Get Mystery Box with random crypto!

Ministry of education®

የቴሌግራም ቻናል አርማ tmihirt_minister — Ministry of education® M
የቴሌግራም ቻናል አርማ tmihirt_minister — Ministry of education®
የሰርጥ አድራሻ: @tmihirt_minister
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.99K
የሰርጥ መግለጫ

ቀዳሚ የተማሪዎች የመረጃ ምንጭ 🇪🇹
Share and Support us
ጥያቄ ና አስተያየት ለመስጠት
  👉 @Student_Comment_bot

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 15

2022-06-30 09:41:57
71 ሺ 832 ተማሪዎች የሚፈተኑበት የዘንድሮው የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ሰኔ 27 ይጀምራል።

የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከሰኔ 27 እስከ 29 እንደሚሰጥ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ምክትል ሃላፊ አቶ ዳኘው ገብሩ በፈተናው አሰጣጥ ዙሪያ መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫው የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና በከተማዋ በ 792 ትምህርት ቤቶች እንደሚሰጥ ተነግሯል።

ለዚህም 179 የመፈተኛ ጣቢያዎች ተዘጋጅተዋል ብለዋል ።

አቶ ዳኘው አክለውም አጠቃላይ በከተማዋ 71 ሺህ 832 ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ነው የተናገሩት።

ኮማንድ ፖስት ተቋቁሞ እስካሁን ያለውን የፈተናው ዝግጅት ሂደት የገመገመ ሲሆን ፈተናው ወደ መፈተኛ ጣቢያዎች ለማጓጓዝ ሂደት ላይ ነውም ተብሏል።

ሰኔ 24 ቀንም ለሁሉም ፈተናውን ለሚመለከት የትምህርት ማህበረሰብ ኦረንቴሽን እንደሚሰጥም ተገልጿል፡፡

(አዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ)

ለጓደኛዎ ሼር ያድርጉ

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
2.0K views06:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-30 09:41:09 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2014 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና አፈጻጸም ዙሪያ ሂደቱን ለመከታተል ከተቋቋመው የኮማንድ ፖስት አደረጃጀት ጋር ውይይት አካሄደ ፡፡

በውይይቱ የከተማ አስተዳደሩና የክፍለ ከተማ የሰላምና የጸጥታ እንዲሁም የፖሊስ ኮሚሽን አመራሮችን ጨምሮ የክፍለ ከተማ ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊዎች ተሳታፊ የሆኑ ሲሆን ፈተናው ዘንድሮ ከሰኔ 27 እስከ 29/2014 ዓ.ም ድረስ ለተከታታይ ሶስት ቀናት እንደሚሰጥ የወጣው መርሀ ግብር ያሳያል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘላለም ሙላቱ የፈተና አፈጻጸም ሂደቱን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ ፈተናው ሰላማዊ ሆኖ በስኬት እንዲጠናቀቅ ከፈተና ህትመት ጀምሮ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መሰራታቸውን ገልጸው በከተማ አስተዳደሩ በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች የፈተና ሂደቱ ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ እስከ ፍጻሜው ድረስ ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ የትምህርት መዋቅሩ እንደተለመደው ከፖሊስም ሆነ ሌሎች ጉዳዩ ከሚመለከታቸው የጸጥታ ሀይሎች ጋር በጋራ እንደሚሰራ አስታውቀዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ በበኩላቸው በ2014 ዓ.ም በከተማ አስተዳደሩ በ179 የመፈተኛ ጣቢያዎች 71,832 ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱና ለሁሉም ተማሪዎች አድሚሽን ካርድ መታደሉን ጠቅሰው በፈተናው ወቅት ከጣቢያ ኃላፊ ውጭ ማንኛውም አካል ሞባይል ይዞ ወደፈተና ጣቢያ መሄድ እንደማይችል በአጽንኦት አሳስበዋል፡፡

ዘንድሮ በሁሉም የፈተና ጣቢያዎች 1,800 ፈታኝ ፤ 450 ሱፐር ቫይዘር ፤ 179 የፈተና ጣቢያ ኃላፊዎችን ጨምሮ በድምሩ 2,429 የፈተና አስፈጻሚዎች መመደባቸው የተገለጸ ሲሆን ከቢሮ ጀምሮ እስከ ፈተና ጣቢያዎች ድረስ የፈተናውን ሂደት የሚከታተል ኮማንድ ፖስት እንደተዋቀረም ተገልጻል፡፡

ለጓደኛዎ ሼር ያድርጉ

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
1.7K viewsedited  06:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 14:28:14
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርስቲዎች ዉስጥ እንደሚሰጥ ተገለፀ።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በሆሳዕና፣ በወራቤና በወልቂጤ ከተሞች የሚገኙ ሁለተኛ ደረጃና ሞዴል ትምህርት ቤቶችን ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸው ወቅት ከተማሪዎችና ከትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ ጋር ባደረጉት ቆይታ የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና በትምህርት ቤቶች ሳይሆን #በዩኒቨርስቲ ውስጥ እንደሚሰጥ ገልጸዋል።

