Get Mystery Box with random crypto!

ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

የቴሌግራም ቻናል አርማ memehirhenok — ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
የቴሌግራም ቻናል አርማ memehirhenok — ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
የሰርጥ አድራሻ: @memehirhenok
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 12.40K

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች 6

2023-05-09 07:52:03 #_ታሪክ_ድንግል_ማርያም_!

#_የልደቷ_ነገር!

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ሼር በማድረግ ለወዳጆ አዳርሱ!

የወለላይቱ እመቤት ልጆች የእመቤታችን ታሪክ አበው ቅዱሳን ናቸው፡፡ ይህንን ዳዊት “መሠረቶቿ ተቀደሱ ተራሮች ናቸው“ እንዳ በተለያያ ቅዱሳን መሠረት ስትወርድ እንደመጣች የቤተክርስትያን ሊቃውንት ይናገራሉ፡፡ መዝ 86፥1

#_ጥንተ_ታሪክ፡-በኢየሩሳሌም አካባቢ በቅዱስ ጋብቻ ተወስነው ለፈጣሪ ተገዝተው የሚኖሩ ጴጥርቃ እና ቴክታ የሚባሉ ቅዱሳን ሰዎች ነበሩ፡፡ እነዚህ ሰዎች በትዳር ሕይወታቸው ልጅ የሌላቸው መካኖች ነበሩ፡፡ በተለይ በዘመናቸው ያፈሩትን የተትረፈረፈ ምድራዊ ሀብት የሚወርስላቸው ልጅ ስለሌላቸው ያዝኑ ይተክዙ ነበር፡፡

አንድ ቀን ጴጥርቃና ቴክታ ስለ ሀብታቸው ብዛት ከተወያዩ በኋላ ጴጥርቃ በተስፋ መቁረጥ ስሜት “እህቴ ይህ ሁሉ የሰበሰብነውን ሀብታችንን ምን እናደርገዋለን? አንቺ መካን ነሽ የሚወርሰን ልጅ የለንም እኔ ደግሞ ከአንቺ ሌላ ሴት አላውቅም“ አላት፡፡

የተባረከች ቴክታም “ጌታዬ ሆይ የእስራኤል አምላክ ለእኔ ልጅ ቢነሳኝ አንተም እንደ እኔ ልጅ አልባ ሆነህ ትቀራለህን? ከሌላ ሴት ውለድ እንጂ“ ብላ ብታሰናብተው ጴጥርቃም “እንዲህ ያለ ነገር እንኳን ላደርገው በልቦናዬ እንደማላስበው የእስራኤል አምላክ ያውቃል“ አላት፡፡

ከዚህ በኋላ ብርክት ቴክታ ለክቡር ጴጥርቃ እንዲህ አለችው “እግዚአብሔር የሚያደርገውን የሚያውቅ የለም፡ ትላንት ማታ በሕልሜ ነጭ ጥጃ ከማህጸኔ ስትወጣ ያቺም ነጭ ጥጃ ሌላ ነጭ ጥጃ ስትወልድ እስከ ሠባት /7/ ትውልድ ድረስ ሲዋለዱ ሰባተኛዋ ጨረቃን ስትወልድ ጨረቃም ፀሐይን ስትወልድ አየሁ“አለችው፡፡

ሁለቱም በራዕዩ ተደንቀው እግዚአብሔርን አመስግነው ወደ ሕልም ፈቺ ዘንድ ሄደው ያዩትን ነገሩት፡፡ ሕልም ፈቺውን በነገራቸውን ከሰማ በኋላ በመደነቅ እእዲህ አላቸው “አግዚአብሔር በምህረቱ በቸርነቱ አይቷችኋል የሕልማችሁም ፍቺ እንዲህ ነው ፦ ነጭ ጥጃ መውለዳችሁ ጥጃዋም እስከ ሠባት ትውልድ ስትዋለድ ማየታችሁ ሴት ልጅ ትወልዳላችሁ፡፡

