Get Mystery Box with random crypto!

YeneTube

የሰርጥ አድራሻ: @yenetube
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 125.42K
የሰርጥ መግለጫ

መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 15

2024-03-06 12:00:27
የ 7000 ብር ሽልማት እርስዎን ይጠብቃል!
አሁኑኑ በ7868 ላይ OK ብለው በመመዝገብ የጠቅላላ እውቀት ውድድር ላይ ተሳታፊ ይሁኑ፣ ይወዳደሩ፣ ይሸለሙ!

አሁኑኑ ይመዝገቡ
Click 7868 OK
14.1K views09:00
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-05 21:59:02
ቴሌግራም በሰዓታት ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አዳዲስ ተጠቃሚዎች አገኘ።

ዓለም ላይ ለሰዓታት ፌስቡክ እና ኢንስታግራም መቋረጣቸውን ተከትሎ " ቴሌግራም "ን በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች መቀላቀላቸውን የቴሌግራም መስራች እና ዋና ስራ አስፈፃሚ ፓቨል ዱሮቭ ገለጹ።

ዋና ስራ አስፈፃሚው ፤ " ኢንስታግራም እና ፌስቡክ በተቋረጡበት ባለፉት ሰአታት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች ቴሌግራም ላይ ሲመዘገቡ እና ይዘቶችን ሲያጋሩ ቆይተዋል " ብለዋል።

" ቴሌግራም " ከእነዚህ አገልግሎቶች የበለጠ አስተማማኝ ነው ሲሉም አክለዋል።

" ምንም እንኳን ከሜታ አንድ ሺህ ጊዜ ያነሱ ቋሚ የሆኑ ሰራተኞች ቢኖሩንም በመተግበሪያው ላይ አዳዲስ ይዘቶችን ለማሻሻል እና አዳዲስ ፈጠራዎችን ለማከል ፈጣኖች ነን " ብለዋል።

ዋና ስራ አስፈፃሚው ፤ " በ2023 ሙሉ ከዓመቱ 525,600 ደቂቃዎች ውስጥ የቴሌግራምን አገልግሎት ማግኘት ያልተቻለው በአጠቃላይ ለ9 ደቂቃ ብቻ ነው " ያሉ ሲሆን " ይህም 99.999983% ቴሌግራም ስራ ላይ እንደነበር አመላካች ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
15.5K views18:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-04 18:09:35
የቢጂአይ-ኢትዮጵያ ዋና መሥሪያቤት ህንፃ ሽያጭ ተቋረጠ።

ቢጂአይ-ኢትዮጵያ እና በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ትሬዲንግ አ/ማ መካከል ሲካሄድ የቆየው ድርድር የሽያጭ ውል ለማሰር ባለመቻሉ ሂደቱ መቋረጡን ቢጂአይ-ኢትዮጵያ ገልጿል።

ቢጂአይ-ኢትዮጵያ የሽያጭ ውል በተዋዋይ ወገኖች መካከል እንዲኖር እና የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጩ እውን እንዲሆን ያላሰለሰ ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን የገለፀ ሲሆን " በፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ ትሬዲንግ አ/ማ በኩል ግብይቱን ለማጠናቀቅ እና የሽያጭ ውሉን ለመፈረም ፍላጎት እና ቁርጠኝነት ባለመኖሩ ምክንያት የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጭ ሂደቱን ለማቋረጥ ተገደናል። " ሲል አሳውቋል።

" ስለዚህም በተዋዋይ ወገኖቹ ቀድም ሲል በተፈረመው የቀብድ ውል ውስጥ በተገለጹት ድንጋጌዎች መሠረት የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ሽያጩ በይፋ ተቋርጧል " ብሏል።

ቀደም ብሎ ፐርፐዝ ብላክ ኢትዮጵያ በሜክሲኮ የሚገኘውንና የቢጂአይ ኢትዮጵያ ለረዥም ጊዜ ዋና መሥሪያ ቤት አድርጎ ሲጠቀምበት የነበረውን ሥፍራ ለመግዛት መስማማታቸውን ከሁለቱም ወገን መገለጹ ይታወሳል።

