Get Mystery Box with random crypto!

Our World

የቴሌግራም ቻናል አርማ ourworl_d — Our World O
የቴሌግራም ቻናል አርማ ourworl_d — Our World
የሰርጥ አድራሻ: @ourworl_d
ምድቦች: ቴክኖሎጂዎች
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 894

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 5

2022-08-17 19:27:28
በ2ኛው የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የሥራ ጉባኤ አሸናፊ የሆኑ ሦሥት ምርጥ የንግድ ሥራ ሃሳቦች፦

1ኛ. በፀሀይ ብርሃን የሚሰራና ተጨማሪ
አገልግሎቶች የተገጠሙለት ዊልቼር

• የፈጠራ ሃሳቡ ባለቤት ናትናኤል ታከለ።
• ፈጠራው ወደ አገልግሎት ሊለወጥ የሚችል፡፡

2ኛ. በሀገር ውስጥ የሚመረት የሊዝ ማሽን

• የፈጠራ ሃሳቡ ባለቤት ፉአድ መሀመድ።
• ሥራ ላይ የዋለና የውጪ ምንዛሪን በማስቀረት ለአምራቾች ተደራሽ የሚሆን።

3ኛ. ከብቶች፣ በጎች እና ፍየሎች መንታ መንታ እንዲወልዱ የሚያደርግ ግኝት

• የሃሳቡ ባለቤት የእንስሳት ሀኪም አዲሱ ወርቁ
• ከዕጽዋት የተቀመመና ውጤታማነቱ የተፈተሸና እውቅና ያገኘ።

የሥራ ፈጠራ ሃሳብ አሸናፊዎቹ ለእያንዳንዳቸው 260 ሺህ ብር ተበርክቶላቸዋል።
30 viewsBekele Ejeta, edited  16:27
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-17 06:35:13

32 viewsBekele Ejeta, 03:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-16 05:44:04
#MoE

" የ2014 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከመስከረም 30 /2015 ዓ/ም ጀምሮ በ2 ዙር እንዲሰጥ ታቅዷል " - ትምህርት ሚኒስቴር

የ2ዐ14 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና በዩኒቨርስቲዎች እንዲሰጥ መወሰኑ ይታወቃል፡፡

ፈተናው ከመስከረም 30 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ #በሁለት_ዙር እንዲሰጥ መታቀዱን በትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ተፈርሞ ለ42 ዩኒቨርሲቲዎች በተላከውን እና ቲክቫህ ኢትዮጵያ ትክክለኛነቱን ባረጋገጠው ደብዳቤ መመልከት ችለናል።

በዚሁ መሠረት ከመስከረም 28 እስከ ጥቅምት 17 ቀን 2015 ዓ.ም ድረስ ዩኒቨርስቲዎች ፦

1. ምንም አይነት የመደበኛ ተማሪ በግቢ እንዳይኖር እንዲያደርጉ፤

2. በቀጣይ በሚገለጸው ተማሪ ቁጥር ልክ ምግብ እንዲቀርብ ዝግጅት እንዲያደርጉ፤

3. ለፈተናዎች ማቆያ ቦታ አንዲዘጋጅ እና

4. የፈተናውን አሰጣጥና ደህንነት የሚቆጣጠር በፕሬዚዳንት የሚመራ ዋና ግብረ-ኃይልና በየካምፓሶቹ በዲን /ካምፓስ ኃላፊ የሚመራ ንዑስ ግብረ-ኃይል እንዲያደራጁ መልዕክት ተላልፎላቸዋል።

ዩኒቨርሲቲዎች የ2ዐ15 የአካዳሚክ ካላንደር የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና ወቅት (ከመስከረም 28 - ጥቅምት 17) ታሳቢ በማድረግ እንዲያዘጋጁ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ አሳስበዋል።
112 viewsBekele Ejeta, edited  02:44
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 10:17:19
በቻይና ሲያቅፈኝ የጎን አጥንቴን ሰብሯል ያለችዉ ግለሰብ የስራ ባልደረባዋን ከሰሰች

በቻይና ሁናን ግዛት ዩያንግ ከተማ ነዋሪ የሆነችዉ ግለሰብ በስራ ላይ እያለች አንድ ወንድ የሥራ ባልደረባዋ መጥቶ እቅፍ አድርጎ ሰላምታ ያቀርብላታል፡፡እቅፍ ሲያደርጋት ግን ከፍተኛ ህመም ስለተሰማት ትጮኃለች፡፡ ሰውዬው በጣም አቅፎት የነበረ ሲሆን ከስራ ከወጣች በኋላም ደረቷ ላይ ህመም ይሰማት ይጀምራል፡፡ነገር ግን ወዲያውኑ የህክምና እርዳታ አልፈለገችም ደረቷ ላይ ትንሽ ትኩስ ዘይት በመቀባት እና በምትኩ መተኛትን ትመርጣለች።

