Get Mystery Box with random crypto!

YeneTube

የሰርጥ አድራሻ: @yenetube
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 125.42K
የሰርጥ መግለጫ

መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Ratings & Reviews

3.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 14

2024-03-16 14:07:34
ኬና ልዩ የጥርስ ህክምና ክሊኒክ ዘመኑ ባፈራቸው መሳሪያዎች በመታገዝ ሙሉ የጥርስ ህክምናን በመስጠት ላይ ይገኛል::  ከምንሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል በከፊል
➢ መጥፎ የአፍ ጠረንን ማከም
➢ የቆሸሹ ጥርሶችን በማሽን እናፀዳለን
➢ በህክምና መዳን የማይችሉትን ጥርሶች መንቀል
➢ ወጣ ገባ ያሉ ጥርሶችን በ ኦርቶዶንቲክ አፕላይንስ እና በብሬስ ማስተካከል(with ceramic bracket and metal brackets
➢ የጥርስ ስር ህክምናን መስጠት
➢ የተቦረቦሩ ጥርሶችን እንሞላለን
➢ የተነቀሉ ጥርሶችን በሰው ሰራሽ አርተፊሻል መተካት (partial dentures, full denture, zirconia , ceramic crown, Implant
➢ የጥርስ ራጅ አገልግሎት መስጠት


አድራሻ: ፒያሳ ከኢትዬ ሴራሚክስ ወረድ ብሎ ከአንበሳ ፉርማሲ አጠገብ ኢመኤ ህንዓ 4ኛ ፋሎር ላይ
  Tel: 0911892011 / 0930202124
14.4K views11:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-15 20:39:22 ታግተው የነበሩ አምስት የወንጂ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች መገደላቸው ተነገረ!

ለሁለት ሳምንት ያህል ታግተው የነበሩ አምስት የወንጂ ስኳር ፋብሪካ ሠራተኞች ተገድለው መገኘታቸውን የፋብሪካውን አንድ ኃላፊ ለቢቢሲ ገለጹ።ስማቸውን እንዳይጠቀስ የጠየቁት የስኳር ፋብሪካው ኃላፊ የአምስቱ ሠራተኞች አስከሬን ዛሬ ጠዋት መጋቢት 6/2016 ዓ.ም. መገኘቱን ገልጸዋል።

አስከሬናቸው ከፋብሪካው ማሳ ወጣ ብሎ ጨካ በሚባል የገጠር አካባቢ ነው የተገኘው።ከተገደሉት መካከለ ሦስቱ ሠራተኞች ከወንጂ አካባቢ ሲሆኑ፣ የቀብር ሥነ ሥርዓታቸውም በዛሬው ዕለት መፈጸሙ ተገልጿል።ሌሎቹ ሁለቱ ሠራተኞች አንደኛው ከአዳማ የመጣው ሲሆን ቀብሩ ዛሬ የሚፈጽም ሲሆን፣ እንዲሁም ሌላኛው ከደሴ የመጣው ግለሰብ አስከሬን ወደ ስፍራው ተልኳል ተብሏል።

አራቱ ሠራተኞች በፋብሪካው ውስጥ በትራክተር ኦፕሬተርነት ለረጅም ጊዜ ያገለገሉ እና ዕድሜያቸው ከፍ ያለ እንደሆኑም እኚሁ የፋብሪካው ኃላፊ ለቢቢሲ ተናግረዋል።ሌላኛው የኤሌክትሪክ ሠራተኛ (ፎርማን) ወጣት ሲሆን በቅርብ የተቀጠረ እና ለአንድ ዓመት ያህል በፋብሪካው አገልግሏል።

አንደ ኃላፊው ከሆነ ግለሰቦቹ ከሁለት ሳምንታት በፊት የአዳር ስር ላይ ምሽቱን አሳልፈው ጥዋት ላይ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን ዶዶታ ከሚባለው ፋብሪካው ከሚገኝበት ስፍራ በታጣቂዎች ታግተው ተወስደዋል።ኃላፊው፣ ሠራተኞቹን ያገቷቸው ሰዎች ገንዘብ ጠይቀው እንደነበር? ወይም የጠየቋቸው ጉዳዮች እንዳሉ ዝርዝሩን እንደማያውቁ አስረድተዋል።

