አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ከአንጎላ ጠቅላላ ምርጫ ባለድርሻ አካላት ጋር ተወያዩ
የአፍሪካ ህብረት የምርጫ ታዛቢ ቡድንን የሚመሩት የቀድሞ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ከአንጎላ ጠቅላላ ምርጫ ባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይተዋል፡፡
አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በቅድመ ምርጫ ውይይታቸው የተፎካካሪ ፓርቲ አመራሮችን ጨምሮ ከተለያዩ ምርጫ አስፈጻሚ አካላት ጋር መክረዋል።
የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር የአንጎላ ብሔራዊ ምርጫ ኮሚሽን ፕሬዝዳንት ዶክተር ማኑኤል ዳ ሲልቫንም ማነጋገራቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
የአንጎላ ጠቅላላ ምርጫ በመጪው ረቡዕ እንደሚካሄድ ተገልጿል፡፡