Get Mystery Box with random crypto!

Our World

የቴሌግራም ቻናል አርማ ourworl_d — Our World O
የቴሌግራም ቻናል አርማ ourworl_d — Our World
የሰርጥ አድራሻ: @ourworl_d
ምድቦች: ቴክኖሎጂዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 894

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 4

2022-09-24 13:13:06 ሊባኖሳዊቷ ሳሊ ሃፊዝ ገንዘቧን ወደምትቆጥብበት ቤይሩት ውስጥ ወደሚገኘው ብሎም ባንክ ሄዳ ማናጀሩን ማናገር እንደምትፈልግ ነግራ ወደማናጀሩ ቢሮ በማምራት የመጣችበትን ጉዳይ ከእንባዋ ጋር እየታገለች አስረዳችው ።
..................
እኔ የዚህ ባንክ የአመታት ደንበኛ ነኝ ። በተደጋጋሚ እየመጣሁ ለባንክ ሰራተኞቹ ጉዳዬን ባስረዳም ምንም መፍትሄ ሊሰጡኝ አልቻሉም ። እህቴ በከፍተኛ ሁኔታ በካንሰር ተይዛ ህመም ላይ ነች ። ከህመሟ እንድታገግም ብር ያስፈልጋታል ። እናም እዚህ ባንክ የቆጠብኩትን 12 ሺህ ዶላር በሙሉ አውጥቼ እህቴን ከስቃይ ማዳን እፈልጋለሁ ። እርዳኝ ስትል ተማፀነችው ።
......................
የባንኩ ማናጀር ጉዳዩ አሳዛኝ ቢሆንም ፡ ለባንኮች በወጣው ህግ መሰረት ፡ በወር ከ200 ዶላር በላይ ሊሰጣት እንደማይችል ነገራት ። ሳሊ ሃፊዝ ይህን መልስ ወደባንኩ በተመላለሰች ቁጥር ሰምታዋለች ። ዛሬ ማናጀሩን ቀርባ ያናገረችው ፡ የችግሯን አሳሳቢነት ተረድቶ መፍትሄ እንደሚሰጣት ገምታ ነበር ። ሆኖም ፡ የተለየ ነገር አልጠበቃትም ። ሳሊ የባንኩን ማናጀር መለመን ያዘች ። አዝናለሁ በርግጥ የራስሽ ብር ቢሆንም በገጠመን የኤኮኖሚ ግሽበት ምክንያት የወጣውን  ህግ ተላልፈን ልንረዳሽ አንችልም ፡ ሲል ቁርጥ ያለ ምላሽ ሰጣት ።
................
ሳሊ ሃፊዝ የማናጀሩን ምላሽ እንደሰማች ወደ ቤቷ በማምራት ፡ በሶሻል ሚዲያ ከምታውቃቸው ሰወች ጋር በጉዳዩ ላይ አውርታ ፡ ነገ ልታደርግ ያሰበችውን ነገር ነገረቻቸው ። የሳሊ ጓደኞች እቅዷን እንደሰሙ አብረዋት እንደሚቆሙ ቃል ገብተውላት ፡ በማግስቱ የሚገናኙበትን ቦታ ተቀጣጥረው ተለያዩ ።
................
በማግስቱ ጠዋት ሳሊ ሃፊዝና ጓደኞቿ ገንዘቧን ወዳስቀመጠችበት ብሎም ባንክ አመሩ ።
.................
ወደባንኩ እንደገቡም ፡ ሳሊ ሃፊዝ የባንኩ ባንኮኒ ላይ ወጥታ  ከወገቧ ስር ያስቀመጠችውን ሽጉጥ በማውጣት ፡ እየጮኸች መናገር ጀመረች ። በባንኩ ውስጥ ይስተናገዱ የነበሩት ደንበኞች በድንጋጤ መርበትበት  ጀመሩ ።
..................

