Get Mystery Box with random crypto!

ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

የቴሌግራም ቻናል አርማ memehirhenok — ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
የቴሌግራም ቻናል አርማ memehirhenok — ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
የሰርጥ አድራሻ: @memehirhenok
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 12.40K

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 8

2023-04-15 10:02:06 ዛፍዋም ከአንድም ሁለት ሦስቴ ብትነገረኝ እኔ ዘዴዬ ያዋጣኛል ብዬ ብልጠት ለመጠቀም ሞከርኩ፡፡ ብልጠቴ ምን መሰላችሁ፡፡ ጌታችሁ ከዘጠኝ ሰዓት በኋላ ለአምስት ሺ አምት መቶ አመታት ሲሰቃዩ የነበሩትን ነፍሳት ለማውጣት ሲኦል እንደሚወርድ አውቅ ነበር፡፡

እኔም ጌታችሁ በራሱ ሥልጣን ዘጠኝ ሰዓት ቅድስት ነፍሱን ከክቡር ሥጋው ሳይለይ ቀድሜ ሞቼ ሲኦል ዱቅ ብዬ ልጠብቀው ወሰንኩ ምክንያቱም ከሲኦል ከሚወጡት ነፈሳት ጋር አብሬ ልወጣ፡፡ ኡኡቴ ተዘይዶ ተሞቷል፡፡

ጌታችሁም ብልጠቴን አውቆ ከዛፉ በጢንቢራዬ ቢጥለኝ አንጀቴ ተዘርግፎ ለአርባ ቀን በሰቀቀን ሳልሞት ቆየሁ፡፡ ጌታችሁ በሲኦል ያሉትን ነፍሳት ጥርግርግ አድርጎ ካወጣ በኋላ እኔ በአርባ ቀኔ ሞትኩ፡፡ አዳሜ ገነት ለመግባት የሚያስፈልገው ዘዴ/ብልጠት/ ሳይሆን ሕጉን መጠበቅ፣ ምግባር መሥራት ወዘተ ነው፡፡ በብልጠት የትም አትደርሱም፡፡

ጀለሶቼ ሲኦል ስሄድ ከሦስት ሰዎች በስተቀር ሲኦል ኦና ሆና ጠበቀችኝ፡፡ እነዚህ ሦስት ሰዎች ያልኳችሁ ጌታ በእለተ አርብ ከሲኦል ያላወጣበት ምክንያት በደላቸው፣ ኃጢአታቸው አገር አቀፍ ስለሆነ ነው፡፡ እነሱም ፈርዖን፣ ጽሩ ጻይዳ እና ሔሮድስ ናቸው፡፡

የፈርዖንን በደል እና ኃጢአት ዘመናችሁን ስትሰሙት፣ ስትማሩት ነው ያደጋችሁት ታሪኩን ለእናንተ ትቻለሁ፡፡ ጽሩ ጻይዳ በምድያምና በሜዶን አምልኮተ ጣዖትን አስፋፍቷል፤ ይባስ ብሎ ንጹሐኑን የመቃቢስን ልጆች ሲላ፣ አብያና ፈንቶስን አስገድሏል፡፡

ሔሮድስም እንደምታውቁት አሥራ አራት እልፍ/መቶ አርባ ሺ ሕፃናትን አስፈጅቶ፣ እስራኤልንም በደም ውሃ አርግቶ ግፍ ሠርቷል፡፡ እነዚህ ሦስቱ ክፉ ሰዎች ጌታችሁ በዲያቢሎስ መንግሥት በሲኦል ተዋቸው፡፡ ምክንያቱም ፍዳቸው ፅኑ ነውና፡፡ ሲዖልም አትለቅም ገነትም አትቀበልም፡፡

ጋይስ አጅሬም በሲዖል ብቻዬን አገኘኝ፡፡ ተዉ ያደረገልኝን የመከራ አቀባበል በቃላት ልነግራችሁ አልችልም፡፡ ጌታ የማረከበትን የሺ ዓመታቶች ነፍሳት ብስጭት እኔ ላይ ተወጣ፡፡ ያላደረገኝ ያላሰቃየኝ ነገር የለም፡፡ ስቃዩን ስትመጡ ስለምታዩት ያኔ ትረዱኛላችሁ፡፡

ነፍሳት ከሲኦል ሲወጡ፣ በሲኦል እንደ ተዋጡ የቀሩ ሦስቱ የሲዖል ጀለሶቼ ‹‹ዩዲ አይዞኝ እኛም እንዳንተ ተከርቸም ውስጥ ገብተን በነፍሳችን ቶርች ስንደረግ ነው የከረምነው፣ ዩዲ ሲዖል ቻል ነው የሚደረገው እንጂ አይለቀስም፡፡ ለነገሩ ብታለቅስ ማን ሊደርስልህ›› ብለው መከሩኝ ልበል አጽናኑኝ አላውቅም፡፡

ይኸው ሲኦልን ግዛቴ ርስቴ አድርጌ ከተቀመጥኩ ሁለት ሺ ዓታት አለፉኝ፡፡ ወድጄም በትንቢት ተገድጄም ጌታዬን ብሸጥም ለሳጥናኤል በሲኦል እየተገዛሁ እኖራሉ፡፡ ጀለሶቼ ገና ምን አየሁ ያ ‹‹ገሃነመ እሳት›› የሚባል ይጠብቀኛል አሉ፡፡

ዞሮ ዞሮ ነብዩ ኤርምያስ በትንቢቱ ‹‹ከእስራኤል ልጆችም አንዳንዶቹ የገመቱትን፣ የተገመተውን ዋጋ ሠላሳ ብር ያዙ›› የተባለው ቀደምት ትንቢት፤ የዕንባቆምም ንግርት፤ ጌታችሁም የተናገረብኝ ሁሉ ደርሶብኝ ባልበላሁት ሠላሳ ብር ጌታችሁን ሽጬ ለዘመነ አዝማናት አሳሬን እበላለሁ፡፡

ጋይስ እኔ አሁን በሲኦል እየተቀበልኩ ያለሁት መከራ ከበቂዬ በላይ ነው፡፡ ግን እናንተ ሁሌም በየዓመቱ ስትረግሙኝ ስትደበድቡኝ በኋላ በሲኦል ተገናኝተን ከምንላቀስ፤ ለራሳችሁ ብትጠነቀቁ፣ የጌታችሁን ትዕዛዛት ብትጠብቁ፣ ንስሐም ገብታችሁ ብትጸድቁ ነው የሚያዋጣችሁ፡፡ ለማንኛውም የእኔ ፋሲካ በሲኦል መሰቃየት ስለሆነ እችለዋለሁ፡፡ ‹‹ላይችል አይሰጥ›› አሉ!

አንድ ነገር እወቁ የሲኦል የመግቢያ በር ላይ ለሚመጡት ምስኪን ነፍሳት አቀባበል የማደርገው እኔ ስለሆን ወደ ተሻለ የስቃይ ቦታ ለመሄድ ከፈለጋችሁ በመልክ ባታውቁኝም ‹‹ዩዲ›› ካላችሁኝ የሐበሻ ፈገግታ እና ሰላምታ ሳቀርብ እኔ መሆኔን እወቁ፡፡ ይቺ የሲኦል የመግባብያ ኮዳችን ትሁን፡፡

እኔ ካለሁበት እስክትመጡ በሲኦል ናፍቆት እጠብቃቹኃለሁ፡፡

ዩዲ ከሐዲ ነኝ ከሲኦል!

