Get Mystery Box with random crypto!

ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

የቴሌግራም ቻናል አርማ memehirhenok — ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
የቴሌግራም ቻናል አርማ memehirhenok — ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም
የሰርጥ አድራሻ: @memehirhenok
ምድቦች: ሃይማኖት
ቋንቋ: አማርኛ
ሀገር: ኢትዮጵያ
ተመዝጋቢዎች: 12.40K

Ratings & Reviews

2.33

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

2

2 stars

0

1 stars

1


የቅርብ ጊዜ መልዕክቶች

2023-07-04 01:51:32

1.3K views22:51
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 08:59:19
1.9K views05:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-03 08:59:11 #_ታላቅ_የንግሥ_በዓል_ጥሪ_በወይን_አምባ_ማርያም!

#ሰኔ_30_አርብ_የመጥምቁ_ዮሐንስ_የልደት_በዓል_ይከበራል!

#_ሰኔ_30_ወይን_አምባ_ማርያም_እንገናኝ!

"በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል" ሉቃ 1፥14

#_ሼር_በማድረግ_ለመጥምቁ_ዮሐንስ_ወዳጆች_አዳርሱ!

የወለላይቱ እመቤት ልጆች አርብ ሰኔ 30 ቀን በወይን አምባ ማርያም የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ ዓመታዊ የልደት በዓል በደማቅ ሁኔታ ይከበራል። በዚህም የተአምረኛው ብዙዎቹን ከጡት፣ ከአጥንት፣ ከማህጸን ካንሰርና ከተለያዩ በሽታዎች እየፈወሰ ያለው የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ ታቦት ወጥቶ ሕዝቡን ይባርካል።

የመጥምቁ ዮሐንስ ታቦቱ ወደ መንበረ ክብሩ ከገባ በኃላ ሰፊ ዝክር አለ። ጌታችን "ዝክርህን የቀመሰ ዘሩን ቆጥሬ እስከ 55 ትውልድ እምርልሃለሁ" ስለላው መጥታችሁ ከበዓሉ ረድኤትን፣ ከዝክሩ ቃል- ኪዳንና በረከትን ተቀበሉ፣ 55 ትውልዳችሁን አስምሩ።

"በመወለዱም ብዙዎች ደስ ይላቸዋል" "ከሴቶች ከተወለዱት መካከል ከመጥምቁ ዮሐንስ የሚበልጥ አልተነሳም" /ማቴ 11፥11/ የተባለለት ቅዱስ ዮሐንስ የተወለደው ሰኔ 30 ስለሆነ መጥተን በዓሉን አክብረን፣ እንደ ቃሉ ደስ ይበለን።

#_የትራንስፖርት_መምጫው ፦

ከየትኛውም አቅጣጫ የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርዳችሁ፣ ሠፈራ ብላችሁ በባጃጃ ተሳፍራችሁ፣ ድልድዩን እንደተሻገራችሁ አስፓልቱ ጫፍ ላይ ቤተ ክርስትያኗ ትገኛለች።

ከመገናኛ ቀጥታ ወይን አምባ ማርያም የሚል ታክሲ አለ ተሳፍራችሁ ቤተ ክርስቲያኗ በር ላይ ያወርዳቹኃል።

ከመገናኛ በቀጥታ ጎሮ ብለው ተሳፍረው፣ ጎሮ አደባባይ ወርደው፣ ከዚያ ባጃጅ ተሳፍረው፣ ሠፈራ ድልድይ ጫፍ ላይ ስትወርዱ ትገኛለች፡፡

ከሲ አምሲ፣ ከአያት፣ ከሰሚት የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርደው፣ ባጃጅ ተሳፍረው ሠፈራ ድልድይ ጫፍ ወርደው ትገኛለች፡፡

ከቃሊቲ፣ ከቱሉ፣ ዲምቱ፣ ከኮዬ ፈጩ የምትመጡ ጎሮ አደባባይ ወርደው ከዚያ በባጃጅ ተሳፍረው ሠፈራ ድልድይ ወርደው ጫፍ ላይ ትገኛለች፡፡