በጣም ጥብቅ ከሆነው እቅፍ ከአምስት ቀናት በኋላ በደረቱ ላይ ያለው ህመም እየጠነከረ ይሄዳል፡፡ በመጨረሻ ምርመራ ለማድረግ ወደ ሆስፒታል ትሄዳለች፡፡በኤክስሬይ ምርመራ አንድ ሳይሆን ሶስት የተሰበሩ የጎድን አጥንቶች፣ ሁለቱ የጎድን አጥንቷ በቀኝ እና አንድ በግራ በኩል እንዳለ ይረጋገጣል፡፡

በዚህም የተነሳ ከስራ እረፍት ለመዉሰድ ትገደዳለች ፣ይህም ገቢ እንድታጣ እና ለህክምና ሂሳብ ብሎም ለነርሶች አገልግሎት በርካታ ገንዘብ አውጥታለች።በህመሜ ወቅት እንዲረዳኝ ብጠይቀዉም ፍቃደኛ አልነበረም ያለችዉ ግለሰብ ካገገመች በኃላ በስራ ባልደረባዋ ላይ በዩኢያንግ ከተማፍርድ ቤት ክስ በመመስረት ለደረሰባት የገንዘብ ኪሳራ ካሳ ትጠይቃለች፡፡ፍርድ ቤቱ በሥራ ባልደረባው ላይ በአጋጣሚ በማቀፍ የጎድን አጥንቷን በመስበር 10,000 ዩዋን (1,500 ዶላር) ካሳ እንዲከፍላት ትእዛዝ አስተላልፏል።
70 viewsBekele Ejeta, edited  07:17
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-15 06:07:34 " አዲሱ ስርዓተ ትምህርት "

የአዲሱ ስርዓተ ትምህርት በመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ በተወሰኑ ትምህርት ቤቶች ተሞክሮ የተጠናቀቀ ሲሆን ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ በሁሉም ትምህርት ቤቶች ስራ ይጀምራል ተብሎ ይጠበቃል።

ክልሎች አስፈላጊ መፅሀፍትና ቋንቋ የመተርጎም ስራ እየሰሩ ሲሆን በፍጥነት ወደ መፅሀፍ የማሳተም ስራ እንዲገባ እየተሰራ ነው ተብሏል።

በዚህም ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት (ኤለመንተሪ) ካሪኩለም ስራ ላይ ይውላል።

በተመሳሳይ በቀጣይ ዓመት የሁለተኛ ደረጃ ካሪኩለም የሙከራ ስራ በተወሰኑ ትምህርት ቤቶች ላይ የሚሞከር ሲሆን 2016 ዓ/ም ላይ ሙሉ ለሙሉ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል።
69 viewsBekele Ejeta, 03:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-13 21:24:56 ዓለም አቀፍ የግራኞች ቀን አስደናቂ መረጃዎች

~ ዛሬ ነሀሴ 7 ቀን ዓለም አቀፉ የግራኞች ቀን የሚከበር ሲሆን እ.ኤ.አ ከ1996 ጀምሮ በዓለም አቀፉ የግራኞች ማህበር መስራች ዲን ካምቤል አማካይነት መከበር ጀምሯል።

~ 12 በመቶ የአለም ህዝብ ግራኝ ሲሆን ወንዶች ከሴቶች የበለጠ ግራኞች ናቸው።17 በመቶ መንትዮች ግራኝ ናቸው።

~ ታይም መፅሄት በ10ሺ ሰዎች ላይ በሰራው ጥናት በወሲባዊ ህይወት ግራኞች ከቀኞች ደስተኛ ናቸው ይላል።ከግራ ጭንቅላት አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ግራኞች ከስትሮክ ከቀኞች በተሻለ በቶሎ ያገግማሉ።

~ በኮከብ ቆጠራ ረገድ ስንመለከተው ከግንቦት 14 እስከ ሰኔ 13 የተወለዱት ከሌሎች ዞዳይኮች ሲነፃፀር ጄሚኒዎች ውስጥ ብዛት ያላቸው ግራኞች አሉ።

~በየአመቱ ለቀኝ ተጠቃሚዎች ብቻ ተብለው በተሰሩ መገልገያዎች የተነሳ ከ2500 በላይ ግራኞች ህይወታቸውን ያጣሉ።ግራኞች በገቢ ከቀኞች በአማካይ 12በመቶ ያንሳሉ።

~አለማችን ላይ ታዋቂ ከሚባሉ ግራኞች መካከል ቻርሊ ቻፕሊን፣ዳ ቬንቺ ፣ኦፕራ ፣አንስታይን፣ ኒውተን ቢል ጌት እና ሚካኤል አንጄሎ  ተጠቃሽ ናቸው።ከቅርብ ጊዜ 9 የአሜሪካ ፕሬዝዳንቶች መካከል አምስቱ ግራኝ ናቸው።እነርሱም ኦባማ፣ቢል ክሊንተን፣ፎርድ፣ሮናልድ ሬገን እና ትልቁ ቡሽ ናቸው።

~ በሂሳብ ስሌት ረገድ ግራኞች የበለጠ ውጤታማ ናቸው።ነፍሰ ጡር ሴት በተደጋጋሚ በእርግዝና ወቅት በድብርት የምትጠቃ ከሆነ ግራኝ ልጅ የመውለድ ሰፊ እድል አላት።

