Get Mystery Box with random crypto!

YeneTube

የቴሌግራም ቻናል አርማ yenetube — YeneTube
ርዕሶች ከሰርጥ:
Whatsapp
የሰርጥ አድራሻ: @yenetube
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 123.08K
የሰርጥ መግለጫ

መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 16

2024-04-13 23:23:23
ሰላም፣ ቆንጆ ፉድስ ነን!

የኢትዮጲያ ባህላዊ ምግቦች በሚገባቸው ክብር እና ደረጃ በማቀናበር ለሀገር ውስጥ እና ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ቆርጠን ተነስተናል። እርስዎም ይህንን መጠይቅ በመሙላት የሚወዷቸውን ኢትዮጲያዊ ጣዕሞችን በመላው በዓለም ያገኟቸው ዘንድ የበኩልዎን አስተዋፅዎ እንዲወጡ በታላቅ አክብሮት እንጠይቃለን።

ለሚያደርጉት አስተዋፅዎ ያዘጋጀነውን የምስጋና ሽልማት ለመቀበል ስልክ ቁጥሮን መተው እዳይረሱ፣ እናመሰግናለን።

የሚከተለውን ሊንክ በመጫን ወደ ፎርሙ ይግቡ
https://forms.gle/dZ9qwg2L3bJsX9NR7
12.7K views20:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 20:50:00
በዛሬው ዕለት ከ1 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ከሳውዲ አረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ!

በ3ኛው ምዕራፍ ዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ በሳኡዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ የሚገኙ ዜጎችን ወደ ሀገራቸው የመመለስ ስራ እየተከናወነ ሲሆን፤ በዛሬው ዕለትም በሶስት ዙር በረራ 1 ሺህ 71 ኢትዮጵያውያንን ወደ ሀገራቸው መመለስ ተችሏል።

በዛሬው እለት ወደ ሀገር የተመለሱት 1 ሺህ 71 ዜጎች ሁሉም ወንዶች ሲሆኑ ዘጠኙ እድሜያቸው ከአስራ ስምንት አመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች ናቸው ተብሏል።

ለተመላሽ ዜጎች በአየር ማረፊያና በማቆያ ማዕከላት ተገቢውን ድጋፍ እና እንክብካቤ በማድረግ ከቤተሰብ ጋር የመቀላቀል ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

@YeneTube @FikerAssefa
14.0K views17:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 20:48:31
ለድርጅትዎ የGOOGLE ማስታወቂያ ማሰራት ይፈልጋሉ?

ማስታወቂያዎት ደንበኛ ሊሆንዎት ከፍተኛ እድል ወዳላቸው ሰዎች(Potential
Customers) እንዲደርስስ?

-ጉግል ሰርች ላይ ለሚመጡ ማስታወቂያዎች፤
-በዩቲውብና ጂሜይል ለሚታዩ ማስታወቂያዎች፤
-በተለያዩ አፕሊኬሽኖች ላይ የሚታዩ ማስታወቂያዎችን በማሰራት ምርትና አገልግሎትዎን ለማሳደግ ከፈለጉ ያናግሩን።

ከዚህም በተጨማሪ ፌስቡክ፣ ኢንስታግራም እና ኤክስን በመሳሰሉ የማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ ማስታወቂያ ማሰራትም ይችላሉ።

ቴሌግራም፡ @adsommar
ስልክ፡ 0954260423
13.1K views17:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 18:01:13
ሶማሊያ ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ውጥረት ለማርገብ ኬንያ ያቀረበችው የባሕር ጠረፍ ስምምነት ሃሳብ የለም አለች!