ሰኔ 26/10/15 ዓ.ም
ኒዮርክ አሜሪካ
1.9K views05:59
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-02 06:11:47

2.1K views03:11
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-07-01 04:57:52

2.3K views01:57
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 05:43:40
2.7K views02:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 05:43:33 ወዳጆቼ ለሰው መልካም ማድረግ ለራስ ነው። እናንተ ለሰው መልካም ስታደርጉ መልካሙ እግዚአብሔር ለእናንተ በችግራችሁ በፈተናችሁ ጊዜ መልካም ነገር ያደርግላቹኃል። እናንተ ለሰው ስትቆሙ እግዚአብሔር ለእናንተ ይቆማል። ሰውን ስታግዙ እግዚአብሔር በችግራችሁ ጊዜ ያግዛቹኃል። እናንተ ሰው ስትረዱ በፈተናችሁ ጊዜ የሚራዳ መልአክ ያዝላቹኃል። አበቃሁ!

ሰኔ 22-10-15 ዓ.ም

ኒዮርክ አሜሪካ
2.5K views02:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 05:43:33 #_ሰኔ_22_የቅዱስ_ዑራኤል_እለት_ከሞት_የዳንኩበት_ዕለት_ነው

በቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ተወዳጆች ሆይ ከላይ በርዕሱ የነገርኳችሁ የሞት አፋፍ ታሪክ የተፈጸመው የዛሬ 17 ዓመት በ19 98 ዓ.ም ምህረት ነው።

የዛሬ 20 ዓመት ጻድቃኔ ማርያም እያለሁ በረከት አገኝባቸዋለሁ ብዬ የማስታምማቸው ሁለት ወጣቶች ነበር። የሁለቱም ሕመም ይዘት አንድ አይነት ቢመስልም፣ በሳይንሱ ዓለም ስም ቢሰጠውም በመንፈሳዊው ዓለም ደግሞ የዛ የመናጢ ሥራ ነው።

እነዚህን ሁለት ወጣቶች በክፉ መናፍስት አእምሮአቸው ታስሮ ስለነበር፣ አእምሮአቸው መታሰር ብቻ ሳይሆን፣ በተለይ አንደኛው ሙሉ በሙሉ እራሱን አያውቅም ነበር። ሁለተኛው ሻል ቢልም አልሸሹም ዞር አሉ ነው።

እነዚህን ሁለት ታማሚ ወጣቶችን ያለ ገንዘብ ክፍያ በነጻ ሳስታምም እመቤታችን ታድናቸዋለች ለእኔም ለነፍሴ ይሆኑኛል ብዬ ነበር የማስታምማቸው። በእመቤታችን ፈቃድ እነዚህን ሁለት ወጣቶች ከጻድቃኔ ማርያም ወደ እንጦጦ ማርያም ይዣቸው መጣሁ። በዛም መንፈሳዊ ትግል ጀመርን።

መቼም ማስታመም ሲባል የለመዳችሁትን የሰማችሁትን ማስታመም ሳይሆን እራሳቸውን ስለማያውቁ፣ እንደ ሕፃን ልጅ ተከታትሎ ምግብ ማብላት ሥራዬ ነበር። ሌሊት ኪዳን፣ ጠዋት ጸበል፣ ጾም ከሆነ ደግሞ ከሰዓት ቅዳሴ ወስዶ አስቀድሰን መምጣት ሥራዬ ነበር። እራሳቸው ላይ ሽንት ሲሸኑ፣ ሲጸዳዱ ሰውነታቸውን፣ ልብሳቸውን ማጠብ ሥራዬ ነበር። ልብሳቸውን ሰውነታቸውን በየሳምንቱ ወንዝ ወስጄ ማጠብ ሥራዬ ነበር።

ሌሊት ተነስተው ስለሚወጡ ለመተኛት እቸገር ነበር። በውድቅት ሌሊት በር እየከፈቱ ሊወጡ ሲሉ ነቅቼ አስተኛቸዋለሁ። እነሱ አይተኙ እኔንም አያስተኙ። ታዲያ አንድ ቀን ሌሊት ከፍተው እንዳይወጡ ምን ላድርግ? ብዬ አሰበኩ! አንድ ሐሳብ መጣልኝ ደስም አለኝ።