ነገር ግን ፋብሪካው ከአጋቾቹ በኩል ምንም እንዳልተጠየቀ ገልጸው፣ ወዲያውኑ ለመንግሥት አካል ማሳወቃቸውን ተናግረዋል።ፓሊስም ሠራተኞቹን ለማስለቀቅ እየተከታታለ እንደነበር የገለጹት ኃላፊው፤ ነገር ግን አስከሬናቸው ዛሬ ጥዋት 2 ሰዓት አካባቢ ተገኝቷል ብለዋል።ስለ ግድያው እንዴት? እና ስንት ሰዓት? ተፈጸመ የሚለውን ባያውቁም ምናልባትም ትናንት ምሽት ተገድለዋል ብለው እንደሚጠረጥሩ የተናገሩት ኃላፊው ሰራተኞቹ መገደላቸውን ሰምተው ወደ አካበቢው ሲሄዱ አስከሬናቸውን አግኝተናል ብለዋል።

በፋብሪካው እገታ ሲያጋጥም የመጀመሪያ መሆኑን እና እስካሁን ባለው ሁኔታ ሰላማዊ እንደነበርም ኃላፊው አስረድተዋል።በእገታው ዙሪያ ቢቢሲ የተለያዩ የመንግሥት ኃላፊዎችን እና ቤተሰቦቻቸውን ለማናገር እየሞከረ ሲሆን በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ መረጃዎችን ስናገኝ እናካትታለን።በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ አቅራቢያ ከአዲስ አበባ 110 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው የወንጂ ስኳር ፋብሪካ በ1946 ዓ.ም. ኤች.ቪ.ኤ በተባለ የኔዘርላንድስ ተቋም እና በኢትዮጵያ መንግሥት የጋራ ባለቤትነት የተቋቋሙ በአገሪቱ ቀዳሚ የስኳር ፋብሪካ ነው።

ወታደራዊው መንግሥት ወደ ሥልጣን ከመጣ በኋላ ፋብሪካው ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያ መንግሥት ባለቤትነት ስር መግባቱ ይታወሳል።ወንጂ ስኳር ፋብሪካ በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 496/2014 ራሳቸውን እንዲያስተዳድሩ ከተደረጉት አምስት ስኳር ፋብሪካዎች መካከከል አንደኛው ነው።

@YeneTube @FikerAssefa
15.5K views17:39
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-09 18:50:57
ዓባይ ባንክ 7 ሚሊዮን ብር ያወጣበትን አዲሱን የንግድ ምልክት ይፋ አደረገ።

የባንኩን አዲስ መለያ የተዘጋጀው በአቶ ያየህይራድ ታደሰ እና በስቱዲዮኔት እንደሆነ ተነግሯል፡፡ ለስራውም 7 ሚሊዮን ብር ተከፍሏል ተብሏል። አዲሱ የንግድ ምልክት የዓባይ ወንዝ ዋና መገለጫ ከሆነው የጢስ ዓባይ ፏፏቴ የተነሳ እና በሰባት አራት ማዕዘናዊ ቋሚ መስመሮች የተወከለ መሆኑን ተጠቅሷል።

ባንኩ ነባሩን የንግድ ምልክት እና መገለጫ ወደዚህ የቀየረው በተለየ መልኩ የደንበኞች አገልግሎት ለመስጠት እና ለእድገት እና ለፈጠራ ያለውን ትጋት ለማስረዳት በማሰብ ነው ተብሏል። ይህም የባንኩን እድገት፣ ችግሮችን የመቋቋም አቅም፣ አስተማማኘነት እና ታማኘነት ያመለክታል ሲባል ሰምተናል፡፡

Via ሸገር ኤፍ ኤም
@Yenetube @Fikerassefa
13.0K viewsedited  15:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-09 10:27:59 የሎተሪ አሸናፊ ባለመቅረቡ ስምንት ሚሊዮን ብር ተመላሽ መደረጉ ተገለጸ

እያንዳንዳቸው የአራት ሚሊዮን ብር ዕጣ ያላቸው ሁለት የሎተሪ ቲኬቶች አሸናፊዎች ባለመቅረባቸው ስምንት ሚሊዮን ብር ዛሬ የካቲት 29/ 2016 ዓ.ም ተመላሽ መደረጉን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር አስታወቀ።

እነዚህ ሁለት ዕጣዎች ብሔራዊ ሎተሪ ከሚያሳትማቸው ከፍተኛ ዕጣ የሆነው 20 ሚሊዮን ብር የሚያስገኘው የእንቁጣጣሽ ሎተሪ ቲኬቶች መሆናቸውን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ዳይሬከተር አቶ ቴዎድሮስ ንዋን ለቢቢሲ ገልጸዋል።

በእንቁጣጣሽ ሎተሪ ከቀረቡት አምስት ቲኬቶች ሶስቱ ቀርበው 12 ሚሊዮን ብር ሁለት አሸናፊዎች ቢረከቡም የቀሪዎቹ ሁለት ቲኬቶች አሸናፊዎች ባለመቅረባቸው ገንዘቡ ወደ ተቋሙ ገብቷል ብለዋል።