አንድም ሰው እንዳይንቀሳቀስ ፡ እኔ ማንንም ሰው ለመግደል አልመጣሁም ፡ ሳሊ ሃፊዝ እባላለሁ ፡ የዚህ ባንክ ደንበኛ ነኝ ፡ በዚህ ወቅት እህቴ በካንሰር ታማ ሆስፒታል ትገኛለች ፡ በዚህ ባንክ የቆጠብኩትን ገንዘብ አውጥቼ እህቴን ለማሳከም የባንኩን ሰራተኞችና ማናጀሩን ጠይቄ ምላሽ ስላጣሁ በዚህ መልኩ ገንዘቤን ለመውሰድ መጥቻለሁ ።
..........
ይህን እንደሰሙ የባንኩ ሰራተኞችና ማናጀሩ በድንጋጤ መተያየት ጀመሩ ፡ ሳሊ ሃፊዝ ወደነሱ እያየች በፍጥነት የራሷን ብር እንደምትፈልግና ይህን ካላደረጉ የባንኩ ሰራተኞችና ባንኩ ላይ እርምጃ እንደምትወስድ ተናግራ ፡  ፡ ከሷ ጋር ለመጡት ጓደኞቿ ምልክት አሳየቻቸው ። በዚህ ጊዜ የሳሊ ጓደኞች በትንሽ ጀሪካን የያዙትን ጋዝ  ባንክ ቤቱ ወለል ላይ ማርከፍከፍ ጀመሩ ።

................
የባንክ ሰራተኞቹ ገንዘቧን ካልሰጧት ጉዳቱ የከፋ እንደሆነ ስላወቁ ፡ በባንኩ ውስጥ የቆጠበችውን 12 ሺህ ዶላር ቆጥረው ሰጧት ። ሳሊ በፍጥነት ከቆመችበት የባንኩ ባንኮኒ ላይ ወርዳ ለመውጣት ወደበሩ ሲያመሩ ፡ ባንኩ በፖሊስ እንደተከበበ አወቁ በዚህ ጊዜ በሌኛው የባንኩ ጎን ያለውን ትልቅ መስታወት በመስበር ገንዘባቸውን ይዘው አመለጡ ።
........................
ይህ ጉዳይ ከተሰማ በኋላ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ሳይቀሩ ፡ ከሳሊ ሃፊዝ ጋር በመቆም ፡ ወጣቷ ማንንም እንዳልጎዳች ፡ ከቆጠበችው ገንዘብ ውጭም አንዳች የባንኩን ብር እንዳልወሰደች በመግለፅ ፡ እህቷን ከስቃይ ለማዳን ያደረገችው የሰብአዊነት ተግባር እንጂ ፡ አንዳች ወንጀል አልፈፀመችም ፡ በመሆኑም ተጠያቂ መሆን የለባትም በማለት ከጎኗ እየቆሙ ነው  ።
....................
ሳሊ ሃፊዝ የወሰደችውን ገንዘብ ለእህቷ መታከሚያ እንዲውል መክፈሏ ታውቋል ። ከሷ ጋር ሆነው ባንኩን ካስገደዱት ወጣቶች መሃከል የተወሰኑትን መያዙን ፖሊስ ቢያስታውቅም ፡ ሳሊ፡ሃፊዝን በተመለከተ ግን የሚወጡት  መረጃዎች የተለያዩ ናቸው ፡ አንዳንዶቹ ከሃገር መውጣቷን ሲገልፁ ሌሎቹ ግን እዛው ሊባኖስ ውስጥ እንዳለች ተናግረዋል ።
..................
  ስለጉዳዩ በቅርበት የሚያውቁ ሰወች እንደገለፁት ግን   ከወንድሟ ልጅ በወሰደችው ፡ አርቲፊሻል የልጆች ሽጉጥ ባንክን አስገድዳ ገንዘቧን የወሰደችው ሳሊ ሃፊዝ እስካሁን በፖሊስ አልተያዘችም
51 viewsBekele Ejeta, 10:13
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-24 11:28:55

54 viewsBekele Ejeta, 08:28
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-08 05:45:39 ኢንትራንስ ተፈታኝ ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲ ይዘው መሄድ የማይፈቀድላቸው ነገሮች

ማንኛውም ድምፅ የሚቀዳ፣ፎቶ የሚያነሳ ፣ ቪድዮ የሚቀርፅ ፣ ከቴሌ መስመርም ሆነ ከቴሌ መስመር ውጭ መልዕክት በዲጅታል መንገድ የሚሰጥ ወይም የሚቀበል የግል ዕቃ/መሳሪያ/የቴክኖሎጂ ውጤት ፣ ስልክ ፣ አይ-ፓድ፣ታብሌት፣ኮምፒውተር፣ላፕቶፕ፣ስማርት ሰዓት ፣ ማጂክ ብዕር፣ማጂክ ጃኬት እና ሌሎች ማናቸውም ፎቶ፣ምስል እና ድምፅ የሚቀርጹ የኤሌክትሮኒክስ መሳሪያዎችን በዩንቨርሲቲው ግቢ ውስጥም ሆነ ግቢ ዙሪያ ይዞ መገኘት ክልክል ነው።