@Yenetube @Fikerassefa
14.0K viewsedited  15:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-03 16:49:09
#ሰበር #BreakingNews
'ዝክረ አድዋ' ዝግጅት እንዳይካሄድ ተከለከለ

እሁድ የካቲት 24 ቀን 2016 (አዲስ ማለዳ)ወደዛሬ የተዘዋወረው ዓመታዊው 'ዝክረ አድዋ' ዝግጅት እስካሁን ባልታወቀ ምክንያት እንዳይካሄድ ተከለከለ።

ሀሙስ የካቲት 21 ቀን 2016 በብሔራዊ ቴያትር ሊካሄድ የነበረው የዝክረ አድዋ ዝግጅት ወደ ዛሬ የካቲት 24 ቀን 2016 ተዘዋውሮ የነበረ ቢሆንም በዛሬው ዕለት እንዳይካሄድ ተከልክሏል።

ዝግጅቱ በቅድሚያ ከታሰበበት ብሔራዊ ቴያትር ወደ ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል ተቀይሮ የነበረ ሲሆን አዲስ ማለዳ በስፍራው ተገኝታ ነበር።

አዲስ ማለዳ እንደተመለከተችው የጸጥታ አካላት በቦታው በመገኘት ዝግጅቱን ለመታደም የተሰበሰቡ ሰዎችን በትነዋል።

በዚህም በዕለቱ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች እና ታዳምያን እንዲመለሱ እየተደረጉ ይገኛል።

እንዲሁም በስፍራው ተዘጋጅተው የነበሩ ባንዲራዎች እንዲወርዱ መደረጉንም አዲስ ማለዳ ተረድታለች።

ሆኖም ግን ዝግጅቱ እንዳይደረግ የተከለከለው "በምን ምክንያት እንደሆነ" ይህ ዘገባ እስከሚወጣ ድረስ የተገለፀ ነገር የለም።

በአብርሃም ግዛው መዝናኛና የሚዲያ ስራዎች ድርጅት ባዘጋጀው መድረክ የጥበብ ሰዎች፣ የሃይማኖት አስተማሪዎች፣ ምሁራን እና ሌሎችም የተጋበዙበትና ሥራዎቻቸውን የሚያቀርቡቡት መድረክ እንደሚሆን ተጠብቆ ነበር።

@Yenetube @Fikerassefa
17.3K views13:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-02 10:47:19
የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ የመከላከያ ሚንስትር ዶ/ር አብረሀም በላይ ፣የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዝዳንቶች ሌ/ጄኔራል ታደሰ ወረዳ እና ሌ/ጄኔራል ፃድቃን ገ/ትንሳኤ እንዲሁም የህወሓት ሊቀመንበሩ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በተገኙበት 128ኛ አመት የዓድዋ ድል በአል በዓድዋ እየተከበረ ነው።

በበአሉ ላይ ከተለያዩ የትግራይ አካባቢዎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ የዓድዋ እና አካባቢው ነዋሪዎችም ተገኝተዋል።

@Yenetube @Fikerassefa
14.2K views07:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-02 09:36:02
መልካም በዓል ይሁንሎ።

በዓሉ የህዝብ ነበር
13.9K viewsedited  06:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-02 08:45:36
128ኛ የዐድዋ ድል በአዲስ አበባ እየተከበረ ሲሆን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩ ነህ በፖሊስ ማርች ታጅበው በአፄ ምኒሊክ ሀውልት ስር ጉንጉን አበባ አኑረዋል።

በዓድዋ ድል መታሰቢያም ልዩ ልዩ ፕሮግራሞች እየተከናወኑ ይገኛሉ።
13.1K views05:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-01 19:05:55
በጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ተከስቷል በተባለ የኮሌራ በሽታ ከአራት መቶ የማያንሱ ተማሪዎች መያዛቸውን በዩኒቨርሲቲው ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎች ተናገሩ።