~ በኮምፒውተር ኪቦርድ ላይ ታይፕ ለማድረግ ከ3ሺ በላይ የእንግሊዝኛ ቃላት ለመፃፍ በግራ የተመቸ ሲሆን በቀኝ ከ300 የበለጠ አይደለም።

~ ግራኞችን በተመለከተ ከተነገሩ ዝነኛ አባባሎች መካከል ጀርመናዊው ፈላስፋ ዋልተር ቤንጃሚን ሁሉም ከባድ ቡጢዎች በግራ ያርፋል ብሏል።
120 viewsBekele Ejeta, 18:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 21:15:36 መንግስት ያሸንፋል
በላይ በቀለ ወያ
82 viewsBekele Ejeta, 18:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 09:36:51 ላይ) ከፍተኛ ጥላቻን ሲዘሩ የወደፊት የፍቅር ሕይወታቸው ላይ የሚያደርሱት ተፅዕኖ መገመት ከሚቻለው በላይ ነው።
በሌላ ፅንፍ ግድ የለሽና ራስ ወዳድ አባቶች ደግሞ ግድ የለሽና ለሰዎች ዋጋ የማይሰጡ ከዛም በላይ የበታችነት ስሜት -
የተጋቱ ልጆችን ያበቅላሉ።
59. የበርካታ ችግሮቻችን ዋነኛ ምክንያት በግለሰብ ደረጃ ማንነታችን የተገነባበት
መሠረት፣ እኛነታችን የተዋቀረበት ማገርና ስብዕናችን የቆመበት ምሰሶ ምንነት ነው ወላጅ፣ መምህር፣ የድርጅት
አስተዳዳሪ፣ የቢሮ ሠራተኛ፣ ወታደር፣ ሳይንቲስት፣ ሃኪም፣ የሀገር መሪ፣... የሚሆነው ይኼው ግለሰብ ነውና።
60. . ትዳር መልካም ማሳ ነው፣ በየጊዜው የፍቅር ውሃ ማጠጣት፣ የቂምና የጐሜ
አረሞችን መንቀልና በቂ የመተሳሰብና የመገነዛዘብ ብርሃን እንዲያገኝ ማድረግ ያሻል። ያኔ ማሳው መልካም ፍሬውን
ይለግሳል።
61. ቤታችን ፍቅር የሚዘንብበት፣ መከባበር የሰፈነበት፣ መተዛዘን የሚታይበት
መረዳዳት ልዩ ባህሪው የሆነ ማረፊያችን ይሆን ዘንድ መሥራት ይኖርብናል።
። በኢማን መድመቅና በመልካም ሥራ መዋብ
እንዲያ ዓይነት ቤት
ይፈጥራል።
62 ህፃናት ስብዕናቸውን ከሚያቆሽሽ ወይም ራሳቸውን ዝቅ አድርገው እንዲመለከቱ
ከሚያደርግ የትኛውም ዓይነት ጥቃት የሚጠበቁበትን ሁኔታ ማመቻቸት ለነገ የማይባል ማኅበራዊ ኃላፊነት ነው።
63. ክብርንና ነውርን ማወቅ ትልቅነት ነው፤ ክብር ነውር፥ ነውር ደግሞ ከብር የሆነበት ማኅበረሰብ የሞራል እሴቶች ሞት
የተበሰረበት ማኅበረሰብ ነው።
64 ሕይወትህ ወጥ፣ የማይዛነፍና በሁኔታዎች ወይም በግለሰቦች ተፅዕኖ
የማይፍረከረክ ይሆን ዘንድ መርህን ማዕከሉ ያደረገ Principle Centered) የሕይወት ፍልስፍና አዳብር።
65 ፍትህን አስፍን፤ እንዲያ በማድረግህ አንተን የሚጐዳ አጋጣሚ ቢፈጠር እንኳ።
የመለኮታዊ ቃሉ ትእዛዝም ይኸው ነው።
66. ምድር ያላት ሃብት ለሰው ልጆች ሁሉ ከበቂ በላይ ነው፤ ስግብግብነትን
አስወግደህ ለጋራ ብልፅግና ትጋ።
67. ደስታ የሚገኘው ለራስ ከማድረግ ይልቅ ለሌሎች በማድረግ፣ ለራስ ከመኖር
ይልቅ ለሌሎች በመኖር ነው።
68. ነፃነት ሁሉም ነገር ሊከፈልለት የሚገባ ውድ የሰው ልጅ ሃብት ነው።
69. ደስታን እንደ ዛፍ አስባት፤ ውሃዋ፣ ምግቧና አየሯ ኢማን ነው።
70. ይህች ሀገር ካለችበት የድህነት አረንቋ የምትወጣው በዕውቀት በጠገቡ
አዕምሮዎች፣ ቅን አስተሳሰብ በተሞሉ ልቦናዎችና ለሌሎች በሚኖሩ ሰብዕናዎች መሆኑን ሁሌም አስታውስ።
85 viewsBekele Ejeta, 06:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 09:36:51 ዲያከብሩት የሚፈልግ፣ እያዋረዳቸው እንዲያልቁት
የሚሻ፣ እየጠላቸው እንዲወዱት የሚመኝ ሰው በርግጥም ቂል ነው።
24, ፍትህ ሃይማኖት፣ ዘር ወይም ብሔር የለውም። ለማንም አይወግንም፡፡ ለሁሉም _ የሰው ዘር እኩል ይቆማል።
እናም ከተበደሉት ሁሉ ጎን ቁም፤ ይህ የሰውነትህ ክብር ነው።
25. ደስታህ ታምቆ የሚገኘው ሌሎችን በማስደሰት ውስጥ ነው፤ ቁስል ላይ
እንደሚያርፍ ዝንብ ጉድለታቸውን ከማነፍነፍ ይልቅ ጠንካራ ጐናቸውን እንዲያጐለብቱ በማገዝ ይደሰቱ ዘንድ
እርዳቸው።
26. ለእያንዳንዷ በጎ ሥራችን በአንድ ወይም በሌላ መንገድ በጎ ይዋልልናል፤
በአንፃሩ ለእያንዳንዷ ክፉ ሥራችን በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ክፉ
ይዋልብናል።
27. በሚደርስብህ ውጫዊ ተፅእኖና በምትመርጠው ምላሽ መሃከል ማገናዘቢያ ጊዜ ያስፈልግሓል።