ሴቶቹም እስከ ሠባት ትውልድ ይዋለዳሉ። ሰባተኛይቱ ጨረቃን መውለዷ ከሰው የበለጠች በጸጋየከበረች ከመላእክት የተለየች ደግ ፍጥረት ትወልዳላችሁ፡፡ የፀሐይ ነገር ግን አልታወቀኝም አልተገለጠልኝም“ አላቸው፡፡

በዚያም ወራት ክብርት ቴክታ ጸነሰች፡፡ ሴት ልጅም ወለደች፣ ስሟንም ሄሜን ብለው አወጡላት፣ ሄሜንም ዴርዴን ወለደች፣ ዴርዴም ቶናን ወለደች፣ ቶናም ሲካርን ወለደች፣ ሲካርም ሴትናን ወለደች፣ ሴትናም ሄርሜላን ወለደች፣ ሄርሜላም ማጣትን አግብታ ከሴቶች ተመርጣ የክርስቶስ አያት የሆነችውን ቅድስት ሐናን መስከረም 7 /ሰባት/ ቀን ወለደች፡፡

ቅድስት ሐናም በመንፈሳዊ ሥርዓት አድጋ ለአካለ መጠን ስትደርስ ከቤተ መንግስት ለተወለደው ክቡር ፃዲቅ ለሆነው ለቅዱስ ኢያቄም ዳሯት፡፡

እመቤታችንም እንደ ነጭ ዕንቁ ከቀድሞ ጀምሮ በአዳም ባሕርይ ስታበራ ኖራለች፡፡ ከአዳም ቀጥሎ ለልጁ ለሴት የተሰጠች እርሷ ናት፣ ከሴትም ለሄኖክ የተሰጠች እርሷ ናት። ጥበበኛው ሰሎሞን ከሠባቱ ሰማያት ተልካ ጥበብ በፃድቃን ሰዎች ውስጥ ትመላለሳለች እንዳለ እመቤታችንም ከሄኖክ እስከ ደገኛው አብርሃም፣ ከአብርሃም እስከ ንጉሱ ዳዊት፣ ከዳዊት እስከ ቅድስት ሐና በቅድስና ወርዳለች፡፡

የብርሃኗ ነፀብራቅም ወርዶ በማህጸነ ሃና እስከ አደረ ድረስ አዳም ከተፈጠረ ጀምሮ በሴቶች ማህጸን እንደ እርሷ ያለ የነጸብራቀ ብርሃን አልታየም፡፡ ሴቶች የተባሉት ከሔዋን ጀምሮ እስከ ብፅዕት ሐና፣ ከብፅዕት ሐና እስከ ዕለተ ምፅአት ያሉት ናቸው፡፡

ቅድስት ሐና ባሏ ኢያቄም ካገባት ጊዜ ጀምሮ ወንድ ወይም ሴት ልጅ ባለመውለዷ የመረረ ለቅሶ ስታለውስ ትኖር ነበር፡፡ በዚህም እስራኤላውያን ናቋት እንዲህም አሏት፡፡ “አንቺ በእስራኤል መካከል ለኢያቄም ቤት የሚቆም ስሙን የሚያስጠራ ዘርዕ ወይም ልጅ የሌለሽ መካን በመሆንሽ ከመካከላችን ውጪ፡፡

የኢያቄምን ቤት አጥፍተሻል ከሃገራችን ሂጂ፡፡ ከእኛም ጋር መኖር አትችይም፡፡ በሕጋችን መሠረት መስዋዕት ወይም ቁርባን በምናሳርግበት ጊዜ ከእኛ ጋር አንድነት የለሽም፡፡“ በኦሪት ሕግ ልጅ የሌላቸው ሰዎች ከመሠዊያው ቦታ ያባርሯቸው ወደ ውጪም ያስወጧቸው ነበር፡፡

ከዚህም በኋላ ቅድስት ሐና በእግዚአብሔር ፊት ጸለየች፡፡ እንዲህም አለች “ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ እስከ ዓለም መጨረሻ የምትኖር፤ ከዓለም በፊት የነበርክ ዓለምን አሳልፈህ የምትኖር የአባቶቻችን የአብርሃም፣ የይስሃቅ፣ የያዕቆብ አምላክ፣ የእስራኤል ጌታ ፈጣሪዬ እግዚአብሔር ሆይ ልመናዬንና ጸሎቴን ስማ ሁሉ ይቻልሃል የሚሳንህ የለም፡፡

