በአዲስ አበባ በደረሰ የህንፃ መናድ " እስካሁን የ6 ሰዎች ህይወት ማለፉን የከተማው ፖሊስ ኮሚሽን ገለፀ። ህንፃው የተደረመሰው በአዲስ አበባ ከተማ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ልዪ ቦታው መሃል አዳራሽ በሚባል አካባቢ አንድ አሮጌ ህንፃ በመናዱ ምክንያት በሰው ሕይወትና በንብረት ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡ እስካሁን ባለው መረጃ 6 ሰው የሞተ ሲሆን ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች ላይም ከባድ እና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸዋል:: ፖሊስ የአደጋውን መንስኤ እና ያስከተለውን ጉዳት እያጣራ ይገኛል ስል አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አሳውቋል። 8.8K viewsNatnael Gecho, 15:49