Get Mystery Box with random crypto!

Ministry of education®

የቴሌግራም ቻናል አርማ tmihirt_minister — Ministry of education® M
የቴሌግራም ቻናል አርማ tmihirt_minister — Ministry of education®
የሰርጥ አድራሻ: @tmihirt_minister
ምድቦች: ትምህርት
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 9.99K
የሰርጥ መግለጫ

ቀዳሚ የተማሪዎች የመረጃ ምንጭ 🇪🇹
Share and Support us
ጥያቄ ና አስተያየት ለመስጠት
  👉 @Student_Comment_bot

Ratings & Reviews

4.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

2

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 10

2022-09-23 09:26:54 ዩንቨርስቲዎች በፌደራል ፓሊስ ብቻ ይጠበቃሉ
==================
ኢሳት (መስከረም 13/2015) አዲስ አበባ:- በ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሊያጋጥሙ የሚችሉ የፀጥታ ስጋቶችን ለመከላከል ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር መደረጋቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

ባለፉት አመታት በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተፈጠሩ ችግሮች ዳግም እንዳይከሰቱ ፣ ወላጆች በእምነት ልጆቻቸውን እንዲልኩና ተማሪዎች ደህንነት ተሰምቷቸው ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ለማድረግ በመንግስት በኩል በቂ ዝግጅት መደረጉ ተገልጿል።

ከዚህ በፊት በዩኒቨርስቲዎች ያጋጥሙ ከነበሩ የፀጥታ ችግሮች በመነሳትም በአዲሱ የ2015 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሊያጋጥሙ የሚችሉ የፀጥታ ስጋቶች ከወዲሁ ለመከላከል ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በፌዴራል ፖሊስ ቁጥጥር ስር መደረጋቸውን የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ደኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ በተለይም ለኢሳት ተናግረዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከዚህ ቀደም ተማሪዎች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ በቆዩባቸው ትምህርት ቤቶች ይሰጥ የነበረው የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና የፈተና ስርቆትና ማጭበርበርን ለማስቀረት ሲባል በዩኒቨርስቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ የትምህርት ሚኒስቴር ማስታወቁ አይዘነጋም።

ይህንን ተከትሎም የፀጥታቸው ሁኔታ አስተማማኝ ባልሆኑ አካባቢዎች በሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፈተናቸውን እንዲወስዱ የተመደቡ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በአካባቢው ያለውን የፀጥታ ችግር በማንሳት ስጋታቸውን ሲገልፁ ተደምጠዋል።

ለዚህ የተማሪዎች አለፍ ሲልም የወላጆች ስጋትም የፀጥታ ችግር አለባቸው በሚባሉ አካባቢዎች የሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎችን ተማሪዎች ያለስጋት ፈተናቸው ላይ ብቻ ትኩረት በማድረግ እንዲፈተኑ ለማስቻል የሚመለከተው አካል እየሰራበት እንደሆነ እና የፀጥታ ስጋቱን ለማስወገድ መፍትሄ እንደተቀመጠለት ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ አክለው ለኢሳት ተናግረዋል።

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
1.1K viewsedited  06:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-23 07:24:17
የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች የልደት ምስክር ወረቀት በመያዝ ለፈተና እንዲቀመጡ ሊደረግ ነው 

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በኩል የመታወቂያ አገልግሎት መቆሙ የሚታወስ ነው።ይህ በእንዲህ እንዳለ የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ዝግጅት እየተደረገ እንደመሆኑ መጠን ለፈተና ለመቀመጥ ተፈታኞች የነዋሪነት መታወቂያ እየጠየቁ በመሆኑ በልደት የምስክር ወረቀት ለፈተና እንዲቀመጡ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የወሳኝ ኩነት ምዝገባ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮናስ አለማየሁ በተለይ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

ማንኛውም የመታወቂያ አገልግሎት አሁን ላይ  የቆመ በመሆኑና የዜጎችን ማንነት የሚገልፅ ገዢ ሰነድ የልደት ምዝገባ በመሆኑ የከተማ አስተዳደሩ ለተፈታኞች በልደት የምስክር ወረቀት ለፈተና እንዲቀመጡ ለማድረግ ከኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ጋር በጋራ በመሆን በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ማስተካከያ እንዲደረግ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የልደት ምዝገባ ያላከናወኑ ተፈታኞች ከወዲሁ ምዝገባውን አከናውነው የምስክር ወረቀት በእጃቸው እንዲይዙ ሲሉ አቶ ዮናስ ጨምረው ለብስራት ሬዲዮ  ተናግረዋል።

