Get Mystery Box with random crypto!

የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ የዓለማችን አሳሳቢ የጤና ችግር መሆኑን የአለም ጤና ድርጅት አስታወቀ በጥ | Our World

ዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ የዓለማችን አሳሳቢ የጤና ችግር መሆኑን የአለም ጤና ድርጅት አስታወቀ

በጥቂት አገሮች በቅርቡ የተከሰተው “የዝንጀሮ ፈንጣጣ” በሽታ የዓለማችን አሳሳቢ የጤና ችግር መሆኑን  የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ።

ድርጅቱ ዛሬ ባወጣው መግለጫ የዝንጀሮ ፈንጣጣ በሽታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተስፋፋ መሆኑንና ባልተጠበቀ ሁኔታ በዓለማችን በ70 ሀገራት ውስጥ በወረርሽኝ መልክ መከሰቱን ገልጿል።

በሽታው ክትባት ያልተገኘለትና ለሕክምናውም ከፍተኛ ኢቨስትመንት የሚጠይቅ በመሆኑ ሌላኛው የዓለማችን አሳሳቢ ወረርሽኝ ሆኗል ሲል የዓለም ጤና ድርጅት አውጇል።