Get Mystery Box with random crypto!

Muktarovich Ousmanova

የሰርጥ አድራሻ: @muktarovichousmanova
ምድቦች: ፖለቲካ
ቋንቋ: አማርኛ
ተመዝጋቢዎች: 63.74K
የሰርጥ መግለጫ

Ethiopia forever

Ratings & Reviews

2.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 151

2022-06-17 00:21:38
በወንዶች 5 ሺህ ሜትር የዳይመንድ ሊግ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በበላይነት አጠናቀቁ።

1ኛ ጥላሁን ሃይሌ ፣ 2ኛ ሳሙኤል ተፈራ፣ 3ኛ ጌትነት ዋሌ በተከታታይ በመግባት አሸንፈዋል።

ሌሎች ውድድሩን የተካፈሉ አትሌቶች ሚልኬሳ መንገሻ 5ኛ፣ አሊ አብዱለመና 10ኛ ሆነው አጠናቀዋል።
2.0K views21:21
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 19:32:36
በኢትዮጵያ የተሸነፉት ግብፆች የቡድኑን ዋና አሰልጣኝ አባረሩ።
.
የየግብፅ እግር ዃስ ፌዴሬሽን የብሄራዊ ቡድኑን ዋና አሰልጣኝ ኤሃብ ጋላል ከሃላፊነት ማሰናበቱን በይፋ አስታውቋል።

ከሳምንት በፊት በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የደረሰባቸው መራር ሽንፈት ለአሰልጣኙ መባረር ዋንኛው ምክኒያት ነው።

ሽንፈቱን ተከትሎ አሰልጣኝ ኤሃብ ጋላል ግብፅ በኢትዮጵያ እንድትዋረድ አደረጋት የሚል ከፍተኛ ውግዘት በአሰልጣኝ ከተለያዩ አካላት ሲሰነዘርበት ቆይቷል።

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታ መልስ ከፕሬዝዳንት ሲሲ ጋር ተገኝቶ ምክር የተሰጠው አሰልጣኙ ኮሪያ ላይም 4 ለ1 በሆነ ውጤት ተሸንፏል።

Abay News Network
8.7K views16:32
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 17:26:45
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዳኞችን አስመልክቶ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት በሰጡት ማብራሪያ ላይ ከአማራ ክልል ፍ/ቤት ዳኞች ማህበር የተሰጠ መግለጫ
11.3K views14:26
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-16 11:35:41
"ለሰብዓዊ ድጋፍ ወደ ትግራይ ከተጓዙት 3, 297 ተሽከርካሪዎች 1, 128ቱ አልተመለሱም»
የኢትዮጵያ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን
.
ምንጭ፦ ፕሬስ ድርጅት
ስትገባ የመታህ ድንጋይ አሁንም ስቶጣ ከደገመህ አንተ ምንድነህ ነበረ የሚባለው?
13.7K views08:35
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-15 14:57:24 ህውሃት ለድርድር ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ

የትግራይ ኃይሎች ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር ከ18 ወራት በላይ ሲያደርጉት የነበረውን ጦርነት ለማብቃት በኬንያ መንግሥት አሸማጋይነት በሚካሄድ ድርድር ላይ ለመሳተፍ ዝግጁ መሆናቸውን አስታወቁ።

በህወሓት ሊቀመንበር እና በክልሉ ፕሬዝዳንት ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል ተፈርሞ የተሰራጨው ደብዳቤ የወጣው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው መንግሥታቸው ጦርነቱን በሰላም ለማብቃት ፍላጎት እንዳለው ካሳወቁ በኋላ ነው።

ከህወሓት በኩል የወጣው ደብዳቤ ከዚህ በፊት ቡድኑ ለድርድር ያቀረባቸውን ቅድመ ኹኔታዎች አላካተተም።

የኬንያውን ፕሬዝዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ላደረጉት ጥረት አድናቆቱን የገለፀው ህወሓት፣ በድርድሩ ላይ ለመሳተፍ የሚችል ከፍተኛ የመልዕክተኞች ቡድን ወደ ኬንያዋ መዲና ናይሮቢ ለመላክ ዝግጁ መሆኑን አመልክቷል።

ደብዳቤው የአፍሪካ ሕብረት የሚጠበቅበትን ያህል አለማከናወኑን በመግለጽ አጥብቆ የተቸ ሲሆን፣ ባለፉት ወራት ሰላም ለማውረድ ከመቀለ አዲስ አበባ ሲመላለሱ በነበሩት የአፍሪካ ሕብረት ልዩ መልዕክተኛ ላይም ጥያቄ አንስቷል።