ጳጉሜ 2015 ዓ.ም የወጣው የእንቁጣጣሽ ሎተሪ የሁለቱ ቲኬቶች ወይም የስምንት ሚሊዮን ብር አሸናፊ በቀን ስራ የሚተዳደር አንድ ግለሰብ ሲሆን ዕጣው ከወጣ ከሶስት ወር በኋላም ወስዷል።

ሌላኛው አሸናፊ የቀን ሰራተኛው የሚሰራበት መኪና አሽከርካሪ የሆነ ግለሰብ ሲሆን መስከረም ወር መጨረሻ ላይ መጥቶ የአራት ሚሊዮን ብር ሽልማቱን ወስዷል።

በ2010 ዓ.ም የወጣው 20 ሚሊዮን ብር የሚያስገኘው የእንቁጣጣሽ ሎተሪ በተመሳሳይ መልኩ ስምንት ሚሊዮን ብር ዕጣ ያላቸው ሁለት የሎተሪ ቲኬቶች የያዙ አሸናፊዎች አልቀረቡም።

የዕጣው አሸናፊዎች አለመቅረባቸውን በተመለከተ በሚዲያ ከተነገረ በኋላ ጊዜው ሊያልፍ አምስት ቀን ሲቀረው አንድ ግለሰብ ሶስቱን ቲኬቶች አቅርቦ 12 ሚሊዮን መቀበሉን አስረድተዋል።

የዕጣ አሸናፊዎች መጥተው ገንዘባቸውን አለመውሰድ በተደጋጋሚ እንደሚያጋጥም የሚገልጹት አቶ ቴዎድሮስ በዚህ አጋጣሚም ገንዘቡን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ተመላሽ ያደርገዋል ብለዋል።

“ህብረተሰቡ ሎተሪ የመግዛት ከፍተኛ ፍላጎት አለው። የዚያን ያህል ደግሞ የማያዩ በርካታ ደንበኞች አሉ” ብለዋል።

በእንቁጣጣሽ የሎተሪ ብቻ ሳይሆን በሌሎች ዕጣ ዓይነቶችም በተደጋጋሚ ይህ እንደሚያጋጥምም ገልጸዋል።

@Yenetube @Fikerassefa
13.2K viewsedited  07:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-09 10:03:50
Biggest Student Event

March 17 Sunday @ Cassiopeia hotel
2:00 Morning until 8:00 Local Time.


Hosted by In Africa Together (IAT)

Licensed company in Michigan, United States and Licensed in Addis Ababa, Ethiopia

Students can start their study abroad applications process

No Pre Payment
No English Proficiency Exam
100% Admission Guarantee

Register only with your documents

USA Italy China

Our Packages will provide you with higher visa chances

66% scholarship in USA the rest 34% with student loan

100% Scholarship in Italy and China with additional pocket money

You can apply for Bachelors Degree,Masters Program  and PHD

To be part of this event
Register in the link below
https://form.jotform.com/240624657131149
13.0K views07:03
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-08 09:19:03
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፒያሳ ለሚነሱ የግል አልሚዎች “ካሳ እና ምትክ መሬት” እንደሚሰጥ አስታወቀ!

በአዲስ አበባ ፒያሳ አካባቢ ከተገነባው የአድዋ ድል መታሰቢያ ጎን በሚገኘው ቦታ ላይ የሚኖሩ ነዋሪዎች፤ ከስፍራው እንደሚነሱ የከተማይቱ ከንቲባ አዳነች አበቤ ማረጋገጫ ሰጡ። ለእነዚህ የልማት ተነሺዎች የከተማው አስተዳደር “የጋራ መኖሪያ ቤት” አሊያም “አዲስ የሚገነባ የቀበሌ ቤት” እንደ የምርጫቸው እንደሚያቀርብ፤ በአካባቢው በተዘጋጀው ፕላን መሰረት ግንባታ ለማከናወን የገንዘብ አቅም ለሌላቸው የግል አልሚዎች ደግሞ “ካሳ እና ምትክ መሬት” እንደሚሰጥ ገልጸዋል።

አዳነች ይህን ያሉት በአዲስ አበባ ከተማ በተለያዩ ቦታዎች ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በመካሄድ ላይ የሚገኙ “የመንገድ ኮሪደር ልማት” ስራዎችን በተመለከተ በሰጡት ገለጻ ነው። በመንግስት እና ለመንግስት ቅርበት ባላቸው የቴሌቪዥን ጣቢያዎች በትላንትናው ዕለት በተላለፈው በዚህ ገለጻ፤ የኮሪደር ልማቱን የተመለከተ ጥናት ሲከናወን የቆየው ከግንቦት 2015 ጀምሮ መሆኑ ተጠቅሷል።

