Get Mystery Box with random crypto!

Our World

የቴሌግራም ቻናል አርማ ourworl_d — Our World O
የቴሌግራም ቻናል አርማ ourworl_d — Our World
የሰርጥ አድራሻ: @ourworl_d
ምድቦች: ቴክኖሎጂዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 894

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 7

2022-08-01 11:37:00
አንዴ ከሄዱ ብትለምኗቸው የማይመለሱ አራት ነገሮች!


በሕይወታችሁ እንደገና ለመመለስ የሚያስቸግሯችሁ አራት ነገሮች፡-

“እድል” - አንዴ ካመለጣችሁ በኋላ!

“ቃል” - አንዴ ከአንደበታችሁ ከወጣ በኋላ!

“ጊዜ” - አንዴ ሳትጠቀሙበት ካለፈ በኋላ!

“አመኔታ” አንዴ ከጎደለ በኋላ ለመመለስ አስቸጋሪ ነው፡፡

1. “እድል” - በአጋጣሚም ሆነ ጠንክራችሁ በመስራታችሁ የመጣን እድል መለየት፣ ማክበርና በተገቢው ሁኔታ መጠቀም፡፡

2. “ቃል” - ሁኔታዎች ሲገፋፏችሁም ሆነ እንዲሁ ስለለመደባችሁ በቀላሉ የምትናገሯቸውን ሰው ጎጂ ንግግሮች በሚገባ ማሰብና ራስን መግታት፡፡

3. “ጊዜ” - በሆነ ባልሆነ የምታባክኑትና አሁን ባላችሁ እድሜ ማድረግ የሚገባችሁን ነገር ባለማድረግ የምታባክኑትን ጊዜ በጥንቃቄ መያዝ

4. “አመኔታ” - ሰዎች ሲያምኗችሁና ራሳቸውንም ሆነ ነገሮቻቸው በእናንተ ላይ ሲጥሉ እምነት ከማጉደል መጠበቅ፡፡

፣ ያለፈው አልፏል፣ የባከነው ባክኗል፡፡ የተራረፈውን እንሰባስበውና ሕይወትን እንደገና በአዲስ መልክ እንጀምር፡፡

ከዶ/ር እዮብ ማሞ የተወሰደ

***
175 viewsBekele Ejeta, edited  08:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 11:24:50 የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ሳሙኤል በ2015 ዓ.ም መጨረሻ ጀምሮ እንደሚተገበር በሚጠበቀው የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ዙሪያ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰደ

የዩኒቨርስቲ መዉጫ ፈተና ምንድነዉ?

ብቁ የሰው ሃይል በማዘጋጀት ወደ ኢኮኖሚ መግባቱን ማረጋገጫው አንደኛው መንገድ ነዉ::

ተመራቂዎች በተማሩበት ሙያ፤ ዘመኑ የሚጠይቀውን እውቀት፣ክህሎትና አመለካከት ገንብተው ስለመውጣታቸው የሚመዝን ነዉ፡፡

ዲግሪ በያዙ ተመራቂዎች መካከል በብቃት የሙያውን ምሉዕነት ተላብሶ የተመረቀው የትኛው እንደሆነ ይመዝናል

ምዘናዉ ለማን ይሰጣል?

ምዘናው የሚሰጠው በመጀመሪያ ዲግሪ ላይ ብቻ ነዉ

ትግበራው አገራዊ ፖሊሲ እንደመሆኑ በግል፣ በመንግስትም በየትኛውም ተቋም የሚማር ዲግሪውን የሚያገኘው ምዘናውን ካለፈ ነዉ፡፡

ምዘናዉ ለምን እና በማን ይሰጣል?