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
1.6K viewsedited  04:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-22 13:50:49
#NationalExam

ለ12ኛ ክፍል የብሄራዊ ፈተና አስፈፃሚዎች ስልጠና ተሰጣቸው።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ት/ት ማጠናቀቂያ ፈተና አስፈጻሚዎች ሥልጠና እንደተሰጣቸው ገልጿል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ፈንታ ማንደፍሮ የፈተና አስፈፃሚዎች ትልቅ ኃላፊነት የተጣለባቸው መሆኑን በመገንዝብ በትጋትና በታማኝነት እንዲወጡ በማሳሰብ ዝርዝር የሥራ መመሪያ ሰጥተዋል።

የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በበኩላቸው ፤ የፈተና አስፈፃሚዎች በቂ ትኩረት በመስጠት ያለ ምንም አድልዎ ሙያዊ በሆነ አግባብ እንዲሁም በቁርጠኝነት የተጣለባቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ አስገንዝበዋል።

ዝርዝር ስልጠና በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አመራርና በዘርፉ ባለሙያዎች ተሰጥቷል።

የ2014 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ከመጪው መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ በሁለት ዙር ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ይሰጣል።

ፎቶ : የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
2.0K viewsedited  10:50
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-21 11:13:05 ለተፈታኞች የተፈቀዱ ነገሮች

ተፈታኞች ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጡ ይዘው እንዲመጡ እና ግቢ ውስጥ እንዲጠቀሙ የተፈቀዱ ነገሮች የሚከተሉት ናቸው፡፡

¤ አዲስ ወይም ቀድሞ ለመማርና ለማጥናት ሲጠቀሙበት የነበረ ማስተወሻ ደብተር፣ የትምህርት መጽሐፍ፣ መንፈሳዊ/ኃይማኖታዊ መጽሐፍት፣ ባዶ ወረቀት

¤ ደረቅ ምግቦች ወይም ሰንባች ምግቦች (ጩኮ፣ በሶ፣ ዳቦ ቆሎ፣ ቆሎ….)

¤ ገንዘብ (ብር)፣

¤ የልብስ ወይም የእጅ ቦርሳ፣ የግል ልብስ፣ ጫማ

¤ የግል ንጽህና መጠበቂያ ቁሳቁስ (ሳሙና፣ ሞዴስ፣ የጥርስ ብሩሽ፣ የጥርስ ሳሙና፣ የገላ ማድረቂያ ፎጣ፣ ሶፍት፣ ሻምፖ፣ ኮንዲሽነር፣ ሎሽን፣ ቻፕስቲክ፣ የጸጉር ቅባት፣ የፊት ቅባት)

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
3.2K views08:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-21 11:12:10 የተፈታኞች ግዴታ

ተፈታኞች የሚከተሉት ግዴታዎች አለባቸው፡፡
¤ ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕከልም ይሁን መፈተኛ ክፍል አድሚሽን ካርድ ይዞ የመገኘት ግዴታ አለበት፡፡

¤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ የትምህርት ቤት ወይም የነዋሪነት መታወቂያ ይዞ መገኘት አለበት፡፡

¤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ግቢ ከመግባቱ በፊትና ወደ መፈተኛ ክፍል ከመግባቱ በፊት ሙሉ አካላዊ ፍተሻ የመፈተሽ ግዴታ አለበት፡፡

¤ ማንኛውም ተፈታኝ በዩኒቨርሲቲ ግቢና በመፈተኛ ክፍል የተከለከሉ ቁሳቁሶችን ዕቃዎችን መያዝ የለበትም፡፡

¤ ማንኛውም ተፈታኝ እርሳስ፣ ላጲስና የእርሳስ መቅረጫ ይዞ መገኘት አለበት፤

¤ ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብን የማክበር ግዴታ አለበት፡፡

¤ ማንኛውም ተፈታኝ በፈተና ማዕከል ውስጥና በመፈተኛ ክፍል ውስጥ የፈተና አስፈጻሚዎች የፈተና አስተዳደር ሥራን ውጤታማ ለማድረግና ሁኔታዎችን ለማመቻቸት የሚያደርጉትን ጥረት የመተባበር ግዴታ አለበት፡፡