በዩንቨርሲቲ ውስጥ ማንኛውም ዓይነት የግል ፍላሽ ዲስክ፣ሃርድ ዲስክ፣ሲዲ፣ሚሞሪ ካርድ ፣ሚሞሪ ሪደር፣ ኦ ቲጂ፣ኮንቨርተርና መሰል ዕቃዎችን ይዞ መገኘት ክልክል ነው

ማንኛውም ዓይነት የአንገት ሐብል፣የፀጉር ጌጥ፣የጆሮ ጌጥ፣የጣት ቀለበት፣የእጅ አንባር አድርጎ ወይም ይዞ መገኘት ክልክል ነው (ከልሙጥ የጋብቻ ቀለበት በስተቀር)
16 viewsBekele Ejeta, 02:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-09-07 17:45:21 ኢንትራንስ ተፈታኝ ተማሪዎች ሊያውቋቸው የሚገቡ ነገሮች
26 viewsBekele Ejeta, 14:45
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 09:55:44 5. የአበሻ አይብ:- የአበሻ አይብ ከአብዛኞቹ አይቦች የሚለየው ቅቤው የውጣለት መሆኑ ነው። አይብ በካልሲዩምና በፕሮቲን የበለጸገ ነው። እንደ አይብ አይነት የወተት ምርቶችን በበቂ መጠቀም insulin resistance (የስኳር በሽታ ዋነኛው ችግር) ይዋጋል።

6. የወይራ ዘይት:- በአንዳንድ የጤና አኳያ ሲታይ የወይራ ዘይት ፈሳሽ ወርቅ ነው ተብሎ በብዙዎች ተሰይሟል። የወይራ  ዘይት ከፍተኛ  anti inflamatory ባህሪይ አለው። ይህ ደግሞ ስኳርን እና የልብ በሽታን የሚዋጋ ባህሪይ አለው ማለት ነው።

7. ስኳር ድንች:-  ለምሳሌ ያህል በድንች ፋንታ ስኳር ድንች መብላት ደም ውስጥ ያለው ስኳር 30% ያህል ከፍ እንዳይል ያግዛል። ስኳር ድንች በበሽታ ተከላካይ ፋይበር የበለጸገ ነው። ከዛ ውስጥ 40% የሚሟሟና ኮለስተሮልን የሚቀንሱና digestion በፍጥነት እንዳይካሄድ የሚረዱ ናቸው። ሌላ ደግሞ በ ኦሬንጅና ቢጫ carotenoids የበለጸጉ ሲሆኑ እነሱም ሰውነታችን ለ insulin respond እንዲያደርግ ይረዳሉ። ከዛ በተረፈ በ chlorogenic acid የበለጸጉ ሲሆኑ እነሱም የስኳር በሽታ መንስኤ የሆነውን  insulin resistance ይዋጋሉ።

8. ቀይ ስጋ በመጠኑ:-  ቀይ ስጋ በ ፕሮቲን የበለጸገ እና ሰውነታችን ጮማ ከሚሆን በቂ የአካል እንቅስቃሴ ካደረግን በጡንቻ እንዲተካ ይረዳል።
44 viewsBekele Ejeta, edited  06:55
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 09:53:39
#ስኳር_በሽታ_ላለባቸው_ሰዎች_8_ምርጥ_ምግቦች

1. ገብስ:-  ለምሳሌ ያህል በነጭ ሩዝ ፋንታ ገብስ መብላት ደም ውስጥ ያለውን ስኳር 70% ይቀንሳል። እሱ ብቻ ሳይሆን ገብስ በ ፋይበር የበለጸገ ስለሆነ የደም ስኳር መጠን ለሰዓታት ወይም ለረጅም ጊዜ ዝቅ ብሎ እንዲቆይ ይረዳል። ስለዚህ ገብስ ስኳር ላለበት እጅግ ምርጥ ምግብ ነው ተብሎ ይታወቃል።

2. ባቄላ እና ዘሮቹ:- ባቄላ፣ አተር እና ሽምብራ አይነት ጥራጥሬዎች አንደኛ በፋይበር የበለጸጉ ናቸው። ሁለተኛ ደግሞ በፕሮቲንም የበለጸጉ ስለሆኑ የደም ስኳር መጠንን ዝቅ አድርጎ ለመጠበቅና እንዳይርብ አስተዋጽኦ ያደርጋሉ።

3. እንቁላል(በመጠኑ):-  እንቁላል በፕሮቲን የበለጸገ ምግብ ከመሆኑም በላይ እንቁላል የፕሮቲኖች ወርቅ ተብሎ ተሰይሟል። በቀን አንድ ወይም ሁለት እንቁላል  መብላት ኮለስትሮልንም ከፍ አያደርግም። ስለዚህ እንቁላል በፕሮቲን የበለጸገ ስለሆነ ቶሎ እንዳንራብ ይረዳል።