ተማሪዎች ሲገቡ እንጂ ለምን ወውጫ ላይ ይፈተናሉ የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ቢሆንም ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡት የሁለተኛ ደረጃ መልቀቂያ ተፈትነው መሆኑን መዘንጋት አይገባም

የከፍተኛ ትምህርት አዋጅ 1152/2011 የመውጫ ፈተና ሊሰጥ እንደሚችል በግልጽ አስቀምጧል፡፡ የሪፎም አካል ነው፣

የሪፎም አጀንዳን መንግስት የሚመራው እንደመሆኑ ሂደቱን ትምህርት ሚኒስቴር መንግስትን ወክሎ የሚሰራዉ ነዉ፡፡

ምዘናዉን ለማካሄድ ምን እየተሰራ ነዉ ?

ትምህርቶቹን የሚያዘጋጁ ተቋማትና መምህራን የዝግጅት ስራዎች እስከ ግንቦት 2015 ዓ.ም ይሰራሉ
61 viewsBekele Ejeta, edited  08:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-01 06:33:15 #ትምህርት_ሚኒስቴር

የ2014 12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን በ12 ኮድ (በጥያቄ አቀማመጥ ስብጥር) ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው።

የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከዚህ በፊት እንደነበረው በ4 ኮድ (4 የተለያዩ ፈተናዎች/በጥያቄ አቀማመጥ) ሳይሆን እስከ 12 እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል።

ይህ የፈተና ኩረጃን ለመከላከል ከሚሰሩት ስራዎች መካከል አንዱ መሆኑን የሚገልፁት ፕ/ር ብርሃኑ ጎን ለጎን ያሉ ተማሪዎች እርስ በእርስ የሚፈተኑት ፈተና የጥያቄው ዝርዝር (order) በፍፁም የተገናኘ እንዳይሆን እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል።

ፈተናው በዩኒቨርሲቲዎችና በፌዴራል ተቋማት እንደሚሰጥም ገልፀዋል።

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ለኢፕድ የሰጡት ቃል፦

" ...የክልል ባለሟሎች፣ የክልል ኃላፊዎችን ከፈተና ጉዳይ ጋር እንለያቸው ፤ ፈተናው እራሱ የፌዴራል ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ስለሆነ በፌዴራል ተቋማት ውስጥ ብቻ እንስጥ ብለን አሁን በሙሉ ተማሪዎቹን አጓጉዘን ቢቻል ሁሉንም ከክልላቸው ውጭ በሆኑ ክልሎች ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች እና የፌዴራል ተቋማት ውስጥ ለመስጠት ነው እየተዘጋጀን ያለነው።

ያ የሚያደርገው ሁለት ነገር ነው። አንደኛ በመንገድ ላይ ሊኖር የሚችለውን የመሰረቅ አደጋ ይቀንሰዋል። ሁለተኛ ክፍል ውስጥ ከተገባ በኃላ ለመስረቅ የሚቻልበትን አደጋ ይቀንሰዋል።

ከዛም በላይ ፈተናዎቹን በማዘጋጀት ደረጃ በፊት በ4 የተለያዩ ፈተናዎች ነበር የምናዘጋጀው እስከ 12 አድርገን Completely scrambled እንዲሆኑና ማንም ጎኑ ያለው ተማሪ የሚፈተነው ፈተና አንተ ከምትፈተነው ፈተና order ጋር በፍፁም ያልተገናኘ እንዲሆን አድርገን እየሰራን ነው።

ይሄ በጣም በብዙ ደረጃ የፈተና ስርቆትን ይቀንሰዋል ብለን ነው ተስፋ የምናደርገው። "

ኢፕድ/ቲክቫህ


65 viewsBekele Ejeta, 03:33
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 20:51:04
ከቁጥጥር ውጭ የሆነችው የቻይና ‘Long March-5B’ ሮኬት አካል በከፍተኛ ፍጥነት ወደ ምድር እየተምዘገዘገች መሆኑ በረካቶች ዘንድ ስጋትን ፈጥሯል።

የሮኬቱ ስባሪ በመጪዎቹ ሶስት ቀናት ውስጥ ምድር ላይ ሊወድቅ ይችላል የተባለ ሲሆን፤ በተለይም ሰኞ እለት ምድር ለይ ሊደርስ እንደሚችል ተነግሯል።

