Get Mystery Box with random crypto!

Skyline media

የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media S
የቴሌግራም ቻናል አርማ skyline7777 — Skyline media
የሰርጥ አድራሻ: @skyline7777
ምድቦች: መኪናዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 49.60K
የሰርጥ መግለጫ

ይህ የኢትዮ ስካይላይን የቴሌግራም ቻናል ነው። 🙌 ዓላማችን እናንተን ውድ ተከታታዮቻችንን በቅድሚያ ማሳወቅ ፣ ማስተማርና ዘና ፈታ የሚያደርጉ ርዕሰ ጉዳዩች ላይ በማተኮር ማገልገል ነው 🙌
ቁም ነገሮች፣ ቀልዶች፣fun GIF:ትረካዎች:
መጣጥፎች ሌሎችንም ዜናዎች የሚያገኙበት ምርጥ ቻናል🤗
ለጥቆማና አስተያየታችሁ
For any promotion 👉 @Skyline7777

Ratings & Reviews

5.00

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

3

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 29

2022-09-01 15:42:59 ማስራብ›› የአሸባሪው ህወሓት የትግል ስልት

አሸባሪው ህወሓት ከወራት በፊት ወደ  አፋርና አማራ ክልል ያደረገው ወረራ ተቀልብሶ በመቀሌ ከመሸገ ወዲህ ከዓለም አቀፍ ድርጅቶች የሚላከውን የእርዳታ እህል ከዜጎች በመንጠቅ ለቀጣይ ግዳጅ የመለመላቸውን ታጣቂዎች ሲቀልብ የከረመ ሲሆን፤ በዚህም የተነሳ ሕዝቡ  በከፋ ረሐብ እየማቀቀ ይገኛል፤ መከራውም በዝቷል፡፡

ደብረጽንም በቅርቡ በውጭ ከሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ጋር በዙም ያደረገውና አፈትልኮ በወጣው ምስጢራዊ ውይይት ‹‹በቂ የሰብአዊ አቅርቦት ካለ የትግራይ ሕዝብ አሁንም ለምን በችግር ይማቅቃል፤ የእርዳታ እህል ለታጣቂዎች ታከፋፍላላችሁ የሚባለው እውነት ነው?›› የሚል ጥያቄ ቀርቦለት በሰጠው ምላሽ ‹‹አዎ የእርዳታ እህል ለታጣቂዎች እናከፋፍላለን፡፡ ታዲያ ምን እንቀልባቸው፡፡ ሰው ሳይበላ አይዋጋም፡፡ ጦርነት አይቀሬ ነው፡፡ ከጦርነት ውጪ አማራጭ የለንም፡፡ ህጻናትም አዛውንትም በግንባር ይሰለፋሉ፡፡›› በማለት ምላሽ መስጠቱ የሚታወስ ነው፡፡

ታዲያ ቃል በተግባር እንዲሉ፤ ሕዝብን ሆን ብሎ በማስራብ፤ ቁጭ ብለህ ከምትራብ ደግሞ ዝመት የሚል ስልት በመጠቀም ህጻናትና አዛውንትን ሳይቀር በጦርነት እየማገዱ የሚገኙት የአሸባሪው ቡድን መሪዎች ዛሬም ወረራውን ከማስፋት አልተቆጠቡም፡፡ ትናንት ምንም ውጤት ያላስገኘውን ጦርነት በመድገምም ሕዝብን ለከፋ ሰቆቃና ረሐብ እየዳረጉ ነውና ሕዝቡም በቃችሁ ሊላቸው ይገባል፡፡
3.3K viewsTopia Media, 12:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-29 11:15:54 https://fb.watch/fcbQ6CgIFq/
1.3K viewsTopia Media, 08:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-27 10:57:05 ወሳኝ የጥንቃቄ መልዕክት ሼር! ሼር!