ለድርድር ዝግጁ መሆናቸውንም በተመለከተ “ለሰላም ተጨማሪ ርቀት ለመሄድ ዝግጁ መሆናችን ከደካማነት ወይም ከስግብግብነት በመነጨ የቆምንለትን መርህ ለመተው እንደ መዘጋጀት ተደርጎ መታየት የለበትም” ብሏል።

በዚህ ድርድርም በኬንያ መንግሥት መሪነት የአፍሪካ ሕብረት፣ የተባበሩት መንግሥታት፣ አሜሪካ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ ተሳታፊ እንዲሆኑም መጠየቁንም ቢቢሲ ዘግቧል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ማክሰኞ ትናንት ሰኔ 07 ቀን 2014 በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው እንደተናገሩት፣ መንግሥታቸው ከየትኛውም ወገን ጋር ሰላም ማውረድ እንደሚፈልግ ለዚህም ኮሚቴ ተዋቅሮ እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ኮሚቴው በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን የሚመራ እንደሆነና በገዢው ብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚ መሰየሙን አመልክተው፤ ሰላሙን በተመለከተ መሳካት ያለባቸው ተግባራትን፣ እንዲሁም ስለሚጠበቁ ነገሮች እያጠና መሆኑን አመልክተዋል።

“ከህወሓትም ይሁን ከማንኛውም ሰላም ፈላጊ ጋር የምንፈልገው ሰላም ነው፤ የሚቻል ከሆነ ለሰላም መቆም ችግር የለውም” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ጦርነት እንደማያተርፍና ከኹለቱም ጎን የሚያለማ ወጣት እየረገፈና አገሪቱም የምታወጣው ገንዘብ ከፍተኛ እንደሆነ ተናግረዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከህወሓት ጋር በሚደረገው ድርድር ይኸው ኮሚቴ ተደራዳሪ መሆኑን እና ኮሚቴው በቅርቡ የደረሰበትን ለፓርቲው ሲያቀርብ በይፋ ለሕዝብ በዝርዝር የሚቀርብ ይሆናል ብለዋል።

ቢቢሲ
13.1K views11:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-13 12:31:08
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ፍርድ ቤት ነገ እንዲቀርብ ዛሬ መጥሪያ ደርሷታል::

ጠበቃው አቶ ሄኖክ አክሊሉ እንደተናገሩት "ለነገ ሰኔ 7/2014 ዓ.ም ፍርድ ቤት እንዲቀርብ መጥሪያ ዛሬ እንደደረሰው አረጋግጫለሁ" በለዋል:: በዚህ መሰረት በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በአራዳ ምድብ ቻሎት ነገ ጠዋት 3:00 ሰዓት ላይ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ፍርድ ቤት ይቀርባል"::
(ወንድሙ ታሪኩ ደሳለኝ)
13.2K views09:31
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-10 21:09:56
#WazemaAlert
የኢትዮጵያ መንግሥት እና የትግራዩ ሕወሃት በታንዛኒያ አሩሻ ከተማ ድርድር ሊጀምሩ እንደሚችሉ ከምንጮች መስማቱን ጠቅሶ የፈረንሳዩ ሊ ሞንድ ጋዜጣ ዘግቧል። ጋዜጣው የአፍሪካ እና ምዕራባዊያን አገራት ዲፕሎማቶች የሁለቱ ወገኖች ድርድሩን ከሰኔ ወር ማለቂያ በፊት ሊጀምሩ እንደሚችሉ ነግረውኛል ብሏል። ምዕራባዊያን ዲፕሎማቶች ሕወሃት የአማራ ክልል ልዩ ኃይሎች በሚቆጣጠሩት ወልቃይት ግዛት ላይ ያለውን የይገባኛል ጥያቄ ቀስ በቀስ እየተወው እንደሆነ ጥቆማ መስጠታቸውን ዘገባው ጨምሮ ገልጧል። ከመጋረጃው ጀርባ በሚደረገው ድርድር ከሁለቱ ወገኖች ከእያንዳንዳቸው አምስት አባላት ያሏቸው ተደራዳሪዎች ሊሳተፉበት እንደሚችሉም ዘገባው ጠቅሷል። [ዋዜማ ራዲዮ]
6.9K views18:09
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-09 18:02:49
የብርጋዴር ጄነረል ተፈራ ማሞ የችሎት ውሎ
***
የአብክመ ጠቅላይ ፍ/ቤት ዛሬ ሰኔ 2 ቀን 2014 ዓ/ም በዋለው ችሎት የብርጋዴል ጀኔራል ተፈራ ማሞን ጉዳይ ተመልክቷል።