ያ ምርጫሕን እንድታስተካክል የሚያስችልሕ ቁልፍ መሳሪያ ነው።
አለያ ግን ምላሽህ ግልብና በውሉ ያልተሰላ በመሆኑ በአብዛኛው ለባሰ ችግር ያጋልጥሃል። ከደረሰብን ችግር ይልቅ ለችግሩ የምንሰጠው ያልበሰለ ምላሽ
ይበልጥ ይጐዳናል።
28 በሕይወት ተስፋ ለቆረጡና ዙሪያቸው ገደል ለሆነባቸው ወገኖች ተስፋ ከመሆን .
የተሻለ የመንፈስ ምግብ ፈፅሞ አይገኝም።

29 “ከሰዎች ሁሉ በላጩ ለሰዎች የነፍስ ፈጣሪ የሆነው ነው....
ነቢዩ ሙሐመድ (ሰበ መ
ለጹ 30. ላንተም ሆነ ለሰው ዘር የማይጠቅም ብሎም የሚጐዳ ሃሳብ ለማውጠንጠን
የምታፈሰውን ኃይል ጠቃሚና አወንታዊ ሃሳቦች ለማፍለቅ ብታውለው ሰው _ የመሆንን ክብር ትረዳበታለህ። በአንፃሩ
ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት የምታውለው
ኃይል የተገባ ጥቅም ማግኘት የሚያስችልህን አቅም ያመክናል።
31 የታላቅነት መንገድ ፈታኝ መሆኑን አትዘንጋ፤ ዳገታማ ነውና የምድር ስበትን
መቋቋም ይኖርብሃል። በአንፃሩ የውድቀት መንገድ ግን ቀላል ነው፤ ቁልቁለት ነውና ስበቱም ያግዝሃል። በፈጣሪህ
የተቸረህን የመምረጥ ነፃነት ተጠቅመህ ምርጫህን አስተካከል።
32. አዕምሮህን በዕውቀት ቀልበው፤ አካልህን በተመጣጠነ ምግብና በስፖርታዊ _እንቅስቃሴ ተንከባከበው። ልቦናህን
በፍቅር ሙላው፤ መንፈስህን በዘልዓለማዊ
ግብ አድሰው። ለምሉዕ ስብዕና የሚያበቃህ አካልህን፣ አዕምሮህን፣ ልብህንና መንፈስህን ሚዛናዊ በሆነ መልኩ

ማበልፀግህ ነውና።
33. ልብህን ከጥላቻ፣ ከምቀኝነትና ከጐሜ አፅዳ፣ ይህንን በማድረግህ ነፃነትህን
ትቀዳጃለህ፣ ክፉ ስሜት ተሸክመህ ከመኖር ትገላገላለህ።
34 ይቅር በል፤ ለራስህ ያልሰጠኸውን ፍፁምነት ከሌሎች አትጠብቅ።
35. ባለፈ ነገር እርር ድብን አትበል፤ እንዲያ መሆንህ አዎንታዊ ለውጥ አያመጣም"
ይልቁንስ፡- ዛሬን በትክክል ኑር፤ ይህ ትናንትን ማረሚያ፣ ነገን ማሳመሪያ መንገድ ነውና።
36. የምታደንቃቸውን ሰዎች ለመምሰል ከመጣር ይልቅ አድናቆቱ ውስጥህ ያለውን ያንተኑ አቅም እንድታወጣ ያድርግህ፤ ሁሉም ሰዎች የራሳቸው ተሰጥኦ አላቸውና ራስህን ሁን።