ከተከሰተ አንድ ሳምንት ግድም ሆኖታል ስለተባለው ኮሌራም ሆነ በበሽታው ሳቢያ ስለደረሰ ጉዳት ከዩኒቨርሲቲውም ሆነ ከክልሉ ጤና ቢሮ ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ ባለመሳካቱ ሀሳባቸውን ማካተት አልተቻለም።ይሁን እንጂ አስተያየት የሰጡ ተማሪዎች በበሽታው ተይዘው ህክምና ሲደረግላቸው ነበሩ ከተባሉ መካከል አንዳንዶቹ እያገገሙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በዩኒቨርሲቲው ተከሰተ ስለተባለው ወረርሽኝ ለተማሪዎች በይፋ የተገለጸ ነገር የለም ። ይሁንና የበሽታዉ መንስኤ በአንድ በኩል "በውኃ ብክለት" በሌላ በኩል "የግል ንፅህና ባለመጠበቅ" የመጣ ነው የሚል አስተያየቶች ተሰምተዋል።በዚህም ምክንያት ተማሪዎች ወደ መመገቢያ አዳራሾች ሲገቡ ለጥንቃቄ እንዲታጠቡ ሲደረግ ነበር ተብሏል።

ከተከሰተ አንድ ሳምንት ግድም ሆኖታል ስለተባለው ኮሌራም ሆነ በበሽታው ሳቢያ ስለደረሰ ጉዳት ከዩኒቨርሲቲውም ሆነ ከክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት ይህ ዘገባ እስከተጠናከረበት ሰዓት የሞባይል ስልክ ባለመነሳቱ እና ባለመስራቱ ሳቢያ ሀሳባቸውን ማካተት አልተቻለም።በሶማሌ ክልል መቀመጫ ጅግጅጋ ከተማ የሚገኘው ይኸው ዩኒቨርሲቲ ከቀናት በኃላ የተማሪዎች ምረቃ መርሀ ግብር ያከናዉናል ተብሎ ይጠበቃል።

Via DW
@YeneTube @FikerAssefa
14.3K views16:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-01 17:41:10 የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሶማሊያ የአየር ክልል በኩል መብረር አቆመ!

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ እስያ አገራት ለሚያደርጋቸው በረራዎች ይጠቀምበት በነበረው የሶማሊያ የአየር ክልል በኩል መብረር ማቆሙን አስታወቀ።አየር መንገዱ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው ከሶማሊያ የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች “አስተማማኝ የአየር ትራፊክ አገልግሎት” ባለማግኘቱ እንደሆነ ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን ጣሰው ለቢቢሲ አማርኛ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ እስያ ለሚደርጋቸው በረራዎች “ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ” ይጠቀምበት በነበረው የሶማሊያ አየር ክልል መብረር ያቆመው፤ የአየር መንገዱ አውሮፕላን ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ የካቲት 16/2016 ዓ.ም. በአገሪቱ የአየር ክልል ውስጥ ካጋጠመው ክስተት ጋር በተያያዘ መሆኑን አቶ መስፍን አስታውሰዋል።

ኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን፤ “በዓለም አቀፍ አሠራር መሠረት እንደዚህ ዓይነት ነገር ሲያጋጥም ለሚመለከታቸው የሲቪል አቪየሽን ባለሥልጣናት ሪፖርት እናደርጋለን። [የቅዳሜውን ክስተት በተመለከተም] ለሶማሊያ እና ለኢትዮጵያ የሲቪል አቪየሽን ባለሥልጣናት ሪፖርት ተደርጓል” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል። ይሁንና እስካሁን ድረስ በጉዳዩ ላይ የተሰጠ ምላሽ አለመኖሩን አክለዋል።የቅዳሜ ዕለቱ ክስተት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሶማሊያ አየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች የሚሰጠውን አገልግሎት “አስተማማኝ ሆኖ እንዳያገኘው” ማድረጉን አቶ መስፍን ገልጸዋል።