የዓመት ሰው ይበለን!

ሚያዝያ 7-8-15 ዓ.ም
አዲስ አበባ
219 views07:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 10:02:06 እኔ ሆዬ የጨላ ከረጢቴን አጥብቄ እንደያዝኩ አንድ ሐሳብ አወጣ አወርድ ጀመር፡፡ ጌታችሁም ሐዋርያትን ለማረጋጋት እኔ እንጂ እነሱ አሳልፈው እንደማይሰጡት እንደማይሸጡት ለማሳወቅ ‹‹እኔ ቁራሽ አጥቅሼ የምሰጠው እርሱ ነው›› ብሎ ለእኔ ሰጠኝ፡፡ ይገርማቹኃል ያኔ በገንዘብ ፍቅር የገባው ሳይሆን ዋናው ሰይጣን በልቤ ገባ፡፡

ስፖንሰሬን ልብ አላችሁ? ጌታችሁም ‹‹የምታደርገውን ቶሎ አድርግ›› አለኝ፡፡ ጌታችሁ እንዲህ ሲለኝ ሐዋርያት አልባነኑም ነበር፡፡ እነሱ ጌታቸው ለበዓሉ የሚያስፈልገውን ነገር እንድገዛ ለድሆች እንድመጸውት ያዘዘኝ ነው የመሰላቸው፡፡ አይገርምላችሁም! ካላመናችሁ ዮሐ 13÷29 አንብቡ፡፡ ያኔ ሰይጣን እራሴን መቆጣጠር እስኪያቅተኝ ድረስ ወሰወሰኝ፣ ጌታችሁን ሽጥ ሽጥ አለኝ፡፡

የሚገርማቹ ሰው እንደ ዕቃ መሸጥ ባልተለመደበት እንዴት ጌታችሁን እንደሸጥኩት እስከ ዛሬ ይገርመኛል፡፡ ምን ላድርግ ትንቢት ነዋ፡፡ ደግሞም የጨላዋ ከረጢት በእጄ እያለች ጌታችሁን ለመሸጥ መሯሯጤ ዛሬም ምን ነክቶኝ ነው እላለሁ፡፡ ግን ትንቢት ነዋ፡፡

ብዙዎች ‹‹ጌታህን ለምን በሠላሳ ብር ብቻ ሸጥከው›› ይሉኛል፡፡ ትንቢቱ እንዳለ ሆኖ ዮሴፍ የሚባል ጻድቅ ሰው ወንድሞቹ በሃያ ብር ሽጠውት እንደነበር ሰምቻለሁ። ከዮሴፍ ላስበልጠው ብየ ነው በሠላሳ ብር የሸጥኩት፡፡ ደግሞም እኔ ሆኜ ነው ሠላሳ ብር የሸጥኩት፡፡ አይሁድ ጌታችሁን ይጠሉት ስለነበር እንኳን ሠላሳ ብር አንድ ብርም አይሸጡትም ነበር፡፡

እውነት እናውራ ከተባለ "ይሁዳ ጌታውን ሸጠ" ትላላችሁ። እናንተ ጌታችሁን ስንቴ ሽጣቹኃል? ስንቴ ክዳቹታል? ስንቴ በድላቹታል? ስንቴ ሕጉን አፍርሳቹኃል? በቤተ ክርስቲያን እያገለገለ ሰዉግ በመተት የሚያሰቃየው መተተኛ ኃጢአቱ ከእኔ ቢብስ እንጂ የሚያንስ አይደለም።

በቤተ ክርስቲያን እያገለገሉ እየተመላለሱ መተት የሚመትቱ እኮ ከእኔ የባሰ ጌታቸውን የካዱ ናቸው። ሙዳየ መጽዋት የሚገለብጡት፣ ከቤተ ክርስቲያን ገንዘብ የሚዘርፉት አገልጋይ ተብዬዎች በምን ሞራላቸው ነው "ይሁዳ ጌታውን በሠላሳ ብር ሸጠ" ብለው የሚናገሩ የሚያስተምሩ? ስለ እውነት ፍረዱ!

እኔ አንዴ ነው ጌታችሁን የሸጥኩት የካድኩት። መቶ ጊዜ ጌታችሁን የካዳችሁ፣ የሸጣችሁ የላችሁም? እኔ ጌታችሁን አንዴ ነው ያሳዘንኩት የካድኩት። እናንተ ጌታችሁን ስንት ጊዜ አሳዝናቹኃል ክዳቹኃል? ትንቢት ሳይነገርባችሁ ትንቢት የምትፈጽሙ አይደላችሁ?

በእውነት ጌታችሁ በዚህ ዘመን ሊሰቀል ቢመጣ እንደው ስንት ብር ትሸጡት ነበር? በዳይሬክት ነው ወይስ በጨረታ? ደላሎችስ ስንት ብር በጌታችሁ ላይ ፈርቅ ትይዙ ነበር? የሚስማር ፋብሪካዎች ‹‹እኔ ከንጽህ ብረት የተዘጋጀ ምርጥ ሚስማር ችንካር አቀርባለሁ›› ይላል፡፡

አንዱ የእንጨት ፋብሪካ ‹‹እኔ ለስቅላት የሚያመች፣ እጅ እግር ከወርች የሚያስቸነክር ጠንካራና ጌታን የሚሸከም መስቀልኛ እንጨት አቀርባለሁ›› ይላል፡፡

አንዱ የቆዳ ፋብሪካ ‹‹ተረፈ ምርት ከሆነው ቆዳ ደንበኛ ሥጋን የሚያሳርር ደንበኛ መግረፊያ ጠፍር አቀርባለሁ›› ይላል፡፡ እናንተስ ስቃዩን እንደ ዮሐንስ እያለቀሳችሁ ከማየት ይልቅ ሰልፊ ለመነሳት አይደል የምትሯሯጡት?

ፎቶውን በፌስ ቡክ፣ በኢንስታ ግራም ወዘተ ላይ ፖስት ለማድረግ እንጂ ፎቶውን እያያችሁ ለማንባት አትቸኩሉ፡፡ ብቻ ጉድ ነው!

ከዛማ ጌታችሁንና ሐዋርያትን ትቼ ጌታችሁን ለመሸጥ ገዢ ፍለጋ ወጣሁ፡፡ ስበር ስከንፍ ሄጄ የአይሁድ አለቆችን አገኘሁ፡፡ እኔም ‹‹እንደ ጠላት የምታዩትን ሰው አሳልፌ እሰጣችኃለሁ ምን ትሰጡኛላችሁ›› አልኳቸው፡፡

እነሱም የጨላ ነገር እንደማይሆንልኝ ማን እንደነገራቸው አላውቅም ‹‹ሠላሳ ብር እንገጭኃለን አንተ ብቻ አሳልፈህ ስጠን›› አሉኝ፡፡ እኔም ተስማማሁ፡፡ ሠላሳ ብር ገጩኝ፡፡ ከዛማ በቃ ጌታችሁን ለመሸጥ ቀብዲ ኸረ የምን ቀብዲ ሙሉ ክፍያውን ተቀብዬ ጌታችሁን አሳልፌ የምሰጥበትን መንገድ ማሰብ ሥራዬ ሆነ፡፡