¤ ማንኛውም ተፈታኝ ፈተና ከመጀመሩ በፊት መፈተኛ ክፍል የመገኘት ግዴታ አለበት፡፡

¤ ተፈታኙ ፈተናው ሳይጠናቀቅ ከፈተና ክፍል የሚወጣ ከሆነ የፈተና ጥያቄ የያዘውን ቡኩሌት ለፈታኙ የማሰረከብ ግዴታ አለበት፡፡

¤ ማንኛውም ተፈታኝ ወደ ተመደበበት ዩኒቨርሲቲ ሲመጣ አንሶላ፣ ብርድልብስና የትራስ ጨርቅ ይዞ የመምጣት ግዴታ አለበት።

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
2.7K viewsedited  08:12
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-19 11:55:26
በኦሮሚያ ክልል ላሉ ተማሪዎች የ መፈተኛ ማዕከል

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
3.7K views08:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-19 11:54:31
የ2014 የ12ኛ ክፍል የአዲስ አበባ Entrance ፈተና መፈተኛ ቦታ ምደባ ይፋ ሁኗል።

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
3.3K viewsedited  08:54
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-16 21:08:34 በአማራ ክልል በቅርቡ ለሚሰጠው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች የተላለፈ አስቸኳይ መልዕክት፡፡

የ2014 /2015 ዓ.ም በአማራ ክልል የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎች ከመስከረም 30/2015 ዓ.ም ጀምሮ በክልሉ ባሉ ዩኒቨርስቲዎች ፈተናው እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወሳል፡፡

በመሆኑም ተፈታኝ ተማሪዎች ቀድመው ሊዘጋጁባቸው የሚገቡ ዋና ዋና ነጥቦች እንደሚከተለው ይቀርባሉ፡፡

1. ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች በፈተና ማዕከልም ይሁን በመፈተኛ ክፍል አድሚሽን ካርድ ይዞ መገኘት ግዴታ በመሆኑ አድሚሽን ካርድ ፎርም ከሞሉበት ትምህርት ቤት እና ወረዳ በአካል በመገኘት እስከ መስከረም 10/2015 ዓ.ም እንዲረከቡ፡፡

2. በአድሚሽን ካርዱ ላይ የስም፣ የስትሪም እና የጾታ ወዘተ..ስህተት ካለ በአስቸኳይ ለትምህርት ቤቱ እና ለወረዳው ሪፖርት እንድታደርጉ በጥብቅ እያሳሰብን ይህንን የማያደርጉ ተማሪዎች ካሉ ፈተና ለመውሰድ እንደሚቸገሩ፤

3. ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲመጡ የትምህርት ቤት ወይም የኗሪነት መታወቂያ ይዞ መገኘት የሚገባ መሆኑ፤

4. ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች በፈተና ጊዜ እርሳስ፣ ላጲስና የእርሳስ መቅረጫ ይዘው መገኘት ያለባቸው መሆኑ ከዚህ ዉጭ ሌሎች ቁሳቁሶችን በዩኒቨርሲቲ ግቢ እና በመፈተኛ ክፍል መያዝ የተከለከለ መሆኑ፤

5. ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ትምህርት ቤቱ፣ ወረዳው እና ዞኑ በሚያዘጋጀው የጉዞ ፕሮግራም መሰረት ወደ መፈተኛ ዩኒቨርሲቲ የሚጓዙ መሆኑን በመረዳት ዝግጅት ማድረግ ያለባቸው መሆኑን፤

6. ሁሉም ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ተመደበበት ዩኒቨርሲቲ ሲሄድ አንሶላ፣ ብርድልብስና የትራስ ልብስ ይዞ የመምጣት ይኖርባቸዋል፡፡

ይህን መረጃ ሸር በማድረግ ለተማሪዎችና ተማሪ ወላጆች እንዲሁም የሚመለከታቸው አካላት እንዲደርስ ትብብራችሁን እንድታደርጉ በተፈታኝ ተማሪዎች ስም ቢሮው ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ
ባህርዳር

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ ! !