አሁን ላይ ባለው ሁኔታ ሮኬቱ በየትኛው ስፍራ ላይ ሊወድቅ እንደሚችል መገመት አዳጋች ቢሆንም፤ ሰዎች በብዛት የሚኖሩበት ስፍራ ላይ ሊወድቅ ይችላል የሚል ስጋትም ቀስቅሷል።
መቀመጫውን አሜሪካ ካሊፎርኒያ ያደረገው ለትርፍ ያልተቋቋመው ኤሮስፔስ ኮርፖሬሽን እንዳስታወቀው፤ ወደ ምድር እየተምዘገዘገ ያለው የሮኬቱ ስባሪ 25 ቶን አሊያም 25 ሺህ ኪሎ ግራም እንደመሚዝን አስታውቋል።
ሮኬቱ መቼ ምድር ላይ ይወድቃል የሚለውን ሙሉ በሙሉ መገመት ባይቻልም ሰኞ ማለዳ ላይ ሊሆን እንደሚችል ግን ተቋሙ ግምቱን አስቀምጧል።
ስብርባሪው የሚወድቅበትን ስፍራ ለማወቅ ገና ነው ያለው ከቋሙ፤ አሜሪካ፣ አፍሪካ፣ ብራዚል፣ ህንድ ወይም ደቡብ እሲያ ላይ ሊወድቅ ይችላል ብሏል።
ቻይና ሎንግ ማርች 5 የተባለ ሮኬቷን ባሳለፍነው እሁድ ወደ ጠፈር ማምጠቋን ማስታወቋ ይታወሳል።

የቻይና መንግስት ባሳለፍነው ረቡዕ እንዳስታወቀው፤ የሮኬቱ ስብርባሪ በምድር ላይ ለሚገኝ ማንኛውም አካል መጠነኛ ስጋት ሊፈጥር እንደሚችል በመግለፅ፤ ነገር ግን ስባሪው ውሃ ላይ የመውደቅ እድሉ ሰፊ መሆኑን አስታውቋል።
ሆኖም ግን የሮኬቱ ስብርባሪ አካል ሰው በብዛት ወደሚኖርበት አካባቢ ላይ የመውደቅ እድል እንዳለው ተነግሯል።

በፈረንጆቹ 2020 ላይ ከቁጥጥር ውጪ የሆነ የሮኬት አከል በአይቮሪኮስት ወድቆ በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱ ይታወሰል።

#አልዓይን
21 viewsBekele Ejeta, edited  17:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 18:07:36
ጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የ5.5 ቢሊዮን ብር የብድር ስምምነት ተፈረመ።

በዛሬው ዕለት አዋሽ ባንክ መካከለኛ፣ አነስተኛና ጥቃቅን ኢንተርፕራይዞች የፋይናንስ አቅርቦት እንዲያገኙ ከዘጠኝ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማት ጋር የ5.5 ቢሊዮን ብር የብድር አቅርቦት ስምምነት አድርጓል።

ከባንኩ ጋር ይህን ስምምነት ያከናወኑት ዘጠኙ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋማት ቪዥን ፈንድ፣ ንስር፣ ቀንዲል፣ መተማመን፣ መክሊት፣ ዳይናሚክ፣ ዋሳሳ፣ ሃርቡ እና ፒስ አነስተኛ ፋይናንስ ተቋም ናቸው።

ማይክሮ ፋይናንስ እና ባንኩን በማስተሳሰር ትልቅ ሚና የተጫወቱት ማስተርካርድ ፋውንዴሽን እና ፈርስት ኮንሰልት ብሪጅ ፕሮገራም መሆናቸው በዕለቱ ተጠቅሷል።

ፈርስት ኮንሰልት ባቀረበው ማብራሪያ መሰረትም የ5.5 ቢሊዮን ብር ብድሩ 110ሺህ ኢንተርፕራይዞችን ተደራሽ የሚያደርግ ሲሆን በዚህም እስከ 330 ሺህ ወጣቶች እና ቤተሰቦቻቸው ተጠቃሚ የሆናሉ፡፡