አንድ ቀን ጌታችሁ እኔን ሳይጨምር ደቀ መዛሙርቱን ይዞ ሊጸልይ ወደ ደብረ ዘይት ተራራ ሄደ፡፡ ይህ ቦታ ጌታችሁ እንደሚውልበት እንደሚያድርበት አውቅ ስለነበር ከዚህ የበለጠ ምቹ ጊዜ አላገኝም ብዬ የአይሁድ አለቆችንና ወታደሮችን አስከትለን እሱ ወደለበት ሄድን፡፡

አይሁድም ‹‹እሱን በምን እናውቃለን›› አሉኝ። አይሁድ ይህን ያሉት ጌታችሁ እና የድሮ ጓደኛዬ ዮሐንስ በመልክ ስለሚመሳሰሉ መለየት ስለማይችሉ ነው። እኔም ‹‹ቀጥታ ሄጄ የምስመው እርሱ ስለሆነ ያኔ ያዙት›› ብዬ ነገርኳቸው፡፡

ይገርማቹኃል ጌታችሁ እኔን ሲያይ ፊቱ ላይ ያለው የፍቅር ፈገግታው አሁንም በሲኦል ሆኜ አልረሳውም፡፡ ጌታ በፍቅር ሲቀበለኝ እኔ በተንኮል መሳም ሳምኩት። እሱም ስላወቀብኝ ‹‹ይሁዳ ሆይ፣ በመሳም የሰውን ልጅ አሳልፈህ ትሰጣለህ›› ሲለኝ አንጀቴ ሳይሆን ነፍሴ ተላወሰች፡፡

ግን ምን ላድርግ እኔ ጌታችሁን አሳልፌ የሰጠሁት ስስመው ሳይሆን ሠላሳ ብር ስቀበለው ስለሆነ አሳልፌ ሰጠሁት፡፡ ዛሬም እናንተ ጌታችሁ የሰጣችሁን ጸጋ፣ ክብር፣ አደራ፣ ታማኝነት፣ እምነት ለኃጢአት/ለሰይጣን አሳልፋችሁ ትሰጣላችሁ፡፡

ጌታችሁን ሲያንገላቱት ሲመቱት ሳይ አንዳች ነገር ተሰማኝ፡፡ ገንዘብ ወዳድነቴ፣ ሌባነቴ፣ ከሃዲነቴ፣ እምነት አጉዳይነቴ፣ ላመነኝ ጌታችሁ አለመታመኔን ሳስብ ወዲያው የአይሁድ አለቆች ጋር ሄጄ ‹‹ንጽህ ደም አሳልፌ በመስጠት በድያለሁ›› ብዬ በጸጸት ተናገርኩ።

ሠላሳ ብሩንም ውሰዱ አልኩ፡፡ እነሱም ‹‹አንተው ተጠንቀቅ እራስህ ተወጣው›› አሉኝ፡፡ እኔም ጌታችሁን የሸጥኩበትን ሠላሳ ብር በቤተ መቅደስ ጥዬ ሄድኩ፡፡ በጣም የሚያሳዝነው ፈራጆች ሠላሳ ብሩን ላልበላው ላልጠቀምበት ነው ጌታችሁን የሸጥኩት። በቃ ትንቢት ነዋ! ባደረኩት ነገር እራሴን ወቅሼ ለማረጋጋት ባለመቻሌ ለእኔ ሞት ይገባኛል ብዬ እራሴን ሰቅዬ አጠፋሁ፡፡

ግን አንድ ነገር ልብ በሉ፡፡ ብዙ ሰው ጌታችሁን መሸጤን እንጂ ክፍኛ መጸጸቴን ልብ አይሉም፡፡ በእጃችሁ ያለው መጽሐፍ ቅዱስ ጸጸቴን አስመልክቶ ‹‹ተጸጸተ›› ብሎ መስክሮልኛል ደግሞም ጸጸቴ የእውነት ሳይሆን የውሸት ቢሆን ኖሮ የእውነት ቃልን የያዘው ቅዱሱ መጽሐፍ ‹‹ተጸጸተ›› ብሎ አይመሰክርልኝም ነበር፡፡ በእውነት መጸጸቴን ካላመናችሁ የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 27፥ 3 አንብቡ!

ታድያ እናንተ በሠራችሁት ስህተት እና ኃጢአት እንደ እኔ ተጸጽታችሁ ታውቃላችሁ? ብትጸጸቱማ ከስንት የክፋት መንገዳችሁ፤ ከስንት የዝሙት ወዘተ የኃጢአት ሕይወታችሁ ትመለሱ ነበር፡፡ ግን ማትመለሱት ጸጸታችሁ ጊዜያዊ ስለሆነ ነው፡፡

ኤኒ ወይስ ጌታችሁን የሸጥኩበት ብር ለእኔም ለአይሁድም ሳይሆን አይሁድ ‹‹የደም ዋጋ ነው›› ብለው ለእንግዶች የመቃብር ስፍራ እንዲሆን መሬት ገዙበት፡፡ ያ የደም መሬት ዛሬም እስራኤልና ፍልስጥኤም ደም ሲፋሰሱበት ይኖራል፡፡ የዛሬ ሁለት ሺ ምናምን ዓመት ጌታችሁን የሸጥኩበት የሠላሳ ብር ገዳፋ፣ እስራኤልንና ፍልስጥኤምን ዛሬም ሲያዳፋ ይኖራል።

የሚያሳዝነው ያኔ ጌታችሁ እንደ ጴጥሮስ የሰጠኝን የንስሐ እድል ብጠቀምበት ኖሮ ዛሬ መኖርያዬ ሲኦል ሳይሆን ገነት ነበር፡፡ እራሴን ላጠፋ ዛፍ ላይ ስንጠለጠል ዛፍዋ ‹‹ይሁዳ ሆይ እንደ ወንድምህ እንደ ጴጥሮስ ንስሐ ግባ›› ስትለኝ አልሰማም አልኩኝ፡፡ ዛሬም ንስሐ ግቡ ሲባሉ የማይሰሙ እንደ እኔ የደነደነ ልብ ያላቸው ስንት አሉ፡፡
167 views07:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-15 10:02:05 ስንት_ይሁዳ_እያለላችሁ_እኔን_ለምን_በየዓመቱ ትደበድባላችሁ?

/በምናቤ የሳልኩት፣ የይሁዳ ብሶት ከሲኦል/

የዛሬ አምስት ዓመት የተጻፈ!