አንተ ትገድላለህ ታድናለህ፣ አንተ ትዘጋለህ አንተ ትከፍታለህና ማህጸኔን ክፈትልኝ። አንተ ባዘዝከው መሠረት ያማረ የተወደደ መስዋዕት እጅ መንሻ አድርጌ እሰጥህ ዘንድ አንተን ደስ የሚያሰኝ ፍሬ ስጠን። ጸሎቴን ሰምተህ ልመናዬን ተቀብለህ የለመንኩህን ካልፈጸምክልኝ ያማረ የተቀደሰ ዘር ካልሰጠኸኝ አባቶቼ እናቶቼ ለዘለዓለም ወደሚኖሩበት የሞት ሃገር እኔንም ውሰደኝ።

እኔ አኗኗሬ የከፋ የልብ ሐዘንተኛ ስሆን በምድር ላይ መኖርን ለምን እመኛለሁ፡፡ የእስራኤል ሴቶች ልጆቻቸውን በደስታ ተሸክመው እኔ ላይ ይዘባበታሉ። ልጅ ባለመውለዴም ይስቁብኛል። እኔንም ባዩ ጊዜ እራሳቸውን ይነቀንቃሉና፡፡ “አቤቱ ጌታዬ ፈጣሪዬ ሆይ የተናቅሁኝ የተጣልኩኝ የእኔን የገረድህን ስቃይ እይ ተመልከት“ ብላ በእስራኤል ሴቶች መካከል ሃና ልመና አበዛች፡፡

ባሏ ኢያቄምም አይኖቹ በሃዘን ወደምድር ሲመለከቱ ሕሊናውን ግን ወደ ሰማይ አቅንቶ “ሳይነግሩህ ሁሉን የምታውቅ የእስራኤል አምላክ ጌታዬ እግዚአብሔር ሆይ ለምን ለጠላቶቼ መሳለቂያ መዘባበቻ አደረከኝ? አለምንም ካለመኖር ወደመኖር አምጥተህ የፈጠርክ አንተ ነህና። ጸሐይና ጨረቃን የምታፈራርቅ አንተ ነህና ልመናዬን ስማኝ፡፡

የልቤን ጭንቀት አቅልልኝ የጥበብና የአዕምሮ መንፈስ ያለው ወደ አንተ መስዋት አድርጌ በማቀርበው ልጅ ስጠኝ፡፡ በእስራኤል ሁሉ ዘንድ የተናቅሁ አታድርገኝ አንተ ብዙውን ትንሽ ትንሹንም ብዙ ማድረግ ትችላለህና“ አለ፡፡

ከዚህ በኋላ ጸሎታቸውንም በጨረሱ ጊዜ እግዚአብሔር የሃናን ሀዘን የኢያቄምን ጭንቀት አየ፡፡ ሃናም ሌሊት በራዕይ ከሰባቱ ሰማያት ነጭ ወፍ ወርዳ በማህጸኗ ስታድር አየች፡፡ ኪሩቤል እንደ ሰው እጅ በምስጋና ይጋርዳት ነበር፡፡ በእጁ የሕይወት ገመድ ተይዟል፡፡ ይህም የሕይወት መንፈስ በነጭ ወፍ አምሳል በሃና እራስ ላይ ተቀመጠ፡፡ ባህሪዋ ከኢያቄም አብራክ ወጥቶ በሃና ማህጸን ባደረ ጊዜ ሃና በማህጸኗ ተቀበለቻት፡፡

ይህም ባሕርይ የእመቤታችን ሥጋ ነው፡፡ ነጭ ባሕርም የተባለው ንጽህናዋ ነው። ነጭ ወፍም የተባለው ንጹህ ነፍሷ ነው፡፡ ዓለም ሳይፈጠር በፊት በሕሊና አምላክ ታስባ ትኖር ነበርና። በአባቱ ቀኝ ነጭ ወፍም ነጭ ባሕርይም በእጁ ነበረችና ሳይነጣጠሉ ሁለቱ ባሕርያት በሐና ማህጸን አደረ፡፡