ይሄንን መረጃ ያገኘሁት ከማህበራዊ ሚዲያ በተለይም ከጁንታው ደጋፊዎች ዘንድ ውስጥ ውስጡን ሲዘዋወር ነው።
ሃገር ቤት ያላችሁ የሰራዊትን እንቅስቃሴ ከመጠቆም መቆጠብ አለባችሁ።
እኔ ያየሁት መረጃ ይሄንን ይመስላል።

{"ጥብቅ መረጃ!!

ምሽቱን ከባባድ የጭነት መኪናዎች፣ ሜካናይዝድ የጦር መሣሪያዎችን የጫኑ ተሳቢዎች እና ተደጋጋሚ የአየር በረራዎችን በመጠቀም የብልጽግና መንግሥት ቁጥሩ ከፍተኛ የሆነ ኮማንዶ ተዋጊ ኃይል ከአዲስ አበባና ከምዕራብ ወደ ምሥራቅ አካባቢ ሲያንቀሳቅስ ማደሩን ከውስጥ ምንጮች ማወቅ ተችሏል።

የዐቢይ ሠራዊት ይህን ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተዋጊ ኃይልና የጦር መሣሪያ ወደ ምስራቅ ግንባሮች ማለትም ወደ ዓፋር ማስገባቱ በቀጣይ በዚህ ግንባር መጠነ ሰፊ ዘመቻ ለመጀመር ያለውን ዕቅድ የሚያሳይ ሲሆን በሚቀጥሉት ሁለትና ሦስት ቀናት ውስጥም ወደ ኦፕሬሽን ሊገባ እንደሚችል ምንጮቻችን ገልፀዋል።"}
እንዲህ አይነት ሚስጥር ማውጣት ለጠላት መረጃ እንደመላክ ይቆጠራል። እንጠንቀቅ። የሰራዊቱን እንቅስቃሴ ከመግለጽ እንቆጠብ።
https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=112805584881597&id=107429748752514
4.4K viewsTopia Media, 07:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-26 22:04:09
በጉጉት ስጠበቅ የነበረዉ "ዎላይታ በዘመናዊቷ ኢትዮጵያ" የተሰኘው የታሪክ መጻሐፍ ምረቃ ፕሮግራም ይፋ ሆነ

መጽሐፉ በአማርኛ ቋንቋ ስለዎላይታ ህዝብ ታሪክና በኢትዮጵያ ሀገር ግንባታ ላይ ህዝቡ ስላበረከተው አስተዋፅኦ የሚያትት ስሆን መስከረም 7/2015 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ጀምሮ አዲስ አበባ 4ኪሎ በሚገኘዉ አብሮሆት ህዝብ በተመጻህፍት አዳራሽ ይመረቃል።

የታሪኩ ጸሐፊ አማኑኤል አብርሃም ባባንቶ እጅግ ባማረ አጻጻፍ እንደከተበዉ ታላላቅ ባለሙያዎች አስተያየታቸውን አስቀምጠዋል።

ፀሐፊው ከዚህ ቀደምም "የመረጃ ነፃነት በኢትዮጵያ" በሚለው መጽሐፉ በኢትዮጵያ የተጀመረው ለውጥ በምን መልኩ መጠናከር እንዳለበት የበኩሉን ድርሻ ተወጥቷል።

በጋዜጠኝነት፣ በፖለቲካ አመራርነት አሁን ደግሞ በዲፕሎማሲው ረገድ ያካበተውን ልምድ ተጠቅሞ ታሪካችንን የሚያድስ ገፀ በረከት ይዞ ብቅ ብሏል።

ከመጽሐፉ ሽያጭ ለአካባቢው ልማት ቃል የገባ መሆኑ እጅግ የሚያስመሰግን ለሌሎች ደራሲያን መልካም አርአያ እና በር የከፈተ በመሆኑ ክብር አለን!!!

