Get Mystery Box with random crypto!

Muktarovich Ousmanova

የሰርጥ አድራሻ: @muktarovichousmanova
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 63.61K
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopia forever

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 149

2022-08-31 09:40:51
ሰቆጣ

በዋግሹሞች ምድር ሠቆጣ በጀግናው የሀገር መከላከያ ሰራዊት የሚመራው ጥምር ጦር የወራሪ ኃይሉን ሶስት ምሽግ ሰባብሮ ወደፊት እየገሰገሰ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።ራሱ ተንኩሶ መቱኝ አለ እንዴ? 11:00 መጥቶ ተኮሰ ከመጣህማ ብለው በሚገባው ሲያነጋግሩት ፍርስርሱ እየወጣ እንዳለ በስፍራው የሚገኘው የመረጃ ምንጨ ጠቁሞኛል።
ራያ፣ወልቃይት ሰቆጣ ሶስቱንም ግንባር ራሱ የህውሃት ወራሪ አስጀምሯል።መጨረሻው ቦሌ ወይስ መቀሌ የሚለውን አብረን የምናይ ይሆናል። ተነሱ፣ደግፉ ተነሱ፣በሉ ተነሱ

ስለጦርነቱ ቶሎ ቶሎ መረጃ ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ
http://t.me/wasulife http://t.me/wasulife
http://t.me/wasulife http://t.me/wasulife
http://t.me/wasulife http://t.me/wasulife

የቪዲዮና ድምፅ መረጃዎችን ለማግኘት የዩቲዩብ ቻናላችንን Subscribe ያድርጉ

https://www.youtube.com/channel/UCrdWHrcXNEhMfbp1ucgxd1g
16.6K views06:40
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-31 09:02:18
ጳጉሜን 1 ቀን 2014 ወደመንበራቸው ይመለሳሉ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት በሰሜን አሜሪካን የነበራቸውን የሕክምና ክትትል በማጠናቀቅ ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በወሰነው መሠረት ለሕክምና ሰሜን አሜሪካን የሚገኙት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የሚደረግላቸውን የሕክምና ክትትል በማጠናቀቅ ላይ የሚገኙ ሲሆን ጤናቸውንም በተመለከተ የተወሰነ መሻሻል ማሳየቱ ታውቋል።

በመሆኑም ቀደም ሲል በተያዘው የጉዞ መርሐ ግብር መሠረት ጳጉሜን 1 ቀን 2014 ዓመተ ምህረት ወደ ኢትዮጵያ የሚመለሱ ይሆናል።

EOTC
16.8K views06:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 22:57:01
ወላሂ ብየ ልማልና ልንገራችሁ እውነትም ወሎ ወንድ ልጅ አላት !!!

ሻለቃ ደምሌ አራጋው የወሎ ፋኖ የጦር አዛዥ
በትላንትናው እለት ጠዋት ላይ በጎብየ ሲያዋጋ ቆይቶ ከሰዓት ወርቄ የተገኘው አዳሩን ደግሞ አላውሃ ሲመክት እና ሲያዋጋ ያደረ የጁ ጊራና ያፈራችወ የነፃነት ቀንዲላችን ነው።

ዛሬም በድጋሜ ወርቄ ላይ ሲርገበገብ ውሏል።
የጦልሃ ጃዕፈር
የንጉስ ሚካኤል
የልጅ እያሱ
የበላይ ዘለቀ ፈለክ

የአራጋው አህመድ ልጅ ሻለቃ ደምሌ አራጋው ነው
ሻለቃ ደምሌ ቁጥብ ፣ ኮስታራ ስትቀርበው ደግሞ ተጫዋች ወንድም ነው።

ሻለቃ ሞገስ ከበደን ነገ እቀጥላለሁ

ይህ ታሪክህ ነው !!!
ለተጨማሪ መረጃ https://t.me/zenemTeshagariw
21.6K views19:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 21:46:05
ʺለእናት ሀገር መሞት የለውም ኩነኔ
ጠላት ለመደምሰስ ነቃ በል ወገኔ"

ይልሀል ማርኮ ታጣቂው የግዳን ሚሊሻ።
22.3K views18:46
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 21:37:49
አስታውሳለሁ አምና ደረጀ ሀብተወልድ አፋር ለተፈናቃዮች እርዳታ ሊያደርስ ሲሄድ ሴቶችና ህፃናትን ብቻ በመጠለያው አገኘ። ገረመው። ወንዶችስ ብሎ ሲጠይቅ፣
"እነሱማ ከትህነግ ጋር እየተዋጉ ነው" አሉት
ምን ለማለት ነው?
እንደ ህዝብ የመጣብህን እንደ ህዝብ መክተው። አለቀ
22.4K views18:37
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 20:30:16
#ጣርማበር_ሸዋ
ጀግንነቱን የጣርማበር የሚሊሻ አባላት በጀግንነት በተለያዩ አውደ ውጊያዎች ላይ ያረጋገጠው የጣርማበር ወረዳ ህዝባዊ ሚሊሻ ዝግጁቱን አጠናቆ ወደ ግንባር ለመትመም ዝግጁ ሆኗል። በባለፈው ጦርነት በርካታ ጀግኖች የህይወትና የአካል መስዋእትነት የከፈሉ ጀግኖች መኖራቸውን ጠቅሰው በዚህ ዙር እድሉን ያላገኙት ቅድሚያ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል ስምምነትም ተደርሷል።
@Shoa Press
24.1K views17:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 20:23:02 ዛሬ የምንሰማው ነገር አበረታች ነው። የሰማነው በወልዲያና አካባቢው ከሚኖሩ ሰዎች (from the horse mouth) ነው። ወራሪው ኃይል እንዳመጣጡ ወልዲያን መቆጣጠር አልቻለም። መከላከያ፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ ሚሊሺያና ፋኖ ባደረጉት ከፍተኛ ርብርብና ከባድ ተጋድሎ ወራሪው ኃይል ሽንፈቱን ተከናንቦ ተመልሷል። በርግጥ የውጊያ ውሎ ተለዋዋጭ ነው። ቢሆንም፣ ከትናንት ማታ ጀምሮ ከተፈጠረው ውዥንብር አንፃር፣ የዛሬው ውሎ ሊነገር የሚገባው ነው። ይህን ከመናገር ባለፈም፣ በግንባር እየተዋደቀ ላለው ጥምር ጦር ሁለንተናዊ ድጋፍ መስጠት አስፈላጊ ነው። ሁላችንም የቻልነውን እናድርግ
Ali Mohammed Ali
23.5K views17:23
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 19:20:16
የተረፉ እድለኞች። የተሸኘው ቁጥር ስፍር የለውም።
26.5K views16:20
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 19:15:48 ታሪክ የማይረሳው ተጋድሎ!