37. ተፈጥሯዊ ችሎታሕን ፣ ተገንዘብ፤ እሱም ላይ አተኩር፤ የሚስብህን የዕውቀት ዘርፍ በጥልቀት
» ተማር፤ የተመቸህ የሥራ ዓይነት ላይ ተጠመድ። እንዲያ ስታደርግ የስኬት መስመር ላይ መሆንህን እርግጠኛ ሁን።
38 ኪሳራን ወደ ትርፍ
፥ ውድቀትን ወደ ስኬት መለወጥ የምትችለው ከሁኔታዎች ጋር ራስህን በማጣጣም ብልህ ውሳኔ ላይ
መድረስ ስትችል ነው።
39. በፍጡራን ላይ ያለን ተስፋ ሲሟጠጥ በአላህ ላይ ብቻ ተስፋችንን እንጥላለን፤ ያኔ ያልተጠበቀ እርዳታው ይደርሳል።
40. ከአላህ እዝነት ተስፋ አትቁረጥ፤ የርሱን እርዳታ የምታገኘው በሻትከው ያክል
መሆኑን አትዘንጋ።
41. . በዚህች ዓለም ውስጥ አላፊ ያልሆነ ነገር እንደሌለ መገንዘብ በችግር ውስጥ
ብርታትን፣ በደስታ ውስጥ መረጋጋትን ይሰጣል።
42. ስቃያችን መዳኛችን ሊሆን ይችላል፤ ብዙም አምርረን አንጥላው። ለኛ በጎ የሆኑ
ነገሮች በአብዛኛው የሚገኙት በማንወዳቸው ነገሮች ውስጥ ነውና። .
43 ከአላህ ጋር ያለህን ግንኙነት ምንጊዜም መርምር፤ ከፈጣሪ ጋር ያለህ ግንኙነት - መበላሸት ከፍጡራን ጋር ያለህን
ግንኙነት ያበላሻል።
44. ኢማን የጭንቀት ፍቱን መድሃኒት ነው፣ ከሰፊው የአኺራ ዓለም ጋራ ያለህ ግንኙነት በጠበቀ ቁጥር ስለ ጠባቧ ዱኒያ የሚኖርህ
ከልክ ያለፈ ጭንቀት
ምክንያት ያጣብሃል።
45 አላህን ብቻ በፍፁምነት በማምለክ፣ ከሁሉም አይነት ባርነቶች እራስሕን ነፃ አውጣ።

46. ኢማን ሌሎች ሰዎኅ ስላመኑ ብቻ፣ በጭፍን የሚከተሉት መሰረት አልባ አመለካከት ሳይሖን፣ የነፍስወከብ እውቀት የሚጠይቅ ምልከታ ነው።

47. የኢማንን መኖር
_ የሚያረጋግጠው መልካም ሥራ ሲሆን የዒባዳን ፍሬ የሚመሰክረው ደግሞ በጎ ሥነ-ምግባር ነው።

48 እስልምና ሕይወትን ከፋፍሎ የሚመለከት ሃይማኖት አይደለም፣ መንፈሳዊና ቁሳዊ ብሎ በመነጣጠል አንዱን ቀድሶ
ሌላኛውን አያራክስም፣ ኣኺራጥር .
ብሎ በመለያየት አንዱን አወድሶ ሌላኛውን አያወግዝም፤ መንፈሳዊ ልእልናን ከዓለማዊ ሕይወት ስኬት ጋር ያጣመረ
ድንቅ የሕይወት ጎዳና ነው።
49. ግጭት (Conflict) የሕይወት አንድ ገፅታ ነው። በትዳር ውስጥ፣ በስራ ቦታ፣
በአጠቃላይ ከሰዎች ጋር ባለን ግንኙነት ግጭት መፈጠሩ ተፈጥሯዊ ነው፤ ዋናው ጉዳይ የግጭት አፈታት ክህሎታችንን
ማዳበሩ ላይ ነው።
50. ግጭት በአስተማማኝ ሁኔታ ሊፈታ የሚችለው ሁለቱንም ወገኖች አሸናፊ
የሚያደርግ (Win-win) መፍትሄ ላይ መድረስ ሲቻል ነው። በአንፃሩ አንዱን ወገን አሸናፊ ሌላኛውን ወገን ከሳሪ
የሚያደርግ (Win-loss) የግጭት አፈታት ግን ጊዜውን ጠብቆ እንደሚፈነዳ የተቀበረ ቦንብ ከባድ ግጭት እንዲረገዝ
ያደርጋል።
51. ለአጭር ጊዜ ለምታገኘው ሰው መልካም መሆን ቀላል ሊሆን ይችላል፤ ሁሌም
አብራህ ለምትኖረዋ የትዳር አጋርህና ለቤተሰቦችህ መልካም መሆን ግን ያንተ ደግነት መለኪያ ነው። “ከናንተ ውስጥ
የተሻለውና በላጩ ለቤተሰቦቹ (ለባለቤቱ) ይበልጥ መልካም የሆነው ነው፤ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ)
52. ልባዊ ፈገግታ የሰዎችን ልብ ይከፍታል፤ ለሰው ልጅ ያለህን አክብሮት
የምትገልፅበት ዓለም አቀፋዊ ቋንቋም ነው።
53 የልጆች አስተዳደግ የወደፊት ማንነታቸው መሰረት ነው።
የሚታጨደው የተዘራው ነው።


