፤ በፖለቲካ አሰላለፍ ውስጥ የራሱ ፍላጎት፣ ግብ እና ሚና የሌለው፤ አዳሩን እና ተስፋውን በተመን ያስተላለፈ አካል ከተደራጁ ኃይሎች ጋር የሚያደርገው ግንኙነት— አጋርነት ሳይሆን አሽከርነት ነው!

የአቻነት፣ የነፃነትና የትብብር ግምት የማይወሰድበትና የአንድ አቅጣጫ የድጋፍ ፍሰት ያለበት አጋርነት ሳይሆን አሽከርነት ነው። ለአሽከር የሚታሰብ ክፍያ ወይም ዳረጎት የአጋርነት ማስረጃ አይሆንም!
-
በነገራችን ላይ ወገኑን ከድቶ ለአሳዳሪ የሚገባ አሽከር ክፉ እንደሚሆን ይታወቃል! ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በወገኖቻችን ላይ የሚፈፀመውን ግፍና ጭፍጨፋ ከመካድ አልፈው ተጎጅዎችን ለመወንጀል የተሰለፉ አካላት ለዚህ ማሳያ ይሆናሉ።

ምናልባት ዛሬ ለአሳዳሪ ሃሳብ፣ የልብ ትርታና እስትንፋስ ሲባል ዘወትር ወገናቸውን የሚዘልፉና የሚቧጭሩ አካላት ነገ አንገታቸውን ቀና አድርገው ለመሄድ እንደማይችሉ መገንዘብ ይኖርባቸዋል!

አሽከርነት አጋርነት አይደለም!
2.7K views17:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