ኬንያ የኢትዮጵያ እና የሶማሊያን ውጥረት ለማርገብ ቀጣናዊ የባሕር ጠረፍ አገልግሎት ስምምነት አማራጭ ለአገራቱ አቅርቤያለሁ ማለቷን ሶማሊያ ውድቅ አደረገች።

ኬንያ አቀረብኩት ያለችው አማራጭ በቀጠናው የሚገኙ የባሕር በር የሌላቸው አገራት በንግድ ስምምነት መሠረት የባሕር መተላለፊያ አገልግሎት እና ጥቅም የሚያገኙበትን ዕድል የሚፈጥር ነው ተብሎ ነበር።የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በበኩሉ ከኬንያ በኩል የተባለው ዓይነት የቀረበ ስምምነት የለም ብሏል።

የሶማሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲዔታ ዓሊ ኦማር ባላድ “ሶማሊያ እና ኢትዮጵያን የሚመለከቱ የባሕር ጠፈር ስምምነት ዘገባዎች ሙሉ በሙሉ መሠረተ ቢስ ናቸው” ሲሉ ሚያዝያ 4/2016 ዓ.ም በኤክስ ገጻቸው አስፍረዋል።አክለውም “ሶማሊያ በግዛት አንድነቷ ላይ እንደማትደራደር” ጠቅሰው “በቀጣናው ሰላም እና መረጋጋት ላይ ትኩረት እንዲደረግ” ጠይቀዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
13.4K views15:01
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 15:57:35
የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት የአገልግሎት ክፍያ ተመን ላይ ማሻሻያ ማድረጉን አስታወቀ!

ከዚህ ቀደም ሲሰራበት የነበረዉን ደንብ በመሻር የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ለሚሰጣቸው የአገልግሎት ክፍያ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን አስታዉቋል።

የሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት አዲሱ ደንብ ከመዉጣቱ በፊት ሲሰራበት የነበረዉን የሰነዶች ማረጋገጥ እና ምዝገባ አገልግሎቶች ክፍያን በመሻር ማሻሻያዉ ከሚያዚያ 7 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።

የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ አገልግሎት ለሚሰጣቸው የሰነድ ማረጋገጥ እና ምዝገባ አገልግሎቶች ክፍያ ለመወሰን ባወጣዉ በዚህ ደንብ በተቀመጠው አዲሱ የክፍያ መጠን የሰነድ አይነቶቹ ቢለያይም ለሁሉም አገልግሎቶች ከ 200 ብር ጀምሮ እስከ 500 ብር ድረስ ክፍያን ይጠይቃል።

ካፒታል በተመለከተዉ በዚህ ደንብ ላይ ለሚንቀሳቀሱ ንብረቶች ሽያጭ ዉል ሰነድ ፣ የማይንቀሳቀስ ንብረቶች ሽያጭ ፣ ለመመስረቻ ፅሁፍ ሰነድ እና በስጦታ መልክ ለሚሰጡ ንብረቶች ዉል ሰነድ የክፍያ አገልግሎት ተመን ከወጣላቸው መካከል ዉስጥ ተካተዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
13.6K views12:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 11:26:32 ከኢትዮጵያ ለመጡ ዜጎች የተሰጠው ጊዜያዊ የከለላ ፈቃድ ተራዘመ!

ለተለያዩ ጉዳዮች መጥተው አሜሪካ ውስጥ የሚገኙ የኢትዮጵያ ዜጎች፣ በሀገራቸው ባለው የፀጥታ ሁኔታ ምክንያት ካለፈው ጥቅምት 10/2015 ዓ.ም. ጀምሮ ለ18 ወራት ተሰጥቶ የነበረው የከለላ ፈቃድ ወይም ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ እንዲቆዩ የሚፈቅደው ደንብ፣ ለሌላ 18 ወራት መራዘሙን የአሜሪካው የሀገር ውስጥ ደህነት ሚኒስትር አሌሃንድሮ ማዮርካስ ዛሬ አስታውቀዋል።

አዲስ የተራዘመው የከለላ ፈቃድ ከሐሙስ ሰኔ 6፣ 2016 እስከ ታኅሣሥ 3፣ 2018 ተግባራዊ እንደሚደረግ ከሃገር ውስጥ ደህነት ሚኒስቴሩ ዛሬ ዓርብ ሚያዚያ 4፣ 2016 የወጣው መግለጫ አመልክቷል።“በሃገሪቱ የሚካሄደው የትጥቅ ግጭት እንዲሁም ለየት ያሉ ጊዜያዊ አስቸጋሪ ሁኔታዎች፣ ግለሰቦች ደህንነታቸው በተጠበቀ ሁኔታ ወደ ሃገራቸው እንዲመለሱ ስለማያስችሉ፣ የከለላው መራዘም አስፈላጊ ሆኗል” ሲል መግለጫው ጨምሮ ገልጿል።