54 በልጅነት አዕምሮ ላይ የተፈጠረ ጠባሳ ለተንሻፈፈ ስብዕናና ለተዛባ ማንነት ዋነኛ
ምክንያት ነው። ተንቆ ያደገ ህፃን ሰው መናቁ፣ ተዋርዶ ያደገ ህፃን ሰው ማዋረጁ፣ ተፈጥሯዊ ውጤት ነው።
። ህፃናት አድገው
ሰው ያከብሩ ዘንድ ሊከበሩ፡ ለሰው ያዝኑ ዘንድ ሊታዘንላቸው የግድ ይላል።
55. የህፃናትን ኣእምሮ ማዳበር ለነገ የሚባል ስራ አይደለም፤ አሊያ ግን ሕብረተሰቡ ውስጥ የሕፃናት አዕምሮ ያላቸው ትልልቅ ሰዎች መበራከታቸው አይቀርም። እነዚሕ ትልልቅ ሰዎች የሚፈጥሩት ማኅበራዊ ቀውስ
በቀላሉ የሚታከም
አይሆንም።
56. የሕብረተሰባችን የወደፊት እጣ ፈንታ የታመሙ ስብዕናዎችን ለማከምና ንፁሃን ሕፃናትን ጤንነታቸውን ለመጠበቅ
በምናደርገው ትግል ይወሰናል፤ ስኬቱም በውጤቱ ይለካል።
57. <- በአንድ በሆነ አጋጣሚ እንደቀላል የተናገርነው አዋራጅ ቃል በተሰዳቢው ግለሰብ
ላይ የማይሽር ቁስል ሊፈጥር ይችላል፤ ቁስሉ እያመረቀዘ የግለሰቡን ስብዕና በክሎ እርሱም በተራው ሌላ ሰው
እንዲያቆስል ምክንያት ይሆናል።
58. . ጨካኝ አባቶች በልጆቻቸው ሥነ-ልቦና ውስጥ (በተለይም በሴቶች ልጆቻቸው
65 viewsBekele Ejeta, 06:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-12 09:36:50 "ለውጥ" ከተሰኘው የበድሩ ሑሴን መጽሐፍ የተቀነጨበ
ቀን 18/06/06
የእናት ምክር- ለተሳካ ትዳር
ዐውፍ ኢብን ሙሐሊም አሹ ሸይባኒ ከኢስላም በፊት በአረቦች ዘንድ እጅጉን የታወቀ የጎሳ አለቃ ነበር። ኡሙ ኢያስ
የተሠኘች ልጁን ለሓሪሥ ኢብን ዓምር አልኪንዲ ሊድርለት ወስኗል። ሙሽራዋ አስፈላጊው ሁሉ ከተሰናዳላት በኋላ
ወደ ባለቤቷ ቤት ለመሄድ ተዘጋጀች። እናት በሕይወት ዘመኗ ያካበተችውን ልምድ ለውድ ልጇ ለማካፈል፣ ልጅም
ለትዳሯስኬት የሚበጃትን ምክር ከእናቷ ለማድመጥ ፊት ለፊት ተቀምጠዋል። እናቷ ኡማማ ለልጇ የለገሠቻትን ምክር
እንደወረደ ከተብኩት።
“ውዷ ልጄ ሆይ! ትዳር የተከበረ ሥርዓት እና መልካም ቤተሰብ ላለው ሰው የማያስፈልገው ቢሆን ኖሮ በርግጥም አንቺ
ከባል የተብቃቃሽ በሆንሽ ነበር። ነገር ግን ወንዶች የተፈጠሩት ለሴቶች ሲሆን ሴቶችም የተፈጠሩት ለወንዶች ነው።
ውዷ ልጄ የለመድሽውን አካባቢ እና ያደግሽበትን ግቢ ለቀሽ ወደማታውቂው ጎጆ እና ወዳልተላመድሽው ጓደኛ
እየሄድሽ ነው። አንቺን የራሱ በማድረጉ እርሱ ንጉሥሽ ሆኗል፤ አገልጋዩ ሁኚለት ያኔ ባሪያሽ ይሆናል። አንቺ ለርሱ
ምድር ሁኚለት ያኔ እርሱ
ለአንቺ ሰማይ ይሆንልሻል። የምንጊዜም ስንቅና ማስታወሻ የሚሆኑሽን አስር ነጥቦች ያዥልኝ።
ደግሞ በመልካም እሺታ
አንደኛውና ሁለተኛው: ጉድኝትሽ በመብቃቃት፣ መኗኗርስ በመልካም እሺታና መታዘዝ ላይ የተመሰረተ ይሁን። ባለው ነገር መብቃቃት ልብን ሲያረካ፣ በእሺታና በመታዘዝ ውስጥ ደግሙ የአላህ ውዴታ ይገኛል።
ሦስተኛውና አራተኛው። አፍንጫውን ጠብቂለት፣ ዐይኑንም ተጠንቀቂለት። ዐይኑ ካንቺ ላይ ባለ የማያስደስት ነገር ላይ
እንዳያርፍ፣ አፍንጫውም ከአንቺ ምርጥ ሽታን እንጂ ሌላ እንዳያሸት። ኩል ጥሩ መዋቢያ ሲሆን፤ ውሃም ሽቶ በሌለ ጊዜ
ጥሩ ሽቶ ነው።
አምስተኛውና ስድስተኛው። የምግብ ሠዓቱን ጠብቂለት፣ የእንቅልፍ ጊዜውንም የተረጋጋ አድርጊለት። ምክንያቱም
የረሃብ ሐሩር አቃጣይ ሲሆን እንቅልፍ ሲረበሽ ደግሞ ቁጣን ይፈጥራል።
ሰባተኛውና ስምንተኛው፡ ወገኖቹን እና ዘመዶቹን አክብሪለት፤ ገንዘቡንም ጠብቂለት። ገንዘቡን መጠበቅሽ መልካም
አስተዳደርሽን የሚያሳይ ሲሆን ዘመዶቹን ማክበርሽ ደግሞ መልካም አኗኗርሽን ያመለክታል።
ዘጠነኛውና አስረኛው፡ ምስጢሩን አታናፍሺ፤ ትዕዛዙንም አትጣሺ። ምስጢሩን ካባከንሽ ከተንኮሉ አትድኚም፤
ትዕዛዙንም ከጣስሽ ልቡን ታውኪዋለሽ።
አምስቱ የለውጥ መሰረቶች
1. የለውጥ ሑሉ መነሻና መሰረት የአስተሳሰብ ለውጥ ነው።
2. ሐላፊነች መውሰድ።
3. ሕመሙን መቋቋም።
4. የምንሰራውን ስራ በጥራት ወይም በማሳመር መስራት።
5. ለውጥን አስቀጥል።