ክፍል ሁለት /የመጨረሻው/

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ጋይስ ይሁዳ ነኝ! እንዴት ዋላችሁ አደራችሁ ልል ብዬ በሲኦል ቀንና ማታ የሚባል የለም፡፡ ስለዚህ በሲኦል መዋል ማደር የለም በስቃይ መኖር እንጂ፡፡ ይህንን ማመን ካቃታችሁ ስትመጡ አይታችሁ ታምናላችሁ፡፡ አይ ሐበሻ አቤት ወሬ ስትወዱ፡፡ አሁን የእኔን ብላክ ስቶሪ ለመስማት ቸኩላቹኃል አይደል፡፡ ለነገሩ ከእኔ ብትማሩ ባትማሩም ልንገራችሁ ምክንያቱም እኔም ከጌታዬ ስላልተማርኩ፡፡

ዳይ ወደ ገደለው፡፡ እናላችሁ… በሰፈሬ አንበሳ ሳልሆን አደገኛ የዝንጀሮ ገመሬ ሆኜ አደኩ፡፡ በኋላ ያሳደገኝ የአስቆሮቱ አገርና የወላጅ አባቴ የይሁዳ አገር ሰዎች ጦርነት ገጠሙ፡፡ እኔ ሆዬ ምንሽሬን ይቅርታ ቀስቴን ታጥቄ፣ ጦሬን ሰብቄ፣ ጋሻዬን በደረቴ ደቅድቄ ዘመትኩ ጦርነቱም ተጀመረ፡፡

ጥቂት እንደተዋጋን አንድ ጠና ያለ ሰው ‹‹እጅ በአየር፣ መሳርያ በምድር›› ብሎ ሊማርከኝ ፈለገ፡፡ እኔም ዩዲ ‹‹ሳትቀደም ቅደም›› ብዬ ፊቴ የቆመውን ጠና ያለው ሰውዬ ላይ እንደ ነብር በመወርወር ወደቅሁበት፡፡ ሰውዬውም ጥንቢራው ዞሮ እራሱን ሳተ፡፡ እኔ ልምታው መላክ ይቅሰፈው አላወቀም፡፡ ጓደኛዬ ‹‹ዩዲ ሳትሰለብ ስለብ›› አለኝ፡፡ በነገራችን ላይ ዩዲ ጓደኞቼ ይሁዳ የሚለውን ስም ሲያቆላምጡ የሚጠሩኝ ስም ነው፡፡

እኔም ጠና ያለውን ሰውዬ ገድዮ ሰለብኩት፡፡ ምርኮውን ከበዘበዝኩ በኋላ ወደ ጠላት ሰፈር ስገባ አንዲት ጎልማሳ ሴት አግኝቼ ማረኩ፡፡ የማረኳትን ሴት ሚስት ትሆነኝ ብዬ ወሰድኳት፡፡ አብረንም አደርን። መቼም አብረን ስናድር ጣራ ስንቆጥር እንደማናድር ታውቃላችሁ። የሚሆነው ነገር ሁሉ አድርገን አደርን፡፡ ኦህ ዩዲ…ታሳዝናለህ!

ታድያ አብሮ ያደረ ሰው ግለ ታሪክ መጠያየቁ አይቀርምና ያገሬውን የወንዜውን አውርተን ወደ ራሳችን ታሪክ መጣን፡፡ በሚያሳዝን ሁኔታ ያቺ የማረኳት እንደ ሚስትም ያደረኳት ሴት ወላጅ እናቴ ሆና ተገኘች፡፡ እኔም ልጇ ሆኜ እርፍ አልኩት፡፡

በጦርነቱም ወቅት የገደልኩትና ብልቱን የሰለብኩት ጠና ያለ ሰውዬም ወላጅ አባቴ መሆኑን አወኩ። የነብዩ የእንባቆም ትንቢትም "እናቱን ያገባል፣ አባቱን ይገድላል ይሰልባል" የተባለው ጠብ ሳይል በእኔ ተፈጸመ።

ያ ድራማቲክ የመሰለ ሕይወት በእኔ ሲከሰት ግራ በመጋባት እጅግ ተጨነኩ፡፡ ያ ዘመን ደግሞ ጌታችሁ መጥቶ ወንጌል የሚያስተምርበት፣ ድውያንን የሚፈውስበት በአጠቃላይ ጌታችሁ በኢየሩሳሌም ልዩ ክስተት የነበረበት ዘመን ስለሆነ ከማዙካ ጋር ተነጋግረን በሼም የታጠረውን ታሪካችንን ይዘን ወደ ጌታ መጭ አልን፡፡ ወደ ጌታችሁ ለመሄድ የወሰነው ኃጢአተኞችን ያቀርባል፣ ይቅር ይላል፣ ሲበዛ ሰው ወዳድ ነው የማለውን ወሬ ሰምተን ነው።

ጌታ ጋር ደርሰን ያለውን ሂስቶሪ ዋን ባይ ዋን ነገርነው፡፡ ጌታም በገጠመን ነገር እኛን ከመኮነን ይልቅ በማዘን አጽናናን፤ ብዙ መከረን አስተማረን፡፡ በተለይ እኔን ዓይን ዓይኔን እያየ ሲናገረኝ ነብሴ ትንቀጠቀጥ ነበር፡፡ ያ የሐዘኔታና ‹‹ትሸጠኛለህ›› የሚል ዕይታው ዛሬም ድረስ በሲኦል ውልብ ይልብኛል፡፡

ጌታችሁም ሳያሳፍረን/ጌታችሁ የምለው ጌታዬ ብዬ ለመጥራት በሥራዬ ስለማፍር ነው/ ማዙካን ከሠላሳ ስድስቱ ቅዱሳን አንስት፤ እኔንም ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ጋር ቆጠረን፡፡ ለእኔም እንደ ጓደኞቼ ስልጣን ጸጋን ሰጠኝ፡፡

ምን ዋጋ አለው እኔ ሁሌ ምሾፈው ስልጣኔን፣ ጸጋዬን ሳይሆን እንደ ዘመኑ አንዳንድ ካህናትና አስተዳዳሪዎች በሙዳየ ምጽዋት ውስጥ የምትገባውን ጨላ ብቻ ነው፡፡ በነገራችን ላይ ጌታችሁ በሰጠኝ ስልጣንና ጸጋ ድውይ ስፈውስ፣ ለምጽ ሳነጻ አጋንንት ሳስወጣ እንደነበር ስንቶቻችሁ ታውቃላችሁ?

በተለይ አንድ ቀን እንዴት እንደተናደድኩ ልነግራችሁ አልችልም፡፡ ታሪኩ እንዲህ ነው፡፡ በዛ በለምጻሙ በስምዖን ቤት ተጋብዘን፤ ከጌታችሁ ጋር ሰብሰብ ብለን እያለን አንዲት ሴት በውድ ዋጋ የተገዛ ሽቱ ይዛ ከች አለች፡፡ አልባስጥሮስ ሽቱውን ስከልመው ፐ ብሸጠው ብዬ ጆፌዬን ጣልኩበት፡፡

ልጅቷም ተአምረኛ ነች ያንን ሁሉ ሽቱ ጌታዋ ላይ አርከፈከፈችው፡፡ እኔ ዝም ብዬ ከልማታለሁ፡፡ እሷም አውቃለች መሰለኝ በቆረጣ እያየችኝ ሽቶውን በሙሉ ጌታ ላይ አርከፍክፋ ስትጨርስ ይባስ ብላ የጌታዋን እግር በእንሳዋ አበሰችው፡፡ ዞር ብዬ ስሾፍ ጌታችሁ ላይ ያርከፈከፈችውን ሽቶ ባዶ ጠርሙሱን እግሬ ስር ጣለችው። በጣም ተናድጄ "ቁረሌው መሰልካት እንዴ ሽቶ የሌለውን ባዶ ጠርሙስ እግሬ ስር የምትጥለው" ብዬ ልናገራት አልኩና ጌታችሁን ፈርቼ ተውኩት።

በተለይ የሽቱው ብልቃጥ ባዶውን መሬት ላይ ሆኖ ስከልም በቅናት ተቃጠልኩ፡፡ መሬት መሬቱን እያየሁ ለጌታችሁ አንድ ሐሳብ አቀረብኩለት ‹‹ይህ በብዙ ዋጋ ተሸጦ ለድሆች ሊሰጥ ይችል ነበር›› ብዬ አዛኝ አንጓች ሆንኩ፡፡ ጌታችሁም ነውር የነበረ ንግግሬን በፍቅር ‹‹ድሆች ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር ይኖራሉ፣ እኔ ግን ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር አልኖርም›› ብሎ ሴቲቱን መልካም ሥራ እንደሠራች በሁላችን ፊት አመሰገናት፡፡ ካላመናችሁ ማቴ 26÷6-13 አንብቡ፡፡

ጭራሽ ያደረገችው ነገር ‹‹ወንጌል በሚሰበክበት ቦታ ሁሉ ለመታሰብያ ይሆናል›› ብሎ ቃል ኪዳን ገባላት፡፡ ጉድ በል ሳጥናኤል….ከዛማ የእኔ ነገር ጨላ ላይ ማፍጠጥ፤ ካዝና ላይ ማጉረጥረጥ ሆነ፡፡ ከመቶ አስሬን እየቦጨኩ ፍራንካውን እንዲው ላልበላው መቀገር ሆነ ሥራዬ፡፡ በገንዘብ እና በሰይጣን መለከፍ አያድርስ ነው!