“በኢትዮጵያ የትጥቅ ግጭቱ እና ሁከቱ በበርካታ ክልሎች ቀጥሏል፣ የሰብዓዊ መብት ረገጣዎች ተበራክተዋል፣ ሲቪሎች ለጥቃት ተጋልጠዋል። ድርቅ፣ የጎርፍ አደጋ እና የበሽታ ወረርሽኝ የሚሊዮኖችን ሕይወት አደጋ ላይ ጥሏል” ሲል አክሏል። በመሆኑም የከለላው መራዘም አስፈላጊ እንደሆነ አመልክቷል። ሚኒስትሩ አሌሃንድሮ ማዮርካስ ከተለያዩ ሌሎች መ/ቤቶች ጋራ በመመካከር ከለላው ለ18 ወራት እንዲራዘም መወሰናቸው ተመልክቷል።

በከለላው ተጠቃሚ ለመሆን የሚሹ ኢትዮጵያን የሚመዘገቡበትን ድህረ ገጽም ሚኒስቴር መ/ቤቱ ይፋ አድርጓል።ከከለላው መራዘም ጋራ ተያይዞ የወጣውና F–1 በሚል ቪዛ ወደ አሜሪካ የመጡ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎችን የሚመለከተው መግለጫ እንደሚያሳየው፣ የኢትዮጵያ ዜግነት ያላቸውና በአሜሪካ የሚገኙ ተማሪዎች፣ ከለላው በተራዘመበት የግዜ ገደብ ውስጥ፤ የሥራ ፈቃድ መጠየቅ እንዲችሉ፣ ተጨማሪ ሠዓታት እንዲሠሩ እንዲሁም የሚወስዱትን የትምህርት ኮርሶች መጠን መቀነስ እንዲችሉ ይፈቅዳል።

“ጊዜያዊ የከለላ ፈቃድ፤ በአሜሪካ የሚገኙ ግለሰቦች፣ በሃገራቸው ያለው ሁኔታ፣ ደህነታቸው በተጠበቀ መንገድ እንዲመለሱ በማያስችል ጊዜ ከለላ ይሰጣቸዋል” ሲሉ ሚኒስትሩ ማዮርካስ መናገራቸው በመግለጫው ተመልክቷል። ከትናንት ሚያዚያ 3፣ 2016 በፊት አሜሪካ የገቡ ኢትዮጵያን የገጠማቸው ሁኔታም ይኽው እንደሆነ የጠቀሱት ሚኒስትሩ፣ “ለጊዜው ሕጉ በሚፈቅደው መሠረት ሰብአዊ እፎይታ የመሰለ ከለላ ሰጥተናቸዋል” ብለዋል።

ከተመዘገቡ እና ከለላው የሚጠይቀውን መሥፈርት ካሟሉ፣ ከዚህ ቀደም የወጣው ከለላ ተጠቃሚ የሆኑ 2ሺሕ 300 የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን እስከ ታኅሣሥ 3፣ 2018 ድረስ የከለላው ተጠቃሚነታቸው እንደሚራዘምላቸው ተመልክቷል።ኢትዮጵያን አስመልክቶ የተራዘመው የከለላ ደንብ፣ 12ሺህ 800 የሚሆኑና ከትናንት ሚያዚያ 3፣ 2016 በፊት አሜሪካ እንደገቡና በሃገሪቱ መቆየታቸውን ማረጋገጥ የሚችሉ ኢትዮጵያውያን፣ ወይም መኖሪያቸውን ኢትዮጵያ አድርገው የነበሩ ሌሎች ግለሰቦች፣ ተጠቃሚ ሊያደርግ እንደሚችል ታውቋል።

ኢትዮጵያውያን፣ ወይም መኖሪያቸውን ኢትዮጵያ አድርገው የነበሩ ሌሎች ግለሰቦች፣ አሜሪካ የገቡት ከትናንት ሚያዚያ 3፣ 2016 በኋላ ከሆነ፣ ከለላው እንደማይመለከታቸው የሃገር ውስጥ ሚኒስቴር መ/ቤቱ አስታውቋል።