የሉቅማን ማስታወሻ
1 የለውጥ ሁሉ መነሻው የአስተሳሰብ ለውጥ መሆኑን አትዘንጋ፤ ከየትኛውም ውሳኔ
በፊት ዕውቀትን አስቀድም፤ ዕውቀትህን ለማዳበርም ሁሉንም ዓይነት መንገዶት ተጠቀም።
2. ትውልድ የግለሰቦች ቅብብሎሽ ነው፤ ራስህን በመለወጥ ለትውልዱ ጥራት

የበኩልህን ኃላፊነት ተወጣ።
3. የመጀመሪያው መለኮታዊ ቃል “አንብብ!” የሚል መሆኑን ሁሌም አስታውስ፣ ከንባብ ጋር እራስሕን በፅኑ አስተሳስር፤
የሕይወትህ መሠረት በዕውቀት ላይ
ይታነፅ።
4.የስልጣኔን ልጓም የሚጨብጡት አንባቢ ሕዝቦች ናቸው፤ በጥንቱ ዘመን ግሪካዊያንና ሮማዊያን፣ በመካከለኛው ዘመን
ሙስሊሞች፣ በዘመናችን ደግሞ ምዕራባዊያን በንባብ አፍቃሪነታቸው የሚታወቁ ሕዝቦች ናቸው።
5 ከቁስ ድህነት ይልቅ የአዕምሮ ድህነት አደገኛ መሆኑን እወቅ። የበለፀገ አዕምሮ
የቁሱን ዓለም የማበልፀግ አቅም አለው፤ የአዕምሮ ድህነት ግን የበለፀገን የቁስ ዓለም ያወድማል።
6. አዕምሮውን ለማልማት የማይሠራ ትውልድ ወደ ጥፋት የሚያደርሰውን አጭር | ጐዳና በመከተል ላይ ነው።
7 ዘመኑ ያመጣውን ሁሉ ሙሉ በሙሉ አትቀበል፤ የጥንቱንም ሁሉ አትቀድስ።
ከዘመኑ መልካሙን፥ ከጥንቱም ጥሩውን መምረጥ የሚያስችል የአስተሳሰብ ሚዛን አዳብር።
8 ከጭፍን የሃይማኖት ወይም የፖለቲካ አመለካከት ደቀ መዝሙርነት ራስህን
ጠብቀ፤ ዕውቀት ላይ የተመሰረተ እምነት አዳብር። ዕውቀት ልቦናን ያሰፋል፤ እይታን ያስተካክላል፤ ነፍስን ከጭንቀት፣
ከሃዘንና ከመደበት ይገላግላታል።
9. የትኛውም ትውልድ ለሀገሩ የሠራው መልካም ሥራ ሊያስወድሰው፣ በሐገሩና በወገኑ ላይ የፈፀመው በደል ያስውግዘዋል። ታሪክ መልካሙን ለማጎልበትና ከስህተት ለመማር መዋል ይኖርበታል
። በዚህም የተሻለ ዘመን ይፈጠራል።
10. በታሪክ ውስጥ አይነኬ ነገር የለም።
፤ በተለይ የሀገራችን ታሪክ በአዲስ መልክ ሊፈጠር ግድ ይለዋል፤ በሳይንሳዊ መንገድ መፈተሽ ይኖርበታል፤ ይህ
ሲሆን ግን የተሳለች ኢትዮጵያን መፍጠር ዋነኛ ግቡ መሆን ይኖርበታል
• በታሪክ ውስጥ ለተፈፀመ ስህተት ተጠያቂ ትውልድ አሁን የለም፣ የአሑኑ ትውልድ የሚጠየቀው ራሱ በሠራው ታሪክ ነው። በታሪክ ውስጥ ለታየ ስኬትም ተሸላሚ ትውልድ አሁን የለም፣
ተሸላሚዎቹ ያንኑ ታሪክ የሠሩት ትውልዶኅ ናቸው። የዘመኑ ትውልድ ከታሪክ በመማር የተሻለ ታሪክ ሊሠራ እንጂ
በታሪክ ሊኮፈስ ወይም ሊያፍር አይገባውም።