ይህ ነገር ከዚህ በፊት በሐና ማህጸን ያልተለመደ ስለሆነ የሐና ማህጸን ታወከ፡፡ ኢያቄምም በራዕዩ በሐና እጅ የሚመስለው የሌለ የሚጣፍጥ መልካም ፍሬ ተይዞ አየ፡፡ ከሴቶች ሁሉ እንደ እመቤታችን ንጽህት ሆኖ የተፈየረ የለም፡፡
2.4K views04:52
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-08 23:38:53

2.1K views20:38
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 22:30:57

2.4K views19:30
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-07 07:07:27

2.6K views04:07
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-06 09:34:44

2.8K views06:34
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 21:43:41
3.9K views18:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 21:43:30 #_ታላቅ_የንግስ_በዓል_ጥሪ_በወይን_አምባ_ማርያም!

#_ሚያዝያ_30_ሰኞ_ዕለት

የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ በዓለ እረፍት እና የወይን አምባ ማርያም ቅዳሴ ቤት!

ሼር በማድረግ ላልሰሙት አሰሙ አዳርሱ!

የወለላይቱ እመቤት ልጆች ተአምረኛው፣ ፈዋሹ፣ ጌታን ያጠመቀው መጥምቀ መለኮት የተባለው የቅዱስ ዮሐንስ ታቦቱ በወይን አምባ ማርያም አለ። ብዙዎች በተአምረኛ ጸበሉና እምነቱ እየዳኑ ነው።

ሚያዝያ 15 ቀን መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የከበረችው አንገቱ 15 ዓመት ዓለምን ዞራ ወንጌልን አስተምራ በክብር ያረፈችበት ዕለት ነው። እንዲሁም የተአምረኛዋ የወይን አምባ ማርያም ቅዳሴ ቤቷ ነው። የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ የከበረችው አንገቱ ያረፈችበትን ዕለት ለበዓሉ እንዲመች ሚያዝያ 30 ሰኞ በዕለተ ቀኑ ይከበራል።

ሚያዝያ 30 ሰኞ የመጥምቀ መለኮት እና የእመቤታችን ታቦቶች ወጥተው ሕዝቡን ይባርካሉ። ስለዚህ መጥታችሁ ከበዓሉ ረድኤት፣ ከጥምቀቱ ድህነት፣ ከዝክሩ በረከት ተካፈሉ!

#_የትራንስፖርት_መምጫው ፦

ከየትኛውም አቅጣጫ የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርዳችሁ፣ ሠፈራ ብላችሁ በባጃጃ ተሳፍራችሁ፣ ድልድዩን እንደተሻገራችሁ አስፓልቱ ጫፍ ላይ ቤተ ክርስትያኗ ትገኛለች።

ከመገናኛ በቀጥታ ጎሮ ብለው ተሳፍረው፣ ጎሮ አደባባይ ወርደው፣ ከዚያ ባጃጅ ተሳፍረው፣ ሠፈራ ድልድይ ጫፍ ላይ ስትወርዱ ትገኛለች፡፡

ከመገናኛ ቀጥታ ወይን አምባ ማርያም ብላችሁ መሳፈር ትችላላችሁ።

ከሲ አምሲ፣ ከአያት፣ ከሰሚት የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርደው፣ ባጃጅ ተሳፍረው ሠፈራ ድልድይ ጫፍ ወርደው ትገኛለች፡፡

ከቃሊቲ፣ ከቱሉ፣ ዲምቱ፣ ከኮዬ ፈጩ የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርደው ከዚያ በባጃጅ ተሳፍረው ሠፈራ ድልድይ ወርደው ጫፍ ላይ ትገኛለች፡፡

ማያዝያ 25-8-15 ዓ.ም

ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

አዲስ አበባ
3.6K views18:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-03 09:22:18

3.2K views06:22
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 20:24:43
3.2K views17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-05-02 20:24:29 #ክፉኛ_የዝሙት_አጋንንትና_የዝሙት_ፈተና_በአረጋዊ_መንፈሳዊ_

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም!