እንደገና ከለላ ለማገኘት መመዝገብ የሚችሉትም፣ ከዚህ በፊት በመጀመሪያ ኢትዮጵያን አስመልክቶ ወጥቶ በነበረው የከለላ ደንብ ተመዝግበው የነበሩት ብቻ መሆናቸው ተገልጿል።በአሁኑ ወቅት የከለላው ተጠቃሚ የሆኑ ኢትዮጵያውያን፣ ከለላቸውንም ሆነ የሥራ ፈቃዳቸውን ይዘው ለመቆየት፣ ለምዝገባ በተፈቀደው 60 ቀናት ውስጥ፣ ማለትም ከሚያዚያ 7፣ 2016 እስከ ሰኔ 7፣ 2016 ድረስ እንዲመዘገቡ ሚኒስቴር መ/ቤቱ አሳስቧል።

ከዚህ በፊት በወጣው ከለላ መሠረት ለከለላውም ሆነ ለሥራ ፈቃድ እስከ ሚያዚያ 7፣ 2016 ድረስ ያመለከቱ ወይም የሚያመለክቱ ግለሰቦች፣ ለሁለቱም ጉዳዮች እንደገና ማመልክት እንደማያስፈልጋቸው መ/ቤቱ አስታውቋል። የአሜሪካ የዜግነትና የፍልሰተኞች አገልግሎት (USCIS) ከዚህ በፊት የተቀበላቸውን ማመልከቻዎች እየተመለከተና ውሳኔ እየሰጠበት መሆኑም ተመልክቷል። ከዚህ በፊት በወጣው ከለላ መሠረት የገባን ማመልከቻ፣ የአሜሪካ የዜግነትና የፍልሰተኞች አገልግሎት (USCIS) የሚያጸድቀው ከሆነ፣ ከለላውም ሆነ የሥራ ፈቃዱ እስከ ታኅሣሥ 3፣ 2018 እንደሚሰጥ ታውቋል።በአዲሱ የከለላ ፈቃድ መሠረት ለከለላም ሆነ ለሥራ ፈቃድ ማመልከት የሚሹ፣ ከሚያዚያ 7፣2016 እስከ ታህሳስ 3፣ 2018 መመዝገብ እንደሚችሉ ታውቋል።

Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa
14.1K views08:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 10:17:38
ኢትዮ ጂቡቲ ባቡር የአገልግሎት የግንባታ ማሽኖችን ለመጀመሪያ ጊዜ ማጓጓዙን አስታወቀ!

ድርጅቱ እንዳስታወቀው ከጅቡቲ ናጋድ ባቡር ጣቢያ ተጭነው እንዶዴ የባቡር ጣቢያ የደረሱ አምስት ኤክስካቫተሮችን በትላንትናው እለት ለደንበኞች አስረክቧል፡፡

መሰል ጭነት በኢትዮ ጅቡቲ የባቡር አገልግሎት ሲጓጓዝ ለመጀመሪያ ጊዜ መሆኑን ያስታወቀው ድርጅቱ በቅርቡ ተጨማሪ የኮንስትራክሽን ግዙፍ ተሽከርካሪዎች ከጂቡቲ ናጋድ ባቡር ጣቢያ ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ ብሏል።

በተመሳሳይ ሌሎች አዳዲስ አገልግሎት እንደሚያስጀምርም ድርጅቱ ቀደም ሲል ለካፒታል ተናግሯል፡፡

@Yenetube @Fikerassefa
13.1K viewsedited  07:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-13 09:04:39
Yango የትራንስፖርት አገልግሎት መስጫ መተግበሪያ ሲሆን ከ72 ብር ብቻ የሚጀምሩ እጅግ ተመጣጣኝ ዋጋ ያላቸው ጉዞዎችን ይዞሎት መጥቷል! ከመጀመሪያዎ 3 ጉዞዎች ላይ የ30% ቅናሽ ለማግኘት ከGoogle play አሊያም ከApp Store Yangoን ያውርዱ ወይም ወደ 8610 ይደውሉ።
13.6K views06:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-12 14:05:11
ቦሌ የነበረው ተኩስ