እንደሚኒስትሩ ገለጻ የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና በኤሌክትሮኒክስ /online/ መስጠት እስከሚጀመር ድረስ በዩኒቨርስቲዎች መሰጠቱ ይቀጥላል።

የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርስቲ እንዲሰጥ የተወሰነው የፈተና ሰርቆትና ማጭበርበርን ለማስቀረት ታስቦ በመሆኑ ተማሪዎች ትምህርት በስራና በታታሪነት የሚገኝ መሆኑን አውቀው በርትተው መማር ፣ማጥናትና ማወቅ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የትምህርት ሚኒስቴር የትምህርትን ጥራትን ለማሻሻል በአጠቃላይና ከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፎች ሌሎችንም የተለያዩ እርምጃዎች በመውሰድ ላይ መሆኑንም ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ጠቁመዋል።

ለጓደኛዎ ሼር ያድርጉ

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
2.8K viewsedited  11:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-29 07:59:17
ጥራት ያለው ተማሪ የማያፈሩ፤ ማኅበረሰቡን የማይጠቅሙ ዩኒቨርስቲዎች ሊዘጉ እንደሚችሉ ተጠቆመ

ጥራት ያለው ተማሪ ማፍራት የማይችሉ፣ ደረጃውን የጠበቀ ምርምር የማያካሂዱና የአካባቢውን ማኅበረሰብ የማይጠቅሙ ዩኒቨርስቲዎች ሊዘጉ እንደሚችሉ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ጠቆሙ።

ሚኒስትሩ ከዋቸሞ ፣ ወራቤና ወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ምሁራን ተመራማሪዎችና የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው ይህንን የገለጹት።

ዩኒቨርስቲዎች ዓለም አቀፍ ውድድሩን ለመሸከም የሚያስችል ዕውቀት የሚፈራባቸው ቦታዎች መሆናቸውን የጠቆሙት ፕ/ር ብርሃኑ ይሁን እንጂ አሁን ባለንበት ሁኔታ ዩኒቨርስቲዎች ጥሩ ዕውቀት ያላቸው ተማሪዎች ማፍራት ብቻ ሳይሆን ጥሩ ዜጎች እንኳን ማፍራት አልቻሉም ብለዋል።

የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስቴር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በበኩላቸዉ የውይይቱ ዓላማ በትምህርት ዘርፉ ያሉ ችግሮችን ምንነት በመለየት ችግሮችን ለመፍታት የጋራ መግባባት ላይ መድረስ መሆኑን ገልጸዋል።

በውይይቱ ላይ በየዩኒቨርስቲዎቹ ፕሬዚዳንቶች የመነሻ ሀሳቦችና ጥያቄዎች ቀርበው ምላሽና ማብራርያ መሰጠቱን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ለጓደኛዎ ሼር ያድርጉ

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
1.8K viewsedited  04:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-27 11:08:53
ፈተና አላሰራከኝም በሚል ምክንያት ድብደባ የፈጸሙት ተማሪዎች

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ የሀገራችን ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ እየተለመዱ የመጡ ነውረኛ ድርጊቶች ተበራክተዋል። በብዙ ዩንቨርሲቲዎቻችን ላይ ሎካል በመባል የሚታወቁ ዩንቨርሲቲው በሚገኝበት አካባቢ ነዋሪ የሆኑ ተማሪዎች በሌሎች ተማሪዎች ላይ አለፍ ሲልም በግቢው ሰራተኞች ላይ መምህራንንም ጨምሮ ጫና ሲያሳድሩ ይስተዋላል። ሎካል የሚባሉት ስብስቦች ያደርሷቸዋል ከሚባሉት ጫናዎች መካከል በብዛት የሚደርሱን ጥቆማዎች በፈተና ወቅት የሚፈፀሙ ተገቢ ያልሆኑ ድርጊቶች ናቸው።

አንዳንድ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ላይ ግልፅ በሆነ መልኩ ሎካል ለሚባሉት ተማሪዎች የፈተና ጥያቄዎች ቀድመው እንደሚወጡ በተለያዩ ጊዜያት ከሚደርሱን ጥቆማዎች ለመረዳት ችለናል።

አዲሱ የትምህርት ፍኖተ ካርታ ተግባራዊ መደረግ ከጀመረ ወዲህ በብዛት የሚፈለጉ የትምህርት መስኮችን ለመቀላቀል በሚደረገው ውድድር ላይም የሎካሎች ተጽዕኖ ቀላል እንዳልሆነ በርካታ ተማሪዎች በምሬት ጭምር ነግረውናል።

ሎካል የሚባሉ ተማሪዎችን የተለያዩ ፀያፍ ድርጊቶች በሌላ ሰፊ ዳሰሳ የምንመለስበት ይሆናል።

ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጫን የምትመለከቱት የተንቀሳቃሽ ምስል በትላንትናው ዕለት የ atc ቤተሰቦች ያካፈሉን መረጃ ሲሆን ድርጊቱ የተፈፀመው በወልቂጤ ዩንቨርሲቲ ሎካል ተማሪዎች መሆኑን አረጋግጠናል።