የአዋሽ ባንክ ሥራ አስኪያ አቶ ፀሐይ ሽፈራው ባንኩ ከ2016ዓ.ም ጀምሮ ለጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የተለያዩ የብድር አቅርቦቶችን ማድረጉን በማስታወስ በቅርቡ ይፋ ባደረገው “ታታሪዎቹ” የተሰኘ የወጣት ሥራ ፈጣሪዎችን የሚያበረታታ ውድድር 8ሺህ አመልካቾችን ተቀብሎ እያወዳደረ መሆኑንም አንስተዋል።
34 viewsBekele Ejeta, edited  15:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-29 06:41:46

48 viewsBekele Ejeta, 03:41
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-28 02:57:58

6 viewsBekele Ejeta, edited  23:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 04:17:51
በህንድ መአዛ ያለዉን ኮንዶም አፍልተዉ የሚጠጡ ወጣቶች ቁጥር መበራከቱ ስጋት ፈጥሯል ተባለ

በህንድ በምዕራባዊ ቤንጋል ዱርጋፑር ከተማ ተማሪዎች ኮንዶም የመጠቀም ሱስ ዉስጥ ወድቀዋል ተብሏል፡፡የተለየ መዓዛ ያለዉ ኮንዶም ሽያጭ በከተማዋ የተለያዩ ክፍሎች በሚያስገርም ሁኔታ ጨምሯል፡፡ በዱርጋፑር ከተማ ቢድሃናጋር፣ ሙቺፓራ እና ቤናቺቲ፣ ሲ ዞን፣ ኤ ዞንን በተባሉ አካባቢዎች በሚገኙ የመድኃኒት መደብሮች ዉስጥ የኮንዶም ሽያጩ በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩ ተጠቁሟል፡፡

ተማሪዎቹ ኮንዶም በሞቀ ውሃ ውስጥ እየነከሩ ያቆያሉ፤ ከዚያም በኋላ ከ 10 እስከ 12 ሰአታት ድረስ ፈሳሹን እንደሚጠጡ ተነግሯል፡፡መዓዛ ያለዉን ኮንዶም ለመስራት ጥቅም ላይ የሚዉሉ ንጥረ ነገሮችን በሙቅ ውሃ ውስጥ ለረጅም ጊዜ በማቆየት የአልኮሆል ውህድ እንዲፈጠር ያደርጋሉ። ድርጊቱ ግን ዘላቂ ሱስ ከማስያዝ ባለፈ ለጤና እጅግ ጎጂ ስር የሰደደ እክል ሊፈጥር እንደሚችል የጤና ባለሙያዎች ተናግረዋል፡፡

ከዚህ ቀደም ከሶስት እስከ አራት ፓኬቶች ኮንዶም በአንድ ሱቅ በቀን ይሸጥ የነበረ ሲሆን አሁን ግን አንድ ጥቅል ሙሉ ኮንዶም በየቀኙ እንደሚሸጡ የመድኃኒት መደብር ባለሙያዎች ገልጸዋል፡፡
46 viewsBekele Ejeta, edited  01:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-26 03:55:44

28 viewsBekele Ejeta, edited  00:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-07-24 19:44:26
ዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ የዓለማችን አሳሳቢ የጤና ችግር መሆኑን የአለም ጤና ድርጅት አስታወቀ

በጥቂት አገሮች በቅርቡ የተከሰተው “የዝንጀሮ ፈንጣጣ” በሽታ የዓለማችን አሳሳቢ የጤና ችግር መሆኑን  የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ።

ድርጅቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ መሆኑንና ባልተጠበቀ ሁኔታ በዓለማችን በ70 ሀገራት ውስጥ በወረርሽኝ መልክ መከሰቱን ገልጿል።

በሽታው ክትባት ያልተገኘለትና ለሕክምናውም ከፍተኛ ኢቨስትመንት የሚጠይቅ በመሆኑ ሌላኛው የዓለማችን አሳሳቢ ወረርሽኝ ሆኗል ሲል የዓለም ጤና ድርጅት አውጇል።
15 viewsBekele Ejeta, edited  16:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