የሚገርማችሁ አሁን በየ ቤተ ክርስትያኑ ያሉ አገልጋይ ሳይሆኑ ተገልጋዮች ሙዳየ ምጽዋት እየከለሙ መገልበጥ መስረቅ የጀመሩት ከእኔ ኮርጀው ነው፡፡ አሁን ባልጠፋ ነገር እኔን ለሲኦል ዳፋ የዳረገኝን ነገር ከእኔ አይማሩ? ለዚህ እኮ ነው ‹‹ስንት ይሁዳ እያለላችሁ፤ ለምን እኔን በየዓመቱ ትወግራላችሁ›› የምለው፡፡ የምር በየ በተስክያኑ ስንት የሚወገር አስተዳዳሪ፣ ሒሳብ ሹም፣ ጸሐፊ፣ ተቆጣጣሪ፣ ጨላ ቆጣሪ አለላችሁ፡፡

ኤኒ ወይስ ችግር የለውም እያንዳንድሽ እኔ ጋር ስትመጪ የሙዳየ ምጽዋዕት ገንዘብ ገልብጠሸ፣ ቆጥረሽ የበላሽ ሁላ መከራሽን ትቆጥርያለሽ፡፡ ማን የሚሉት ዘፋኝ ነው ‹‹እኛን ነው ማየት ስትመጪ እሱ ብሎት፤ ለጉድ ተናንቀን በእንባ አንገት ላንገት›› ያለው፡፡ ጌታችሁ ሳይሆን ሥራችሁ ፈርዶባችሁ ሲኦል ስትመጡ ተቃቅፈን እንደምንላቀስ ተስፋ አለኝ፡፡

ከዚህ በኋላማ በውስጤ የጌታችሁ ፍቅር ሳይሆን የጨላ ፍቅር አደረ፡፡ ነጋ ጠባ ስለ ገንዘብ ነው የማስበው፡፡ ከመቶ አሥር የማገኘው አልበቃ ሲለኝ ከሐዋርያት ልቀፍል እፈልግ ነበር፡፡ ምን ዋጋ አለው እነሱ ጋር የማይነጠቅ የጌታቸው ጸጋና ፍቅር እንጂ የሚቀፈል ጨላ የላቸውም፡፡

ትዝ ይለኛል! የጸሎተ ሐሙስ ቀን ጌታችሁን ከጓደኞቼ ጋር ግራ ቀኝ ከበነው የመጨረሻ እራት እየበላን ሳለን፤ እኔ የጨላ ከረጢቴን ይዤ ዱቅ እንዳልኩ ጌታችሁን ሳየው አንድ ነገር እንደሆነ ያስታውቅ ነበር፡፡ ጌታችሁም ‹‹ከእናንተ አንዱ አሳልፎ ይተጠኛል›› አለ፡፡ ጌታችሁ ይወደው የነበረው ዮሐንስ የሚባለው ወደ ጌታ ደረት ጠጋ ብሎ ‹‹ጌታ ሆይ ማነው›› አለው፡፡ ሐዋርያትም እጅግ ተጨነቁ "እኔ እሆን እኔ እሆን" እያሉ ታወኩ፡፡
203 views07:02
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 17:48:05
1.4K views14:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 17:47:51 ማዙካ ሸበጡን አውልቃለት፣ ልብሱን ቀናንሳለት አስተካክላው ልታስተኛው ስትል እሱ አስተካክሎ ሳማት፡፡ እሷም ‹‹ተው አይሆንም የነብዩን ትንቢት አስብ ያ የተባለው ልጅ እንዳይፈጠር›› ስትለው መስሚያውን ጥጥ አድርጎ ያለ ውድ በግድ ተገናኛት፡፡ እኔም ተፈልጌ ሳልሆን ሳልፈለግ፣ በትንቢት ወግ ተጸነስኩ፡፡ እስኪ ፈራጆች! እንኳን ጌታዬን የሸጥኩበት መንገድ ቀርቶ የተወለድኩበት መንገድ አይገርማችሁም? አሁን ሰው በእኔ ይፈርዳል? ብቻ አይወለድ የለ ተወለድኩ፡፡

ምን አለ ያኔ እናቴ ሆድ ውኃ ሆኜ በቀረሁ፡፡ ማዙካ በዚህ ዘመን ኖራ ቢሆን በጥቂት ገንዘብ ሜሪ ስቶፕ ታስወጣኝ ነበር፡፡ ድግሞም ትንቢት ስለነበር እሷ በነበረችበት ዘመን ምንም ልታደርግ አልቻለችም፡፡ እኔም ከች አልኩ ተወለድኩ፡፡

ፋዙካም እርግማኑንና ትንቢቱን ሽሽት ምንም የማላውቀውን ሕፃን በሳጥን ውስጥ ዱቅ አድረጎ በባህር ላይ ጣለኝ፡፡ ያልታደለ ግን ለነፍስ ያለ ያስቆሮቱ ሰው አግኝቶኝ አሳደገኝ፤ በነገራችን ላይ የአስቆሮቱ ይሁዳ የተባልኩት ከባህር ላይ አንስቶኝ ባሳደገኝ ሰው ስም እንደሆነ ቲንክ አደረጋችሁ? ኦኬ! እኔም ኃይለኛ ጦረኛ ሆንኝ፡፡ ማን አባቱ ከፊቴ ይቆማል፡፡

በል ያለኝን በካልቾ፣ የጠገበውን በእንጭብጭቢት በስግሪት መታው ነበር፡፡ /አዳሜ የእንጭብጭቢት እና የስግሪት አመታት እዛው ሲኦል ስንገናኝ አሳይሻለሁ/

እባካችሁ ደከመኝ! የሲኦሉም አሳት አቃጠለኝ! ለዛሬ እዚህ ላይ ይብቃ ነገ ሁሉንም ጥቁር ታሪኬን አጫውታቹኃለሁ፡፡ ሰላም ዋሉ እደሩ ልላችሁ ብዬ እኔ ሰላም ያለበት ቦታ ስላልሆንኩ እንደፈለጋችሁ ሆናችሁ ዋሉ እደሩ፡፡

ይቀጥላል …….

ይሁዳ ነኝ ከሲኦል!

ሚያዝያ 6-8-15 ዓ.ም
አዲስ አበባ
1.6K views14:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 17:47:51 #ስንት_ይሁዳ_እያለላችሁ_እኔን_ለምን_በየዓመቱ_ትወግራላችሁ?