ሼር በማድረግ ለወዳጆ አዳርሱ!

ተወዳጆች ሆይ በመጻሕፍተ መነኰሳት በአረጋዊ መንፈሳዊ ላይ ስለ ዝሙት አጋንንት ክፉኛ ፈተና ተጽፏል። ለአንባቢ እንዲመች ይዘቱን ሳይለቅ አቀራረቡን ብቻ ጥቂት በመቀየር፣ ትንሽ በመጨመር አቅርቤዋለሁ።

ከአጋንንት ሁሉ ይልቅ የዚህ የሰይጣን ዝሙት ፈተናው ቡዙ ነው። የዝሙት አጋንንት ሕዋሳታችንን የሚያዝልበት ጊዜ አለ። ልቦናችንን የሚለውጥበት ጊዜ አለ። ሕሊናችንን የሚሰውርበት ጊዜ አለ። ሰውነታችንን ማዘዝ የማንችልበት ጊዜ አለ። ከጸጋ ስጦታ ለይቶ ኅሊናችንን ይለውጣል። ተኝተን ሳለን በዝሙት የሚዋጋን ጊዜ አለ።

የዝሙት አጋንንትን አመጣጡን እንወቅበት። በምን እናውቃለን? ካልን የዝሙት እሳቱ በፊታችን ላይ እንደ እሳት ብልጭ ይልብናል። የዝሙት አጋንንት ሲመጣ ድንግጥ ድንግጥ እንላለን። የዝሙት አጋንንት ሲፈትነን ጸሎታችን፣ ስግደታችን ይከብደናል። እንዳንጸልይ እንዳንሰግድ ከባድ አድርጎ ያሳየናል።

የዝሙት አጋንንት ሲፈትነን ጸሎታችንን የአምልኮት ስግደታችንን ትተን ወይም አቋርጠን እንተኛለን። ቆመን ተኝተን ሕዋሳታችንን እንዳብሳለን። እግራችንን እናፋትላለን። ነገር ግን ታግሰን ብንጸልይ የእግዚአብሔር መልአክ ይረዳናል። ብንጸልይ ብንሰግድ ብንተጋ ፈተናው ይቀልልናል ይርቅልናል።

እነዚህ የዝሙት አጋንንት የፈተና ምልክቶች እያሉብን ያለ ጸሎትና ያለ ስግደት መተኛት የለብንም። ያለ ጸሎት ያለ ስግደት ብንተኛ ጠባቂ መልአክ ይርቀናል የዝሙት አጋንንት ቀርቦ ይፈትነናል።

የዝሙት አጋንንት በዓይን ይገባል። በዓይን ሲገባ ወደ ሰውነታችን ገብቶ በመቆጣጠር ሕዋሳችንን በእጅ እንድናሽ ያደርገናል። /ይህ አባባል ግለ ወሲብ እንድንፈጽም ያደርገናል ለማለት ነው/ የዝሙት አጋንንት እንዲህ ሲፈትነን በክርስቶስ ኃይል እናማትብበት።

ወደ ተግባረ ዝሙት እንዳይከተን በርትተን መጸለይ መስገድ አለብን። ይህን ካለደረግን የዝሙት አጋንንት ወደ አባለ ዘር ገብቶ ያለ ርህራሄ በዝሙት ፈተና ያስጨንቀናል በዝሙት ይጥለናል።

የዝሙት አጋንንት ሰዎችን እንደ ጊንጥ ይነድፋሉ። ቆመንም ቢሆን፣ ተቀምጠንም ቢሆን፣ ሥራም በያዝንበት ጊዜም ቢሆን የዝሙት ስሜት ቢያነሳሳብን በሕሊናችን እንጸልይ እንገስጸው።

