2022-09-03 08:06:34
ለመከላከያ ሰራዊት አባልነት የወጣ የቅጥር ማስታወቂያ!
የሀገር መከላከያ ሚኒስቴር ከነሐሴ 26/ 2014 ዓ.ም እስከ መስከረም 10/2015 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ መስፈርቱን የሚያሟሉ ወጣቶችን መልምሎ በመደበኛ ሰራዊትና በእጩ መኮነንነት በማሰልጠን የሀገር መከላከያ ሠራዊት አባል ማድርግ ይፈልጋል ፤
የመመልመያ መስፈርቶች ፦
1. ህገ- መንግስቱን የተቀበለ/ች ለዚህ በፅናት ለማገልገል ፈቃደኛ የሆነ/ች
2. በብሔር-ብሔረሰቦችን እኩልነት የሚያምን /የምታምን
3. ከአሁን በፊት የፖሊስ ወይም የመከላከያ አባል ያልነበረ/ች
4. ከወንጀል ነፃ የሆነ የፍርድ ቤት ቀጠሮና ክርክር የሌለበት/ባት
5. ከማንኛውም ሱስና አጉል ልማድ የፀዳ/ች እና ሙሉ ጤንነት ያለው/ያላት
6. በመከላከያ ለ7 ዓመት ለማገልገል ፈቃደኛ የሆነ/ች በማንኛውም ቦታ ተመድቦ መስራት የሚችል/የምትችል
7. ፆታ፡- አይለይም
8. ኢትዮጵያዊ የሆነ/ች በሚኖርበት ቀበሌ 2 ዓመት የኖረ/ች
9. ዕድሜ፡- ከ18-25 አመት ፤ ቁመት ለወንድ 1.60 እና ከዚያ በላይ ፣ ለሴት ደግሞ 1.55 እና ከዚያ በላይ የሆነ/ች
10. ክብደት፡-ለወንድ ከ50-75 ኪ.ግ የሆነ ለሴት ደግሞ 45-66 ኪሎግራም የሆነች፣
11. የትምህርት ማስረጃ፦ ለወንድ 6ኛ ክፍል ያጠናቀቀ እና ለሴት እወቅና ካለው የትምህርት ተቋም ዲፕሎማ ወይም በሌቭል ያጠናቀቁ እና ከዚያ በላይ የሆኑ የ 8ኛ ክፍል የሚኒስቲሪ ካርድ ማቅርብ የሚችሉ ፣
12. ያላገባ/ችና ያልወለደ/ች
13. ደመወዝ በመከላከያ ስኬል መሰረት ሆኖ ጥቅማጥቅም የመኖሪያ ቤትና ህክምና አገልግሎት በነፃ የሚያገኙ ሲሆን በመከላከያ ዕቅድና ፍላጎት መሰረት በትምህርት ተቋም ገብተው የመማር ዕድል አላቸው፣
14. የምዝገባ ቦታ ፦ በሁሉም የክልል ከተሞች የፀጥታ ተቋማት ቢሮ( ሚሊሻ ፤ ፖሊስ ፤ ሰላምና ደህንነት ቢሮዎች )
15. የምዝገባ ቀን፡- ከነሐሴ 26/2014 ዓ/ም ጀምሮ አስከ መስከረም 10/2015 ዓ/ም ዘወትር በሥራ ስዓት እንዲሁም ቅዳሜ እና እሁድን ጨምሮ
ማሳሰቢያ፡- በምዝገባ ወቅት መቅረብ የሚገባቸው ማስረጃዎች የቀበሌና የፖሊስ የድጋፍ ደብዳቤ፣ የትምህርት ማስረጃ ኦርጂናልና ፎቶ ኮፒ እንዲሁም የቀበሌ መታወቂያ በዘመኑ የታደሰ ያስፈልጋል።
https://t.me/Skyline7777
https://t.me/Skyline7777
3.4K viewsTopia Media, edited 05:06