በዚህም ፤ የጊዜ ቀጠሮውን ጉዳይ መርማሪ ፖሊስ ምርመራየን ጨርሸ የምርመራ መዝገቡን ለዐቃቢ ህግ ለመላክ በዝግጅት ላይ ነኝ ያለ ሲሆን የክልል ዐቃቤ ህግ በችሎት ቀርቦ አዎ ምርመራው አልቋል የክስ መመስረቻ ጊዜ 15 ቀናት ይሰጠኝ ሲል ጠይቋል።

የተከሳሽ ጠበቃ በበኩላቸው ምርመራ ካለቀ ደንበኛችን የተከሰሱበት ጉዳይ ዋስትና የሚያስከለክል ባለመሆኑ እና ተጠርጣሪው ደንበኛችን ታዋቂ ሠው በመሆናቸው ሊጠፉ ስለማይችሉ የደንበኛችን የዋስትና መብት ይከበርላቸው ሲሉ ተከራክረዋል።

ፍርድ ቤቱም ሲሰጥ የነበረው የጊዜ ቀጠሮ ምርመራው ያለቀ በመሆኑ የጊዜ ቀጠሮውን ጉዳይ ዘግቷል። በመቀጠል የተጠርጣሪ ጠበቆች ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ዐቃቤ ህግ አስተያየት እንዲሰጥበት አድርጓል።

ዐቃቤ ህግ በበኩሉ የተከሰሱበት ጉዳይ የሽብር ወንጀል ስለሆነ በተጨማሪም ከሚዲያ ጋር በተያያዙ ሌሎች ተጨማሪ ክሶች ሊቀርቡ ስለሚችሉ ዋስትና ሊፈቀድላቸው አይገባም ሲል ተከራክሯል።
ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ሰምቶ የተጠርጣሪ የዋስትና ጥያቄ ላይ ብይን ለመስጠት ለነገ ለሰኔ 3/2014 ዓ/ም ቀጠሮ ሰጥቷል።
መረጃው የአብክመ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ነው

Via Yidnekachew Kebede
9.4K views15:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-09 12:14:15
ጠቅላያችን ሞቃድሾ የሀሰን ሼክ በዓለ ሲመትን ሊታደሙ ናቸው።
12.9K views09:14
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2022-06-07 12:24:39 ዝርዝር ዘገባ፦ ተመስገን ደሳለኝ፣ ሰለሞን ሹምዬ እና መዓዛ መሐመድ በ10 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲለቀቁ በፍርድ ቤት ተፈቀደላቸው

የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በ10 ሺህ ብር ዋስትና ከእስር እንዲፈታ የወሰነው በሁለት ምክንያቶች ነው። የመጀመሪያው ምክንያት ለፖሊስ በተሰጠው የምርምራ ጊዜ “በቂ ስራ ተሰርቷል ማለት ስለማይቻል” መሆኑን ችሎቱ አስታውቋል። ሁለተኛው ምክንያት ጋዜጠኛ ተመስገን የተጠረጠረበት “በመገናኛ ብዙሃን ሁከት እና ብጥብጥ የማነሳሳት ወንጀል” ባለፈው ዓመት በጸደቀው የመገናኛ ብዙሃን አዋጅ የሚታይ መሆኑ ነው።

በችሎቱ የተጠቀሰው የመገናኛ ብዙሃን አዋጅ “በመገናኛ ብዙሃን አማካኝነት የወንጀል ድርጊት በመፈጸም የተጠረጠረ ማንኛውም ሰው ወይም አካል፤ በወንጀል ስነ ስርዓት ሕግ ድንጋጌዎች መሰረት ለተጨማሪ ምርመራ በእስር እንዲቆይ ሳይደረግ ክሱ በቀጥታ በዐቃቤ ህግ አማካኝነት ለፍርድ ቤት መቅረብ አለበት” ሲል ይደነግጋል። ጋዜጠኛ ተመስገን በፖሊስ ቁጥጥር ስር ከዋለበት ግንቦት 18 ጀምሮ ለ12 ቀናት በእስር ቆይቷል።

በዛሬው የችሎት ውሎ ከተመስገን በመቀጠል ጉዳዩ የታየለት ጋዜጠኛ ሰለሞን ሹምዬ ነው። ከ18 ቀናት በፊት በፖሊስ የተያዘው ሰለሞን ሹምዬ እንደ ተመስገን ደሳለኝ ሁሉ የተጠረጠረው ሁከት እና ብጥብጥ በማነሳሳት ወንጀል ነው።
12.1K views09:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