ይህ የመንገድ ኮሪደር ልማት ፕሮጀክት፤ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ከጸደቀ ማግስት ጀምሮ “ወደ ስራ እንዲገባ እና ልዩ ክትትል እንዲደረግለት” ውሳኔ ተላልፎ ነበር። ከንቲባ አዳነች በትላንቱ ገለጻቸው ይህንኑ አረጋግጠዋል።

“ይሄንን በምንሰራበት ሰዓት ከመንገድ ላይ የሚነሱ፣ ከመንገድ ላይ ወደ ውስጥ ጠጋ የሚሉ አጥሮች ይኖራሉ። ከተለያየ ቦታ ላይ በእርጅና አሁን ያለንበትን ዘመን የማይመጥኑ ግንባታዎች አሉ። ከከተማው መዋቅራዊ ፕላን ውጪ የተገነቡ አሉ። የተለያዩ ጥፋቶች አሉ...እርሱን ለማስተካከል ሰዎችን ከቦታቸው ልናነሳ እንችላለን” ሲሉም አዳነች ተናግረዋል።

Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
13.9K views06:19
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-08 09:18:54
በውጤቱ የሚደሰቱበት ከችግረወት የሚወጡበት ሀሳበወትን የሚአሟሉበት ለበሽታወት መፍትሔ የሚአገኙበት

ከአሉበት ሁነው በስመወት እና በናትወት ስም ያለበወትን ችግር ማወቅ ይችላሉ

በየቀኑ  የአባቶቻችን እውቀት
የጥበብ ትምሕርት ለማግኔት ከታች ቻናሎቸን ይቀላቀሉ 

      ውጤቱን እንዳዩ ክፍያ ይፈጽማሉ

መሪጌታ ጥበቡ
ባህላዊ መድሐኒት ምርመራ እና ህክምና መስጫ ማእከል  ከምንሰጣቸው በጥቂቱ
  ለገርጋሪ ለአይነጥላ ለአይን ውጊት
ገብያ ለተዘጋበት ለሚገረግረው (ለገብያ)
አፍቅራ ላጣች ለመስተፋቅር (ላጣ)
ለኪንታሮት ባንድቀን የሚአወጣ መዳኒት
ለእሪህ (በአንድቀን ሕክምና)
ለዲስክ መንሸራተት
ለአስም
ለስንፈተወሲብ ለመቸኮል ለመልፈስፈስ
ለቁራኛ ለመተት መፍትሔ
ትዳር ለሚገረግራት
ለመካን
ለጭንቀት
ለሚጥል በሽታ
ለፊት ማድያት
ሌሊት ለሚሸና
የሕዝብ መስተፋቅር
ለሕገጠብቅ እንዳይሔድ (ወይ እንዳቴድ)
ገንዘብ ለሚበተንበት (ባት)
     
        ለበለጠ መረጃ አድራሻ ባህርዳር ቀበሌ11 ዲያስፖራ በአዲሱ አስፓልት ዳሽን ባንክ ጀርባ
ቅርንጫፍ አዲስ አበባ ተደራሽ በሁሉም ቦታወች ከአገር ውስጥም ውጭም
የሚፈልጉትን በውስጥ መስመር በቴሌግራም ያስቀምጡ

ለበለጠ መረጃ 0912718883
                           0917040506
   በቲክቶክ መማማሪያ የእውቀት ምንጭ
https://vm.tiktok.com/zMM2kcDUb/
    በቴሌግራም የቴሌግራም ቻናል መማማሪያ
https://t.me/mergatah
13.1K views06:18
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-07 08:54:40
እንዴት አደራችሁ

ውድ ኢትዮጲያውያን ከተቀረው የሰለጠነ አለም ጋር እኩል ለመራመድ ስለ ኮምፒውተር ሳይንስ ጠለቅ ያለ መሰረታዊ እውቀት በነፃ ከሀርቫርድ ዩኒቨርስቲ በኦንላይን ይማሩ!