ዛሬ ቦሌ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ ተኩስ ነበር

የተኩሱ መነሻ የጎንደር ፋኖ መሪ የነበረው ናሁሰናይ በመንግሥት የፀጥታ ሀይሎች በመያዙ ምክንያት ነው ተብሏል።

ናሁሰናይን ፖሊስ በቁጥጥር ስር ሊያውለው ሲሞክር ከፀጥታ ኃይሎች ጋር የተኩስ ልውውጥ አድርጓል ያሉ ሲሆን አብረውት ከነበሩት ሁለት ሰዎች ውስጥ አንዱ ወዲያውኑ የሞተ ሲሆን ናሁሰናይ ቆስሎ ቢያዝም ህይወቱ አልፏል ተብሏል። አንደኛው ምንም ሳይሆን ተይዟል ተብሏል።

ከፀጥታ ኃይሎች በኩል አንድ የሞተ ሲሆን የቆሰሉም መኖራቸውን ነው የመረጃ ምንጮቹ የገለፁት።
ከቦሌ SNAP PLAZA እስከ ቦሌ መድሃኒያለም ያለው መንገድ ዝግ ተደርጓል ብለዋል።

@Yenetube @Fikerassefa
13.1K viewsedited  11:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-04-11 23:09:49
ኦ ጄ ሲምፕሰን ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ!

ታዋቂው የቀድሞ የእግር ኳስ ተጫዋች፣ እንዲሁም የቀድሞ የትዳር አጋሩን ገድሏል በሚል ከ30 ዓመታት በፊት ከቀረበበትና “የክፍለ ዘመኑ የፍርድ ሂደት” በመባል ከሚታወቀው ክስ ነፃ የወጣው ኦ ጄ ሲምፕሰን፣ በ76 ዓመቱ ትላንት ረቡዕ ላስ ቬጋስ ውስጥ ከዚሕ ዓለም በሞት መለየቱን ጠበቃው አስታውቀዋል።ሲምፕሰን የካንሰር ሕመምተኛ እንደነበርም ጠበቃው ቲ ኤም ዚ ለተባለው ቴሌቪዥን አስታውቀዋል።

በአሜሪካ የእግር ኳስ ጨዋታ ከፍተኛ ዝናን አትርፎ የነበረው ሲምፕሰን፣ በእ.አ.አ 1994 የቀድሞ የትዳር አጋሩን፣ ኒኮል ብራውን ሲምፕሰንን እና ጓደኛዋ የነበረን አንድ ሌላ ግለሰብ ገድሏል በሚል የቀረበበት ክስና የፍርድ ቤት ሂደት፣ የአሜሪካውያንንም ሆነ የተቀረውን ዓለም ትኩረት ሰቅዞ የያዘ ነበር።

ሲምፕሰን፣ ጥቁር፤ የቀድሞ ባለቤቱ ደግሞ ነጭ መሆኗ፣ አሜሪካዉያን የፍርድ ሂደቱን በውጥረት ውስጥ ሆነው እንዲከታተሉት አድርጓል።ሲምፕሰን ከመጀመሪያው ክስ ቢያመልጥም፣ ውድ የስፖርት ማስታወሻዎችን የሚሸጡ ደላላዎችን በመሣሪያ አስፍራርቶ ዘርፏል በሚል ከአሥር ዓመታት በኋላ በቀረበበት ክስ፣ የዘጠኝ ዓመታት እሥር ተፈርዶበታል። በእ.አ.አ 2017 ከእሥር የወጣው ሲምፕሰን፣ የስፖርት ማስታወሻዎቹ የራሱ እንደሆኑ ተናግሯል።

በቀድሞ ባለቤቱ ክስ ወቅት ጠበቃው የነበሩት ታዋቂው ጃኒ ካክረን፣ በሲምፕሰን ላይ በማስረጃነት የቀረበውን የእጅ ጓንት ፍ/ቤቱ ሲለካው መጥለቅ ባለመቻሉ፣ “ጓንቱ ልኩ ካልሆነ፣ ደንበኛዬን ልቀቁ” ማለታቸው፣ የፍርድ ሂደቱን የተከታተሉ ሁሉ የሚያስታውሱት ነው።

[VoA]
@YeneTube @FikerAssefa
12.9K views20:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