ከወትሮ ይልቅ አብዝተን ስንበላ ስንጠጣ የዝሙት ፆር ይጸናብናል። አብዝቶ መብላት መጠጣት እና እላፊ መተኛት የዝሙት አጋንንትን ያቀርበዋል። አብዝተን ስንበላ ስንጠጣ ያኔ የዝሙት አጋንንት ሊዋጋን እንደቀረበ እንወቅ። ሰውነታችንን ለዝሙት ካነሳሳ ያኔ የዝሙት አጋንንት እንደሰለጠነብን እንወቅ።

ወዳጆቼ ብዙዎቻችንን ከንስሐ መንገድ ያራቀን፣ ክብራችንን ቅድስናችንን ያስጣለን፣ ከዓለማዊ እስከ መንፈሳዊ፣ ከምዕመን እስከ አባቶች እናቶች፣ በአምልኮት ሕይወት ከጸኑት፣ በቅዱስ ቁርባን እስከ ተወሰኑት ወዘተ የዝሙት አጋንንት እየፈተነን በቀላሉ እየጣለን ነው። በዚህም ቅድስና ከሕይወታችን ርቋል።

ከዝሙት አጋንንት የሸሸ እግዚአብሔርን ይከተላል። ከዝሙት አጋንንት የሸሸ ጸጋና በረከቱን ይዞ ይኖራል። ከዝሙት አጋንንት የሸሸ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን በማዕረግ ያገባል። ከዝሙት አጋንንት የሸሸ ንጽሕናውን ቅድስናውን ይጠብቃል። ከዝሙት አጋንንት የሸሸ ከርኩሰት ይሸሻል። ከዝሙት አጋንንት ሸሽቶ፣ ወደ እግዚአብሔር ተጠግቶ የሚኖር ሰማያዊ ሽልማት ያገኛል። ከዝሙት አጋንንት እና ከዝሙት እንሽሽ። ለዚህም ነው ቅዱስ ጳውሎስ "ከዝሙት ሽሹ" ያለን። /1ኛ ቆሮ 6፥ 18/

እጅግ በጣም የገረመኝ አረጋዊ መንፈሳዊ "የሰይጣናት ተንኮላቸውን እናገር ዘንድ ከምን ተችሎኝ ላልፈጽመው" በማለት ገና ያላወቅናቸው ነገር ግን በወጥመዱ የተያዝንባቸው፣ በሴራው የወደቅንባቸው ተንኮሎቹ እንዳሉ ይነግረናል።

እኛ ግን ስለ ጥንተ ጠላታችን ከገነት ስላስወጣን፣ ከእግዚአብሔር ስለለየን፣ ከዘላለማዊ መንግሥቱ እንድንባረር ስላደረገን ሰይጣን ተንኮሉ ሴራው ውጊያው ሲነገረን ስለ ሰይጣን የተሰበክን መስሎን እንጃጃላለን። ስለ ጠላታችሁ ንቁ እወቁ ሲባሉ ሰይጣን ለምን ተነካ የሚሉ አሉ።

ቅዱስ ጴጥሮስ ግን "ባላጋራችሁ ዲያቢሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያገሳ አንበሳ ይዞራልና" በማለት ውጊያው ቀላል እንዳልሆነና የማንጸልይ፣ የማንሰግድ፣ ቅዱስ ቁርባን የማንቀበል ከሆነ እንደ አንበሳ፣ በሕይወታችን እያገሳ ስንት ነገራችንን እየነሳ ይኖራል። /1ኛ ጴጥ 5፥8/

ወዳጆቼ ዲያቢሎስ "ፈልጎ እንደሚያገሳ" መባሉን ልብ በሉ። እኛ ባንፈልገውም እሱ ፈልጎ ይዋጋናል። የመንፈሳዊ የጦር ዕቃዎችን ማለትም ጸሎት፣ ስግደት ወዘተ የማያነሳ ሰው ላይ እንደ አንበሳ መሆኑን አንርሳ።

ሚያዝያ 24-8-15 ዓ.ም

አዲስ አበባ
3.4K views17:24
ክፈት / አስተያየት ይስጡ