/በምናብ የሳልኩት፣ የይሁዳ የሲኦል ብሶት/

የዛሬ አምስት ዓመት የተጻፈ!

የአራዳ ቋንቋ የተጠቀምኩት አራዳ ልሁን ያለውን ይሁዳን እያሰብኩት ነው። ስለ ቋንቋው ይቅርታ! እንድትማሩበት ነው።

ከመፍረዳችሁ በፊት በደንብ አንብቡት እራሳችሁን እዩበት!

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ይሁዳ ነኝ! እነሆ ጌታችሁ ከተሰቀለ ይቅርታ አሳልፌ ሰጥቼው፣ በማይረባ በሠላሳ ብር ሽጬው ተሰቅሎ ከሞተ ሁለት ሺ ምናምን ዓመት አለፈው፡፡ ከሲኦል እሳታማው ሰላምታዬ እኔ ካለሁበት ለመምጣት ተፍ ተፍ ለምትሉት ያልከበረ ሰላመ ቢስ ሰላምታዬ በየጭፈራ ቤቱ በዝሙት ለሚንገላቱ፤ በየጫትና ሐሺሽ ቤቱ ለሚጀዝቡ፤ በትዳርና በእጮኛቸው ላይ ለሚቀስጡ፣ እየዘሞቱ ለሚያላግጡ፤ ዛሬም እንደ እኔ ጌታቸውን በክህደት፣ በገንዘብ ወዘተ ለሚለውጡ ይድረሳችሁ ብያለሁ፡፡

አዳሜ ብልጣ ብልጥ እንደ እኔ በአቋራጭ ገነት ገባለሁ ብለሽ ያሰብሽ ሁላ ሳታስቢው እኔ ያለሁበት ሲኦል ከች ትያለሽ፡፡ ይቅርታ በሲኦል አፌ ስማቸውን መጥራት ስለከበደኝ ነው። እነዛ ጓደኞቼ ሐዋርያት ጌታቸውንና ጽድቁን ሲፈል፤ እኔ ሆዬ ጨላዋ ላይ ሳፈጥ ይኸው በሳጥናኤል ስደፈጠጥ እኖራለሁ፡፡ የሚገርማችሁ ሐዋርያት የጌታቸውን ወንጌል ለመሸከም ሲጥሩ እኔ ደግሞ ሙዳየ ምጽዋትዋን ብቻ ስሸከም ይኸው እነሱ በገነት እኔ በሲኦል ገፈት እኖራለሁ፡፡

እየውላችሁ ስንት ሺ ዓመታት በሲኦል ሆኜ እያንዳንድሽን ስታዘብ ከርሜ ነበር፡፡ ዛሬ ግን ትዝብቴን ልተንፍሰው ብዬ ነው፡፡ ‹‹የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም›› አይደል የምትሉት፡፡ መቼም ካለሁበት ስቃይ ያ ገሃነመ እሳት እስኪከፈት የበለጠ አይመጣ፡፡

ዛሬ በሲኦል ሆኜ ፍርፍር ብዬ ስስቅ ነው የዋልኩት፡፡ ነገርዬው ምን መሰላችሁ! እናንተው ‹‹የእምዬን ወዳብዬ አይደል የምትሉት፡፡ የጌታችሁን መከራ ለማሰብ ያንን የመሰለ ሥርዓት ስታከናውኑ ውላችሁ ማምሻውን ‹‹ይሁዳ ወልዱ እምውሉደ ውሉዱ ይደምሰስ›› እያለችሁ ስንት ይሁዳን ስራችሁ አስቀምጣችሁ በስሜ ስትደበድቡኝ ስትረግሙኝ ነው ያሳቀኝ፡፡

ጋይስ እኔ አንዴ ጌታዬን ሽጬ፣ በሲኦል ተቀምጬ፣ የዛ የሲኦል አበጋዝ መጫወቻ ሆኛለሁ፡፡ ግን ስንቶች አሉ በቤተ ክርስትያን አገልጋይ ነን እያሉ ጌታቸውን በስውር ሽጠው የሚኖሩ፡፡ ስንት አሉ እኔን በመቋሚያ እየደበደቡ በጀርባ እየጠነቆሉ፣ ሙዳየ ምጽዋቱን እየገለበጡ፣ የድሆች ኪስ እየመጠመጡ እሚኖሩ፡፡ ስንት ሴቶች ወንዶች አሉ ክብራቸውን በገንዘብ እየሸጡ ጌታቸውን የሚያስቆጡ፡፡

ስንት አሉ ቅድስናቸውን እያረከሱ፣ በኃጢአት ባህር የሚንከላወሱ፡፡ ኸረ የናንተን ጉድ ዘርዝሬ አልጨርሰውም፡፡ ምንኩስናሽን ያፈረሽ፣ ክህነትሽ የጣልሽ ንስሐ ካልገባሽ በሲኦል የስቃይ ስፖንሰር የምሆናችሁ እኔ ነኝ፡፡ አዳሜ እኔ ወዳለሁበት ስትመጪ የኃጢአት ሒሳብሽን እንደ እኔ በስቃይ በመከራ ታወራርጃለሽ፡፡

ምን እንደምመኝ ታውቃላችሁ! ጌታችሁ እድሉን ቢሰጠኝ እኔን ‹‹ይሁዳና ዘር ዘሮቹ ይጥፉ›› የሚሉትን ነጭ ለባሽ ሁላ በያዙት መቋምያ እግር ከወርች እያልኩ ነርታቸው ነበር፡፡ ደግሞም ንስሐ ሳይገቡ በዓመት አንዴ ለስግደት የሚመጡትን፤ በሥራ እንደ እኔ እንደ ይሁዳ፤ በአለባበስ ግን ጸአዳ የመሰሉትን በመቋምያ እየሸከሸኩ ልክ አገባቸው ነበር፡፡ ምን ዋጋ አለው ሰውን የሚቀይረው ዱላ ሳይሆን ወንጌል በመሆኑ ነው፡፡

እንደው ግን ‹‹ይሁዳና ዘር ዘሮቹ ይጥፉ›› እያላችሁ ቤተ ክርትያን ውስጥ ያላችሁ በመቋሚያ፤ ውጭ ያላችሁ ደግሞ በድንጋይ ስትወግሩኝ ስትረግሙኝ ትንሽ ሼም አይዛችሁም፡፡ ፈጣሪያችሁ ፊት የማያቆም ሥራ ይዛችሁ፣ እንደ ድንጋይ የከበደ ኃጢአት ተሸክማችሁ፣ በየዓመቱ ስትወግሩኝ ስትደበድቡኝ ግርም ይለኛል፡፡ መቼም ጌታ ለእኔ የሰጠኝን ያልተጠቀምኩበትን የንስሐ እድል ለናንተም ስለማይነሳችሁ ነው እንደ ፈለጋችሁ የምትሆኑት፡፡

እስኪ አንዳንድ አዛኝ አንጓቾች፣ ሌሎቹም አጉል ፈራጆች ሁሌ ‹‹ይሁዳ እንዴት በሰላሳ ብር ጌታውን ይሸጣል? እንዴት የንስሐ እድሉን ያበላሻል? እንዴት እራሱን ያጠፋል? እንዴት የሐዋርያነት እድሉን ያበላሻል?›› ለምትሉ ገብስ ገብሱን እነግራቹኃለሁ፡፡