መጽሐፉ በወልማ አማካኝነት በሁሉም ቅርንጫፍ ባለባቸው አከባቢ የሚሸጥ ስለሆነ በፖስተሩ ባለው ስልኮች ደዉለዉ መግዛትና ማንበብ ይቻላል።

ገዝተው እንዲያነቡት ለወዳጅ ዘመድም እንዲያጋሩት ተጋብዘዋል!
መልካም ንባብ

ታሪክ ሳይዛባ ከትቦ ማለፍ ለዛ ማህበረሰብ ቀጣይነት ወሳኝ ነው! !
4.9K viewsNatnael Gecho, 19:04
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-25 17:09:55 https://wolaitatimes.com/u-n-says-tplf-stole-570000-liters-of-fuel-from-wfp-warehouse/
5.6K viewsNatnael Gecho, 14:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 16:25:09
አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ከአንጎላ ጠቅላላ ምርጫ ባለድርሻ አካላት ጋር ተወያዩ

የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድንን የሚመሩት የቀድሞ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ከአንጎላ ጠቅላላ ምርጫ ባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይተዋል፡፡

አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በቅድመ ምርጫ ውይይታቸው የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮችን ጨምሮ ከተለያዩ ምርጫ አስፈጻሚ አካላት ጋር መክረዋል።

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የአንጎላ ብሔራዊ ምርጫ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ዶክተር ማኑኤል ዳ ሲልቫንም ማነጋገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

የአንጎላ ጠቅላላ ምርጫ በመጪው ረቡዕ እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡
9.8K viewsNatnael Gecho, 13:25
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 18:49:45
በአዲስ አበባ በደረሰ የህንፃ መናድ " እስካሁን የ6 ሰዎች ህይወት ማለፉን የከተማው ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ።

ህንፃው የተደረመሰው በአዲስ አበባ ከተማ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዪ ቦታው መሃል አዳራሽ በሚባል አካባቢ አንድ አሮጌ ህንፃ በመናዱ ምክንያት በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡

እስካሁን ባለው መረጃ 6 ሰው የሞተ ሲሆን ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች ላይም ከባድ እና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል::

ፖሊስ የአደጋውን መንስኤ እና ያስከተለውን ጉዳት እያጣራ ይገኛል ስል አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አሳውቋል።
8.8K viewsNatnael Gecho, 15:49
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 13:55:35 https://www.facebook.com/107429748752514/posts/pfbid02C8sJYz7rus7wHTNFtXCSXoyYxUZn9dTk2JZnRd2uKwxQFvhcqNRZKroG6magC4bol/?sfnsn=mo
7.8K viewsAnt B, 10:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-18 12:05:46 12ኛ ክልል እንዲቋቋም ህዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ተወሰነ

የፌዴሬሽን ምክር ቤት በክልል የመደራጀት አቤቱታን ተቀብሎ በመመርመር ሕዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ፈቀደ

የፌዴሬሽን ምክር ቤት በደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ስር የነበሩ 6 ዞኖችና 5 ልዩ ወረዳዎች በአንድ ክልል እንዲደራጁ የቀረበውን የውሳኔ ሀሳብ ተቀብሎ ሕዝበ ውሳኔ እንዲካሄድ ወስኗል።

በአዲስ ክልል እንዲደራጁ ምክር ቤቱ የውሳኔ ሃሳብ ተቀብሎ የወሰነላቸውም የዎላይታ ዞን፣ የጋሞ ዞን፣ የጎፋ ዞን፣ የደቡብ ኦሞ ዞን፣ የጌዴኦ ዞን፣ የኮንሶ ዞን፣ እንዲሁም የደራሼ ልዩ ወረዳ፣ የአማሮ ልዩ ወረዳ፣ የቡርጂ ልዩ ወረዳ፣ የአሌ ልዩ ወረዳ እና የባስኬቶ ልዩ ወረዳ መሆናቸው ተመላክቷል።

በሌላ በኩል ቀሪዎቹ በደቡብ ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ስር የሚገኙ የሀድያ ዞን፣ ሀላባ ዞን፣ ከንባታ ጠንባሮ ዞን፣ ጉራጌ ዞን ስልጤ ዞን እና የም ልዩ ወረዳ በነባሩ ክልል እንደሚቀጥሉ ተገልጿል።
9.1K viewsNatnael Gecho, 09:05
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 17:46:53

8.2K viewsNatnael Gecho, 14:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