4. አሳ:- የስኳር በሽታ ዋነኛው መዘዝ የሚባለው የልብ በሽታ ነው። አሳ ደግሞ በሳምንት አንዴ ብቻ እንኳን መብላት ሰው በየትኛውም አይነት የልብ በሽታ የመያዙን እድል 40% ይቀንሳል።
43 viewsBekele Ejeta, edited  06:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-22 11:40:43

58 viewsBekele Ejeta, 08:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-21 08:37:41 እውነተኛና አሳዛኝ ታሪክ/ባለታክሲውን ፍለጋ/በፍቅር ሰበብ የስንቱ ሕይወት ጠፋ
25 viewsBekele Ejeta, 05:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 05:53:22
አየር ላይ እንቅልፍ ጥሏቸው ነበር የተባሉ ሁለት የኢትዮጵያ አየር መንገድ አብራሪዎች ታገዱ

ከሱዳን ካርቱም ወደ አዲስ አበባ ሲበር የነበረ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ሁለት አብራሪዎች አየር ላይ እንቅልፍ ጥሏቸው አውሮፕላኑ መዳረሻውን አልፎ እንደነበር ተነግሯል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዛሬ እኩለ ቀን ባወጣው መግለጫ በእለቱ በአብራሪዎቹ እና በአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች መካከል ግንኙነት ተቋርጦ እንደነበር ያረጋገጠ ሲሆን፣ መንስኤው ምን እንደሆነ እየተጣራ ነው ብሏል።

አየር መንገዱ በአብራሪዎቹ እና በአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪዎች መካከል ግንኙነት በምን ምክንያት እንደተቋረጠ ያለው ነገር ባይኖርም የተጀመረው ምርመራ እስኪጠናቀቅ ድረስ ሁለቱ አብራሪዎች ከሥራ ታግደዋል ነው ያለው።

የበረራ ቁጥር ኢቲ 343 ቦይንግ 737-800 አውሮፕላን ከካርቱም ወደ አዲስ አበባ በ37ሺህ ጫማ ከፍታ ላይ ሲበር ነበር።

ቢቢሲ ፍላይትራዳር24ን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ ቢያንስ ባለፉት 7 ቀናት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በየዕለቱ ከካርቱም ወደ አዲስ አበባ በረራ ያደረገ ሲሆን፣ በረራው የሚፈጀው ጊዜም ከ1 ሰዓት ከ25 ደቂቃ እስከ 1 ሰዓት ከ29 ደቂቃ ድረስ ነው።

ይሁን እንጂ ሰኞ ነሐሴ 9፣ 2014 ከካርቱም አዲስ አበባ የነበረው በረራ አውሮፕላኑ ያረፈው ከ1 ሰዓት ከ49 ደቂቃ በረራ በኋላ ነው።
49 viewsBekele Ejeta, edited  02:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-20 05:53:22
በጋና አንድ ግለሰብ በእንቅልፍ ላይ ሆኖ በአጋጣሚ ብልቱን ቆረጠ

በጋና አንድ ግለሰብ በእንቅልፍ ላይ እያለ በአጋጣሚ የወንድ የዘር ፍሬውን በከፊል ቆርጦ ብልቱ ላይ ጉዳት ማድረሱ ተሰምቷል፡፡ኮፊ አታ የተባለዉ ግለሰብ በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ አደጋው ከተከሰተበት ጊዜ አንስቶ በሆስፒታል ውስጥ ይገኛል።

የ47 አመቱ ግለሰብ ከደረሰበት ጉዳት ለመታደግ ለቀዶ ህክምና ገንዘብ እየተሰበሰበ ይገኛል፡፡አታ ከሆስፒታል ሆኖ አደጋው እንዴት ተከሰተ ሲናገር ወንበሬ ላይ ተቀምጬ አሸለብኩኝ፤ በእንቅልፍ ልቤ ከፊቴ ሥጋ እየቆረጥኩ እንደሆነ አየሁ።"ቢላውን እንዴት እንዳነሳሁ አላስታውስም"ሲል አክሏል፡፡

በእንቅልፍ ልቡ ሆኖ ሲጮህ የደረሱለት ጎረቤቶቹ በክፍሉ ውስጥ ብቻውን ሆኖ ከፍተኛ ደም ሲፈሰዉ እንደደረሱለት ተናግረዋል::
38 viewsBekele Ejeta, edited  02:53
ክፈት / አስተያየት ይስጡ