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
4.7K viewsedited  18:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-16 08:08:39
#FAKE 

የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና መቃረብን ተከትሎ የተለያዩ ሀሰተኛ መረጃዎች በስፋት እየተሰራጩ በመሆኑ ተማሪዎች እንዲሁም የተማሪ ወላጆች ጥንቃቄ ልታደርጉ ይገባል።

" የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ተሸጋገረ " እየተባለ በአንዳንድ የማህበራዊ ገፆች ላይ የሚሰራጨው መረጃ ምንጩ የማይታወቅ በትምህርት ሚኒስቴር ሆነ በሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ያልተገለፀ ነው።

ተማሪዎች ከፈተና ጋር በተያያዘ ማንኛውም አዲስ መረጃ ሲኖር በትምህርት ሚኒስቴር / በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገፆች እንዲሁም በህዝብ መገናኛ ብዙሃን የሚገለፅ መሆኑን በማወቅ በሀሰተኛ መረጃ ሳትረበሹ ተረጋግታችሁ ዝግጅታችሁን ልታደርጉ ይገባል።

የተማሪ ወላጆችም ትክክለኛና የተረጋገጡ መረጃዎች በትክክለኛ የመስሪያ ቤቶቹ አድራሻ እንዲሁም በህዝብ መገናኛ ብዙሃን የሚነገሩት መሆናቸውን በማስገንዘብ ልጆቻችሁ እንዳይረበሹ ልታድርጉ ይገባል።

ተፈታኝ ተማሪዎች እንዲረበሹና የለፉበት ዝግጅታቸው እንዲደናቀፍባቸው የሚያደርጉ ሀሰተኛ የፈጠራ ወሬዎችን የምታሰራጩ አካላት ድርጊታችሁ ፍፁም ተገቢ ያልሆነ ፤ በትውልድ ላይም አሉታዊ ተፅእኖ ያለው መሆኑን በማወቅ ከድርጊታችሁ ልትታቀቡ ይገባል።

ተማሪዎች ምንጩ የማይታወቅ እና የተለያዩ አካላት ተከታይ ለማፍራት እንዲሁም ሆን ብለው ተማሪ እንዲረበሽ ለማድረግ ሲሉ በማህበራዊ ሚዲያ የሚያሰራጩትን መረጃ ወደ ጓደኞቻችሁ ባለመላክ ሀሰተኛ መረጃዎችን ተከላከሉ።

መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን JOIN እና ሼር ያድርጉ ! !

@TMIHIRT_MINISTER
@TMIHIRT_MINISTER
4.0K viewsedited  05:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-15 22:08:31
በ2015 በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት (ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል) አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ እንደሚሆን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

በተመሳሳይ፣ የ9ኛ እና 10ኛ ክፍል አዲሱ ሥርዓተ-ትምህርት ከኹሉም ክልሎች እና ከተማ መስተዳድሮች በተመረጡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሙከራ ትግበራ ይጀመራል ሲሉ የሚኒስቴሩ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ሥራ አስፈጻሚ አመለወርቅ ህዝቅኤል ተናግረዋል።

በአገር አቀፍ ደረጃ ሰኞ መስከረም 9 ቀን 2015 ለሚጀመረው ትምህርት የተለያዩ ዝግጅቶች ማድረጉን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።ሰኞ ዕለት በይፋ ለሚጀመረው ትምህርት በአብዛኞቹ ትምህርት ቤቶች የመክፈቻ ሥነ ስርዓት እንደሚያካሄድም አመለወርቅ ገልጸዋል።

ተማሪዎች ደስ ብሏቸው የትምህርት ቀኑን እንዲጀምሩ የተለያዩ ዝግጅቶች በየትምህርት ቤቶቹ እንደሚካሄዱ የገለጹት ኃላፊዋ፣ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመጡ በክልል ያሉ ትምህርት ቢሮዎች፣ ትምህርት ቤቶች እና የተለያዩ ድርጅቶች በትምህርት ቤት ውስጥ መዝናኛ ዝግጅት አዘጋጅተው ተማሪዎችን የመቀበል ሥነ ስርዓት ያካሄዳሉ ብለዋል።

የክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች፣ መምህራንን እና ማህበረሰቡ በትምህርቱ የጊዜ ሰሌዳ እና በሥርዓተ ትምህርቱ አፈጻጸም ላይ ውይይቶችን እንዳደረጉ ወ/ሮ አመለወርቅ መጠቆማቸውን ኢቢሲ ዘግቧል።ትምህርት ቤቶች የመማር ማስተማር ሥራ ከመጀመራቸው በፊት የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ሲከናወኑ መቆየቱን ያወሱት የኮሚዩኒኬሽን ኃላፊዋ፣ በዚህም የትምህርት ቤቶች እድሳት፣ የአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የመጽሐፍት ማስተዋወቅ እና የትምህርት ጉባዔ የማካሄድ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል።

https://t.me/Tmihirt_Minister
https://t.me/Tmihirt_Minister
3.6K viewsedited  19:08
ክፈት / አስተያየት ይስጡ