በዚህም ምክንያት ይህ ክስተት ካጋጠመበት ማግስት እሁድ የካቲት 17/2016 ዓ.ም. አንስቶ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሶማሊያን አየር ክልል መጠቀም ለማቆም መወሰኑን አስታውቀዋል።አቶ መስፍን፤ ከክስተቱ በኋላ ካለው ቀን አንስቶ “አማራጭ ለመጠቀም ወስነናል። ለዚህም ዋናው ምክንያት [የቅዳሜ ዕለቱ ክስተት] ነው። እዚያ በነበረው ሁኔታ፤ የአየር ክልሉ አስተማማኝ የአየር ትራፊክ አገልግሎት ስላላገኘንበት ለደኅንነት ስንል አማራጭ መንገዶች እየተጠቀምን ነው” ሲሉ የአየር መንገዱን ውሳኔ አብራርተዋል።

አየር መንገዱ ወደ እስያ ለሚያደርጋቸው በረራዎች የሚጠቀመው የሶማሊያን የአየር ክልል እንደነበር ያስታወሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ በአሁኑ ሰዓት እነዚህ በራረዎች የሚደረጉት በጂቡቲ አየር ክልል በኩል መሆኑን ገልጸዋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ የጂቡቲን የአየር ክልል እየተጠቀመ ያለው “ተጨማሪ ወጪ በማያመጣ መልኩ” እንደሆነም አክለዋል።የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሌለሎች አገራት ለሚደረጉ በራረዎች የሶማሊያን አየር ክልል መጠቀም ቢያቆምም ወደ ሞቃዲሾ እና ወደ የሶማሊላንድ ዋና ከተማ ሀርጌሳ ከተማዎች የሚያደርጋቸውን በራረዎች “ያለ ችግር” መቀጠሉን አብራርተዋል።

Via BBC
@YeneTube @FikerAssefa
13.9K views14:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-01 17:21:27
ከፈረንሳዊው ጋዜጠኛ ጋር በታሰሩት የኦነግ የፖለቲካ ኦፊሰር ላይ አምስት ተጨማሪ የምርመራ ቀናት በፍርድ ቤት ተፈቀደ!

ከፈረንሳዊው ጋዜጠኛ አንቷን ጋሊንዶ ጋር አብረው የታሰሩት፤ ፖለቲከኛው አቶ በቴ ኡርጌሳ ላይ ፍርድ ቤት ተጨማሪ አምስት የምርመራ ቀናት ፈቀደ። የአዲስ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ቀናቱን የፈቀደው፤ ፖሊስ “የተጠርጣሪውን ስልክ ምርመራ ውጤት ለመቀበል” ተጨማሪ ጊዜ እንዲሰጠው ያቀረበውን ማመልከቻ በመቀበል ነው።

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ኦፊሰር የሆኑት አቶ በቴ፤ “አፍሪካ ኢንተለጀንስ” ለተሰኘው የዜና ድረ ገጽ ዘጋቢ ከሆነው አንቷን ጋር በቁጥጥር ስር የዋሉት ባለፈው ሳምንት ሐሙስ የካቲት 14፤ 2016 ነበር። የኦነጉ ፖለቲከኛ እና ፈረንሳዊው ጋዜጠኛ በአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት ባለፈው ቅዳሜ በቀረቡበት ወቅት፤ ፖሊስ “ከፋኖ እና ከኦነግ ሸኔ ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሁከት ለማስነሳት በመሞከር” እንደጠረጠራቸው መግለጹ ይታወሳል።

የአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት አስቀድሞ በሰጠው ቀጠሮ መሰረት የተጠርጣሪዎቹን ጉዳይ መመልከት ሲጀምር፤ ቅድሚያ የማስረዳት ዕድሉን የሰጠው ለመርማሪ ፖሊስ ነው። ፖሊስ በተሰጡት ስድስት ቀናት፤ የአንድ ሰው ቃል መቀበሉን እና የተጠርጣሪዎችን የሞባይል ስልክ ለማስመርመር ወደ ፌደራል ፖሊስ መላኩን አስረድቷል። ሆኖም የስልክ ምርመራ ውጤቱን ተቀብሎ ከምርመራ መዝገቡ ጋር ማያያዝ እንደሚቀረው ገልጿል።

Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
13.1K views14:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