ህወሓት ወያኔ በራያ ግንባር እስካሁን ባለው መረጃ ከሁለት መቶ ሺህ የማያንስ ኃይል ይዞ መጥቷል። የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ የምስራቅ አማራ ፋኖ እና ሚሊሻው የታገለው ከዚህ ኃይል ጋር ነው። ባለፈው ቆቦን፣ ትናንት ወልዲያን ለመያዝ የአሸባሪው ቡድን ብዙ ኃይል አልቆበታል። በህዝብ መአበል የጀመረው ጦርነት ለወገን ጦር ከፍተኛ ግፊት የፈጠረ ቢሆንም በጀግንነት ሲፋለም ከርሟል።

ፌስቡከኛው ሰግቶ የሸሸ ወገናችን ፎቶ ይለጥፋል እንጅ ብዙ የሚነገርለት ጀግናም ሞልቷል። ለሰራዊቱ ደጀን የሆኑ ወጣቶች፣ ምግብ እያበሰሉ የሚያቀርቡ እናቶች፣ ሰብሉን ትቶ ከሰራዊቱ ጎን የተሰለፈው አርሶ አደራችን ታሪክም በደማቅ ታሪክ የሚፃፍ ነው። እነዚህ ጀግኖች ለክብራችን ተዋድቀዋል። ሌላው ህዝባችን እንዳይጎዳ በርካታ ዋጋ ከፍለውልናል።

በአካል፣ በስልክ፣ በፌስቡክ የማውቃቸውን የራያ፣ የወልዲያ አካባቢ ወገኖች ደውዬ አነጋግሬያለሁ። ብርታታቸው የሚገርም ነው። ቤተሰቦቻቸው የተገደሉባቸው፣ የተዘረፉባቸው፣ ቤተሰቦቻቸው ይሙቱ ይኑሩ የማያውቁ ናቸው። ብዙ ነገሮችን እምቅ አድርገው ችለው መንፈሳቸውን ያበረቱ ጀግኖች ናቸው። የቤሰተቦቻቸውን ሕመምና ስጋት በሚገባ ያልተረዳናቸው፣ ነገር ግን በርካታ ፅኑ ወገኖች አሉን። አሉባልታና ወሬ፣ ሰበርና አሳዛኝ ዜና ከሚለጠፈው በላይ የእነዚህ ጀግኖቻችን ፅናት ብዙ ትርጉም ነበረው። ለእኛ ሲሉ በየጥሻው ትህነግ ጋር ተናንቀው መስዋዕትነት የከፈሉ ጀግኖች፣ በአካባቢው ንቅንቅ ሳይል ለሰራዊቱ ደጀን የሆነው በርካታ ሕዝባችን ፅናት ሊያስተምረን፣ ላላወቀው ልናሳውቅ ሲገባ እንቶፈንቶው ሊያጨቃጭቀን አይገባም ነበር።

ጌታቸው ሽፈራው
25.7K views16:15
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-08-30 18:59:28 ሰበር መረጃ

ወልዲያን አሰፍስፎ ለመቀራመት የመጣው የህውሃት ወራሪና ዘራፊ ኃይል በጀግናው የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣የአማራ ልዩ ሀይልና ፋኖ የተከፈተበት ፈጣን የመልሶ ማጥቃት እርምጃ መቋቋም ባለመቻሉ የጣለውን ጥሎ ከአልውሃ ተጠቃሎ ሮቢትና አካባቢዋ መድረሱ ታውቋል።ጎብዬና አካባቢው በባለድሉ ጥምር ጦር ቁጥጥር ስር መሆናቸውን ለማወቅ ተችሏል።በሀራ በኩል ወደ ወርቄ ለመሄድ የነበረውም መቀልበሱን ሰምቻለሁ።የመረጃ ምንጮቼ እንደነገሩኝ ከሆነ ወደ ፊት የጥምር ጦሩ ፍጥነት ጨምሯል።በቅርቡ የምንሰማቸው አዳዲስ ጉዳዮች ይኖራሉ።ተከታትዬ አቀርባለሁ ህውሃት ወደ ጨለማ፣የትግራይ ህዝብ ወደ ብርሃን እየተጓዙ ነው ተደራጁ ደግፉ
Wasu Mohammed
24.2K views15:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