በመጀመርያ ‹‹ይሁዳ እንዴት ጌታውን በሰላሳ ብር ይሸጣል?›› ለምትሉ ስለ እውነት ከሆነ እኔ ጌታዬን መሸጥ አልፈልግም ነበር፡፡ ግን ምን ላድርግ ትንቢቱ ቀድሞ ለእኔ ተነገረ በእኔም ላይ ወደቀ፡፡ ቲንክ እያረጋችሁ ነው ወይስ እያሽሟጠጣችሁ? ኦኬ እኔ ጌታዬን ወድጄ ሳይሆን በትንቢት ተገድጄ እንደሸጥኩ ለእያንዳንድሽ መረጃ አቀርባለሁ፡፡ መቼም ዘመናችሁ የመረጃጃ ሳይሆን የመረጃ እንደሆነ ሲኦል ሆኜ መረጃ ይደርሰኛል፡፡

እስኪ ጌታዬን እንዴት እንደሸጥኩት ከመንገሬ በፊት ከማዙካ የሰማሁትን ልንገራችሁ፡፡ እኔ አስቀድሞ ‹‹አባቱን ይሰልባል፣ እናቱን ያገባል፣ ጌታውን ይሸጣል›› የሚል ትንቢት ነበረኝ፡፡ ታድያ ምን ሆነላችሁ! ያ መናጢ አባቴ ስሙን ሰይጣን ይጥራውና አንድ ዕንባቆም የተባለ ነብይና መምህር ነበር፡፡ አንድ ቀን ዕንባቆም የተባለው ሰው ሊያስተምር ሲሄድ በሚያልፍበት መንገድ ላይ ፋዙካ ድንጋይ ላይ ዱቅ ብሎላቹኃል፡፡

በአገራችን መምህር ክቡር ስለሆነ የፋዙካ ጀለሶች ነብዩ ዕንባቆምን ሲያዩት አክበረውት ተነሱለት፡፡ ፋዙካ በንቀት ይሁን በኩራት እግሩን አንፈራግጦ ተቀምጦ ነበር፡፡ ነብዩ የፋዙካ ጀለሶችን መርቆ፣ ፋዙካን ንቆ ላሽ አለ፡፡ ነብዩ አስተምሮ ማታ ላይ ሲመለስ አሁንም ፋዙካ ያችው ድንጋይ ላይ ዱቅ ብሏል፡፡

ነብዩንም ሲያየው ባላየ ብሎ መንጬ ሊል ብሎ በገገመኛ እዛው ዱቅ አለ፡፡ ነብዩም ‹‹ከዚህ ሰው የሚወለደው አባቱን ይሰልባል፤ እናቱን ያገባል፤ ጌታውን ይሸጣል›› ብሎ ትንቢት ተናገረበት፡፡ ፋዙካም በነብዩ ትንቢት ድንግጥ ሳይል ነብዩንም ይቅርታ ሳይጠይቅ እዛው ድንጋይ ላይ ዱቅ እንዳለ ቀረ፡፡

ፋዙካም ሲመሽ ወደ ማዙካ ጋር ሄደ፡፡ ማዙካም የፋዙካ ፊት አሮ፣ ያ ነጭ ፊቱ እንደ ከሰል ጠቁሮ/ይቅርታ ለካ ከሰል የለም ሲኦል/ ብቻ ምን ልበላቹ ግራ ተጋብቶ ስታየው ‹‹ምንሆንክ? ዛሬ ምን አገኘህ?›› አለችው፡፡

እሱም ‹‹ምን… ባክሽ አንድ ነብይ የሚሉት ሰው በመንገድ ሲሄድ እኔ ድንጋይ ላይ ተቀምጬ ለምን አልተነሳህልኝም፤ ለምን አላከበርከኝም ብሎ ተናገረኝ›› አለ፡፡ ማዙካም ተደናግጣ ዓይኗን አፍጥጣ ‹‹ምን አለህ›› አለችው›› ፋዚካ ነብዩ የተናገረውን ነገራት፡፡

እሷም ‹‹እንዴት እንደዚህ ታደርጋለህ? በእኔስ ላይ ይህንን እርግማን ታመጣለህ›› ብላ አለቀሰች፡፡ ፋዙካ ዓይኑን በጨው የታጠበ ደንታ ቢስ ነበርና እሷ ስታለቅስ ምንም አልመሰለውም፡፡ ምን ቢላት ጥሩ ነው ‹‹በቃ አይዞሽ የነብዩ ትንቢት እንዳይፈጸም እኛም ያችን ነገር አንፈጽምም›› አላት፡፡ እሷም ለጊዜው ተረጋጋች፡፡ ዝም ብላችሁ እዩልኝ በእነዚህ ነገሮች ውስጥ ሁሉ እኔ የለሁበትም፡፡

አንድ ቀን ፋዙካ ከጀለሶቹ ጋር ሆኖ የግብጦ አረቄ/ይቅርታ በሐበሽኛ ለማስረዳት ስል ነው የግብጦ አረቄ ያልኩት/ ወይን ጠጁን ልፎ ልፎ ሰክሮ ተንጀፍጅፎ ጀለሶቹ ተሸክመውት ቤት ገባ፡፡
1.4K views14:47
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 11:48:17
1.4K views08:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-14 11:48:12 #_የሌንጊኖስ_ጦር_እና_የክርስቶስ_ፍቅር!

#_ጎኑን_በጦር_ቢወጋው_ጌታ_የጠፋውን_ዓይኑን_አበራለት!

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ሼር በማድረግ ለወዳጆ ያዳርሱ

ተወዳጆች ሆይ የሞተ የገደለ ጀግና አይባልም፡፡ ሌንጊኖስ የሞተ ለመግደል የጨከነ ሰው ነበር፡፡ ጌታችን በራሱ ፍቃድ በቀራኒዮ አደባባይ መከራን ሲቀበል አይሁድና ሕዝቡ እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ፣ እንደ አንድ ልብ መካሪ በመሆን ብዙ ግፍ አድርሰውበታል፡፡ በተለይ እንደ ተራ ሰው በጥፊና በኩርኩም በመምታት፤ ጸያፍ ምራቃቸውን ፊቱ ላይ በመትፋት፤ ከመሳደብ በዱላ እስከ መደብደብ፤ ከግርፋት እከከ ሞት አድርሰውታል።

ጌታም በራሱ ፍቃድ ነፍሱን ከሥጋው ለይቶ፣ የከበረውን ሥጋ በመስቀል ላይ ትቶ ባለበት ሰዓት ሌንጊኖስ በቀራንዮ አልነበረም። ሌንጊኖስ ከሮማ ወታደሮች አንዱ የነበረ ሲሆን በተለይ በባሕርይው ከሰው ጋር በነገር መቀላቀል አይወድም ነበር። በዚህ ምክንያት በጌታ ሞት አልገባም አልተባበርም በማለት በዱር ተደብቆ ዋለ። ማምሻውን ስለ ጌታ ሁኔታ ሰው ሲጠይቅ "እሱማ ሞተ" አሉት።