ተማሪው ላይ ድብደባ የፈጸሙት ተማሪዎች በቪድዮው ላይ መስማት እንደሚቻለውም #ፈተና_አላሰራከኝም በሚል ምክንያት ነበር። የተማሪውን ጉዳይ በቅርበት እየተከታተልን ሲሆን ዩንቨርሲቲው በተማሪዎቹ ላይ የሚወስደውን እርምጃ እንዲሁም የተማሪውን የደህንነት ጉዳይ ተከታትለን እናሳውቃቹሃለን።

ለጓደኛዎ ሼር ያድርጉ

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
2.4K viewsedited  08:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 09:31:33
በክፍል ዉስጥ የነበሩ 85 ተማሪዎችን ከጎርፍ አደጋ መታደጉን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ፡፡

ዛሬ ከቀኑ 7፡00 ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ልዩ ቦታዉ ፊጋ እየተባለ በሚጠራዉ አካባቢ በሚገኘዉ ኒዉ ፖራዳይ መዋለ ህጻናት ትምህርት ቤት በክፍል ዉስጥ የነበሩ እድሜያቸዉ ከ4 እስከ 7 የሆኑ 85 ተማሪዎች ከዋናዉ መንገድ ጥሶ በክፍል ዉስጥ በገባዉ ጎርፍ ተከበው እንደነበር ተገልጿል።

የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ወደ ቦታዉ በመገኘት ከትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ ጋር በመተባበር ሰማናንያ አምስቱንም ተማሪዎች ምንም ዓይነት ጉዳት ሳይደርስባቸዉ በጎርፍ ከተያዙበት ክፍል ዉስጥ በሰላም ማዉጣት መቻሉን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያዉ አቶ ንጋቱ ማሞ ተናግረው ክረምቱ የሚበረታ በመሆኑ ሁሉም ህብረተሰብ ከኮሚሽን መስሪያ ቤቱና ከሚመለከታቸዉ ተቋማት የሚተላለፉ የጥንቃቄ መልእክቶችን ተግባራዊ እንዲያደርግም ኮሚሽኑ አሳስቧል፡፡

ለጓደኛዎ ሼር ያድርጉ

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
2.7K viewsedited  06:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-24 09:31:33 #Fias777

ምስኪኑ የኢትዮጵያ ህዝብ ይህው አዲሱ የማጭበርበሪያ ዘዴ ልክ እንደ ቲያንስ፣ከ3 ሚሊዮን በላይ አባል ያለው እና በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ የሰበሰበው ይህ የonline business website አድራሻውን አጥፍቷል።

ግማሹ :-

* መሬት ሽጦ
* ባጃጁን ሽጦ
*ግማሹ ተበድሮ አተርፋለው በሚል ገንዘባቸውን ያስገቡ ሰዎች በዚህ የonline business website ሿሿ ተሰርተዋል።

ከዚህ በፊት ኢትዮያንቼክ ጉዳዩ እንዳሳሰበው በመግለፅ እንዲጠነቀቁ ቢያሳስብም በበርካቶች ሲተች እና ሲናቅ ተመልክተናል በተጨማሪም ሙሉ ለሙሉ ባይባልም መንግስትም አሳስቦ እንደነበር ተመልክተናል።

አብዛኛው ህዝብ ግን ሲነገረው አልሰማ ስላለ Fiass 777 የተባለው የሌቦች ጥርቅም የብዙሀኑ ገንዘብ ይዞ ላሽ ብሏል።

ባለቤቶቹ የማይታወቁ ሲሆን መንግስትም ተጠንቀቁ ሲል ነበር።
Ethio mereja

ለጓደኛዎ ሼር ያድርጉ

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
2.3K viewsedited  06:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-23 11:40:04
#KotebeUniversityOfEducation

ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ የተቋሙን አዲስ ሎጎ በይፋ አስመርቋል።

አዲሱ አርማ ተቋሙ ወደ አዲስ ምዕራፍ መሸጋገሩን የሚያመለክት መሆኑን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ብርሃነመስቀል ጠና (ዶ/ር) ተናግረዋል።

የየራሳቸው ትርጓሜ ያላቸው ጸሐይ፣ ደረጃዎች፣ መፅሀፍ እና የዲግሪ ቆብ ምልክቶች በአርማው ላይ ሰፍረዋል።

በተጨማሪም የዩኒቨርሲቲው መዝሙር በአርቲስት ሙሉ ገበየሁ በአዲስ መልክ ተሰርቶ መጠናቀቁም ተገልጿል።

የዩኒቨርሲቲውን መዋቅር ጨምሮ በርካታ አስተዳደራዊ ጉዳዮች እየተሰሩ እንደሆነ የጠቆሙት ፕሬዝዳንቱ፤ የአራት አዳዲስ ህንፃዎች ግንባታ መጀመሩንም ገልጸዋል።

ለጓደኛዎ ሼር ያድርጉ

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
2.3K viewsedited  08:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