12. ለሥነ-ምግባር እነፃ ትልቅ ቦታ ስጥ፤ የሰው ልጅ ማኅበራዊ ስኬት በሥነ-ምግባሩ
ደረጃ ይለካልና።
13. ከራስህ ጋር እርቅ ፍጠር፤ ለህሊናህ የሚጎረብጥ አንዳች ነገር በምንም መልኩ
ላለመፈፀም ጥረት አድርግ።
14. ስሜትህ ከህሊናህ በላይ እንዳይነግስ ታገለው፤ ስሜት በአንድ ሰው ሕይወት
ውስጥ ከገዘፈ ወደ ጥፋት ማምራቱ አይቀሬ ነው።
15 ደመ-ነፍሳዊ ስሜት (ሕዋ) ታች የሌለው ጉድጓድ እንደማለት ነው፣ ምንም ያህል
ነገር ቢጨመርበት የማይሞላ ዓይነት። ጉድጓዱን የሚሞላው ለስርዓት ተገዥ መሆን ብቻ ነው።
16. ፍጥረተ-ዓለሙ የተገነባው በሥርዓት ነው፤ አንተም ሕይወትህን በሥርዓት
በመምራት ከፍጥረተ-ዓለሙ ጋር ተጣጣም።
17, ጥሩ አድማጭ ሁን፣ ነፃ ዕይታን በማዳበር ከቅድመ-ፍረጃ ራስህን ጠብቅ። ሰዎች
ሃሳብህን እንዲረዱ ከመሻትህ በፊት አንተ ቅድሚያ ተረዳቸው።
18. ራስህን ብቻ ከማድመጥ ተቆጠብ፤ አለያ በዙሪያህ ያሉ ሁሉ ካንተ ጋር ባላቸው
ግንኙነት ራሳቸውን ብቻ የሚያደምጡ ሆነው ታገኛቸዋለህ። ሰዎችን በሙሉ ልቦናህ አድምጣቸው፤ ያኔ እነርሱም
በሙሉ ልቦናቸው ያደምጡሃል።
19. በአንድ ጫካ ውስጥ ከሚገኙ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዛፎች ላይ የበቀሉ
ቅጠሎች እንኳ አንድ ዓይነት አይደሉም፤ ልዩነትን አድንቅ፡፡
20. የእኔ እምነት (ሃይማኖት) ብቻ ትክክል ነው፤ ሌሎች እምነቶች በሙሉ ስሕተት
ናቸው' ብሎ ማሰብ ፅንፈኝነት አይደለም። ምክንያቱም እምነትና ተራ የግል አስተያየት የተለያዩ ናቸውና። የግል አስተያየት ትክከል ሊሆንም ላይሖንም
ይችላል ተብሎ ይታሰባል፤ እምነት ግን ለአማኙ ፍፁም ትክከል ነው። ፅንፈኝነት ሌላው እምነት በምድር ላይ እንዲኖር አለመፍቀድ
ነው::
21. አንተ ትክክል ነኝ የማለት መብት ለራስህ እንደሰጠህ ሁሉ ሌሎችም በተመሳሳይ . ትክክል ነኝ የማለት መብት እንዳላቸው
አትዘንጋ።
22. የዘር፣ ፣ የሃይማኖት፣ የቀዬ ወይም ሌላ የሚያቀራርብ ምክንያት አንድን ሰው ይበልጥ እንድትወደው ሊያደርግህ ይችላል፤
ይህ ከመሆኑ ጋር የሰው ልጅን በአጠቃላይ ግን ሰው በመሆኑ ብቻ ልታከብረው ግድ ይላል።
23. ሰዎች በናቅካቸው ልክ እንደሚንቁህ፣ ባዋረድካቸው መጠን እንደሚያዋርዱህና
በጠላኻቸው ያክል እንደሚጠሉህ እወቅ። ሰዎችን እየናቃቸው እን
53 viewsBekele Ejeta, 06:36
ክፈት / አስተያየት ይስጡ