አይሁድና ሮማውያን በሞቱ ያልገባውን/ያልተባበረውን/ እንደ ንጉሥ ጠላት አድርገው ያዩት ስለነበር ከእነሱ ላለመውጣት ፈልጎ በፈረሱ ወደ ቀራንዮ ተራራ ገሰግሶ ወጥቶ የሮማ ወታደሮች የሁለቱን ወንበዴዎች ጭኖቻቸውን ሲሰብሩ አይቶ እሱም ‹‹ከሞተ አልጎዳም ስለዚህ እኔስ ለምን ይቅርብኝ›› በማለት ጦሩን ነድሎ፣ የጌታን ቀኝ ጎኑን በጦር ጎልግሎ ወጋው።

ሌንጊኖስ አስቀድሞ አንድ ዓይና/ዓይኑ የጠፋ/ ሰው ስለ ነበር የጌታ የደመ መለኮቱ ፍንጣሪ ጌታ ባወቀ የጠፋ ዓይኑን ቢነካው ብርሃን ተጎናጽፎ፣ ፍቅርና ድኅነትን አትርፎ ተመልሷል፡፡ የሌንጊኖስ አመጣጥ ለጥፋት፣ የጌታ መልስ ግን ቸርነት ነበር፡፡ /ዮሐ 19፥34/

ወዳጄ ሁሌም በእግዚአብሔር መንገድ ለጥፋት፣ ለበደል ብትሰለፍ፣ በክርስቶስ መዳፍ በመታቀፍ ስለምትኖር እርሱ እንደ ሌንጊኖስ ይፈልግኃል፡፡ አንተ ሕጉን ለማፍረስ የእርሱ የሆነውን ለማጥፋት ብትሮጥ እርሱ በፍቅር ወጥመድ፣ በማሳደድ ይይዝኃል፡፡

ዛሬም ብዙ ሌንጊኖሶች አለን፡፡ በጥፋትና በኃጢአት ጎዳና ስንሮጥ ከርመን፣ ጌታ በቸርነቱ ስቦን የራሱ ያደረገን፡፡ ሌንጊኖስ ስለ ጌታ አምላክነት ስላላወቀ፣ ጦሩን በጌታ ላይ ሰበቀ፡፡ ዛሬ ደግሞ እኛ የጌታን አምላክነት አውቀን፣ የጽድቅን ሳይሆን የኃጢአትን ጦር ታጥቀን የተነሳን፣ በኃጢአት የዘመትን አለን፡፡ ሌንጊኖ ባለማወቅ የአይሁድ ተባባሪ ሆኖ ነበር፡፡ ዛሬ ደግሞ እኛ እያወቅን የሰይጣን ተባባሪ ሆነናል፡፡

ዛሬም ጌታ የሞተላቸው ሌንጊኖሶች ጌታን በምንፍቅና በክህደት ጦር እየወጉት ነው፡፡ ተፍጻሜተ ሰማዕት ጴጥሮስ ‹‹ሌሊት ጸሎቴን ጨርሼ በተኛሁ ጊዜ ፊቱ እንደ ፀሐይ የሚያበራና እስከ እግሩ ድረስ ረጅም ልብስ የለበሰ አንድ ወጣት ወደ እኔ ሲገባ አየሁት፡፡ ልብሱም ተቀድዶ፤ የተቀደደውን ልብስ ቁራጭ በእጁ ይዞ ስላየሁት ‹‹ልብስህን ማን ቀደደብህ›› ብዬ በመጮህ ብጠይቀው እርሱም ‹‹ልብሴን የቀደደብኝ አርዮስ ነው›› በማለት ያየውን ተናግሯል፡፡

ወዳጄ የጌታ ልብስ መቀደድ ምሳሌ አርዮስ ጌታችንን ከሦስቱ አካላት በመለየት ‹‹ፈጣሪን ፍጡር ነው›› በማለቱ ነው፡፡ ዛሬም እንደ አርዮስ "ፍጡር ነው፤ አማላጅ ነው" እያሉ የጌታን ልብስ በክህደት በመቅደድ፣ እንደ ሌንጊኖስ የጌታን ጎን በመውጋት የሚኖሩ አሉ፡፡ አይሁድ በቀራኒዮ አደባባይ በጌታ ላይ የፈጽሙትን ግፍ እና ክደት ዛሬም የሚደግሙት አሉ፡፡

እንደ ሌንጊኖስ የጌታን ጎን ዳግም የሚወጉትን፣ በክህደት ልባቸውን ያደነደኑትን ሐዋርያው ‹‹በኋላም የካዱትን እንደገና ለንስሐ እነርሱን ማደስ የማይቻል ነው፡፡ ለራሳቸው የእግዚአብሔርን ልጅ ይሰቅሉታልና ያዋርዱትማልና›› በማለት ይገልጻቸዋል /ዕብ 6፥6/

ወዳጄ በሌንጊስ ጥፋት ውስጥ የክርስቶስ ማዳን እንዳለ ሁሉ ባንተም ክፋት ውስጥ የጌታ ማዳን ስላለ ወደ ክርስቶስ ለመጠጋት እንደ ሌንጊኖስ የክፋት ጦር ሳይሆን የጽድቅን ጦር ስበቅ ያኔ ጌታ የጠፋብህን መንፈሳዊ ሕይወት ያበራልሃል።

ሌንጊኖስ የክርስቶስን ቸርነትና ማዳን ካየ በኋላ በመጨረሻ ምን ሆነ? ምን አደረገ? ካልከኝ ሌንጊኖስ ዓይኑ ከበራለት በኃላ "የጠላትን ዓይን ያጠፉታል አንጂ እንዴት ያበሩታል" በማለት በመገረም በዕለተ አርብ የተደረጉትን ተአምራቶች መመርመር ጀመረ።

የጌታን በሦስተኛው ቀን ከሙታን መነሳት ሲሰማ እውነቱን እንዲያስረዳው ወደ ጌታችን አጥብቆ ጸለየ። ጌታም ቅዱስ ጴጥሮስን ልኮለት ወንጌልን በሚገባ ተምሮ በስሙ መስበክ ጀመረ። በኢየሩሳሌምም የአይሁድና የሮማውያን ተቃውሞ ስላስቸገረው ወደ ታናሽዋ እስያ ወደ ቀጰዶቅያ ሄዶ ወንጌልን በማስተማሩ ብዙዎችን በክርስቶስ ወደ ማመን መልሷቸዋል።

በመጨረሻም ወንጌልን በማስተማሩ ተከሶ በቀጰዶቅያ ከተማ አንገቱን በሰይፍ ተቆርጦ በሰማዕትነት ሐምሌ 23 ቀን አርፏል። በሌንጊኖስ ጦር ውስጥ የክርስቶስን ፍቅር አየህ?

ወዳጆቼ ጌታችን በደሙ የመሠረታትን ቅድስት ቤተ-ክርስትያናችንን በብሔር ሽፋን፣ በፖለቲካ ተንኮል እንዳትከፋፈል በርትተን እንጸልይ፡፡ ዛሬ ቁጭ ብለን የሰቀልነውን ነገ ቆመን ማውረድ እንችልምና በአንድነት መንፈስ እንጽና፡፡

"ሌሊቱ አልፎአል፣ ቀኑም ቀርቦአል እንግዲህ የጨለማውን ሥራ አውጥተን የብርሃንን ጋሻ ጦር እንልበስ" ሮሜ 13÷12

‹‹ከክርስቶስ ጋር እንዴት እንኑር?›› ከሚለው መጽሐፌ የተወሰደ፡፡

ሚያዝያ/ 6/15 ዓ.ም
አዲስ አበባ
1.5K views08:48
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-13 20:42:13
1.3K views17:42
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-04-09 22:11:48

972 views19:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