ይህንን ኮርስ መማር ከእውቀት ባሻገር CV ላይ ከበድ ያለ የተሟላ እንዲሆን የሚያደርግ ሲሆን፣ በትልልቅ የቴክኖሎጂ ካምፓኒዎች እውቅናን ያተረፈ ኮርስ ነው፣ ወጣቶች በሳምንት 2 ቀን ብቻ ኦንላይን ብትማሩ Harvard ነፃ ሰርተፍኬት ይኖራችሗል።

ከዛ በተጨማሪ የፕሮግራሚንግ ቋንቋን በቀላሉ ትማራላችሁ፣ ስለ ኮምፒውተር ሳይንስ፣ ስለ ፓይተን፣ SQL ፣ JavaScript፣ Debugging እና ሌሎችም ድንቅ ድንቅ ሳይንሳዊ እውቀት ምታገኙበት ነው ይጠቅመዋል ለምትሉት ሰው ሁሉ ሼር አድርጉ።

Official Link: https://www.edx.org/learn/python/harvard-university-cs50-s-introduction-to-programming-with-python
12.6K views05:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-06 15:02:31
የኦነግ የፖለቲካ ኦፊሰር አቶ በቴ ኡርጌሳ፤ በ100 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲፈቱ በፍርድ ቤት ተወሰነ

“ሁከት እና በጥብጥ በማነሳሳት” ወንጀል ተጠርጥረው ላለፉት 13 ቀናት በእስር ላይ የቆዩት የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ኦፊሰር አቶ በቴ ኡርጌሳ፤ 100 ሺህ ብር የዋስትና ገንዘብ በማስያዝ ጉዳያቸውን በውጭ እንዲከታተሉ በፍርድ ቤት ተወሰነላቸው። ለፖለቲከኛው ዋስትናውን የፈቀደው፤ የአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት ነው።

አቶ በቴ ሲቪል በለበሱ የጸጥታ ኃይሎች ተይዘው በቁጥጥር ስር የዋሉት፤ “አፍሪካ ኢንተለጀንስ” ለተሰኘው የዜና ድረ ገጽ ዘጋቢ ከሆነው  አንቷን ጋሊንዶ ጋር ሐሙስ የካቲት 14፤ 2016 በአዲስ አበባው ስካይ ላይት ሆቴል በውይይት ላይ በነበሩበት ወቅት ነው። ዛሬን ጨምሮ ለሶስተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረቡት የኦነጉ ፖለቲከኛ፤ በፖሊስ ተደጋጋሚ የጊዜ ቀጠሮ ሲጠየቅባቸው ቆይቷል።

ዛሬ ረፋዱን በተካሄደው ችሎትም፤ ፖሊስ “ምርመራዬን አልጨረስኩም” በሚል ተጨማሪ 11 የምርመራ ቀናትን ጠይቋል። የአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት ባለፈው ሳምንት ሐሙስ በነበረው ችሎት ለፖሊስ ተጨማሪ አምስት የምርመራ ቀናት የፈቀደው፤ ፖሊስ የሚያቀርበውን “የስልክ ምርመራ ውጤትን ለመስማት” ነበር።

በዛሬው ችሎት የተገኙት መርማሪ ፖሊስ፤ የአቶ በቴን የስልክ የምርመራ ውጤት ለመቀበል ለኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢንሳ) በተደጋጋሚ ጥያቄ ምማቅረባቸውን ሆኖም እስካሁን ውጤቱን አለመቀበላቸውን ገልጸዋል። ከዚህ በተጨማሪም የሰው ማስረጃ ለማሰባሰብ ተጨማሪ ቀናት እንደሚያስፈልጓቸው አስረድተዋል።

Via Ethiopia Insider
14.6K views12:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2024-03-06 14:35:42
ወላይታ ሶዶ በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያናችን እየፈረሰችብን ነዉ ድምፅ ሁኑን

በወላይታ ሶዶ በአታ ለማርያም ቤተክርስትያን ይዞታ "ለኢንቨስትመንት ይፈለጋል" በሚል ምክንያት በጸጥታ አካላት በጉልበት እየፈረሰች ነው

በአንድ ኦርቶዶክሳዊ ምዕመን ስጦታ ሰጪነት በተገኘ መሬት ላይ የተተከለችው በወላይታ ሶዶ ከተማ የምትገኘው ዋዱ በአታ ለማርያም ቤተክርስቲያን
የወላይታ ዞን ስፍራውን ለኢንቨስትመንት ይፈለጋል በሚል ምክንያት መቃኞ ህንጻ መቅደሱን ለማፍረስ የጸጥታ ኃይል ያሰማራ ሲሆን የጸጥታ አካላት የጦር መሳርያ በመጠቀም ምዕመናንን ከአከባቢው ለማራቅ ቢሞክሩም አሁን ድረስ ህዝቡ ቤተክርስቲያኒቷን ከበ በመያዝ የማፍረስ ተግባሩን ለማስቆም እየሞከረ ይገኛል። ድምፅ ሁኑን

@Yenetube @Fikerassefa
13.9K views11:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