በጠዋት ተነስቼ መርካቶ ገብቼ ሁለት ሰንሰለት እና አራት ደህና ቁልፍ ገዝቼ መጣሁ። አይመሽ የለ መሸ። ሲመሽ አንዱን ሰንሰለት አንዱ ታማሚ እጁ ላይ አስሬ እጁን በሰንሰለት ቆለፍኩኝ። የእሱን ሰንሰለት ጫፍ ደግሞ የእኔ ቀኝ እጅ ላይ አስሬ የእኔንም እጅ በሰንሰለት ቆለፍኩኝ።

የአንደኛውን ታማሚ ግራ እጅ በሰንሰለት አሰርኩኝ። የእሱን የሰንሰለት ጫፍ አዙሬ ግራ እጄ ላይ አስሬ እጄን በሰንሰለት ቆለፍኩኝ። የእነሱን ሁለት ቁልፍ የእራሴን ሁለት ቁልፍ ያዝኩኝ። እነሱን ግራ ቀኝ አድርጌ እኔ ሆዬ መሃላቸው ተኛሁ። እነሱም ተኙ፣ ተሳስረን መተኛት ጀመርን። እንደነገርኳችሁ እራሳቸውን ስለማያውቁ ሌሊት አንደኛው ቀስ ብሎ ተነስቶ ወደ በሩ ሊሄድ ሲል እጄ ከእጁ ጋር በሰንሰለት ስለታሰረ ጎተተኝ ነቃሁ "ተኛ" ብዬ ተቆጥቼ አስተኛሁት።

እሱ ሲተኛ ከሆነ ሰዓት በኋላ ያኛው እወጣለሁ ብሎ ተነሳ፣ ወደ በሩም ሊሄድ ሲል እጁ ከእጄ ጋር በሰንሰለት ስለታሰረ ሲጎትተኝ ተነሳሁ። ብቻ ምን አለፋችሁ እመቤታችን እንድታድናቸው ከእነሱ ጋር አራት ዓመት በሰንሰለት ታስሬ ተኛሁ። እንዲህ ስላችሁ ጽድቄን ልነግራችሁ አይደለም የቅዱስ ዑራኤልን ተአምር እንጂ። አበው "ነገርን ከስሩ ውኃን ከጥሩ" ስለሚሉ የፈተናዬን መነሻ እንድታውቁት ነው። ለአራት ዓመታት ቀኝና ግራ እጄ በሰንሰለት ስለታሰረ ለረጅም ዓመት ሁለቱ እጄ ላይ የሰንሰለቱ ቅርጽ ነበር። በሂደት ጠፋ።

በአራተኛው ዓመት ሰኔ 21 ቀን 19 98 ዓ.ም እንጦጦ ማርያም ቤተ ክርስቲያን አብረን ሌሊት ገብተን እዛው አደርን። ሌሊቱን እዛው ያለ እንቅልፍ አድረን፣ ጠዋት ኪዳን አድርሰን፣ ጸበል ወስጄ አስጠምቂያቸው ስመጣ ረፋፈደ። ቀን እነሱም እኔም አላረፍንም።

በማግስቱ ሰኔ 22 ሌሊት ሽንቴ መጣ ሲል የግድ እሱን ወደ ሽንት ለመውሰድ የእኔም የእሱም የአንደኛው ታማሚ እጅ መፈታት ነበረበት። ፈትቼ ሽንት ወጥቶ ተመለሰ። ይህ የሆነው ሌሊት 7 ሰዓት ነበር። ከምተኛ ለምን አልጸልይም ብዬ ስለማይመች እነሱን እጃቸውን ፈትቼ አሰተኝቼ ጸሎት ጀመርኩ። ሌሊት 9 ሰዓት ሲል ደከመኝ እዛው ቁጭ ባልኩበት ተኛሁ።

ብቻ ምን አለፋችሁ የሰማሁት ድምጹ መብረቅ ነበር የመሰለኝ። ሰማይ ምድሩ ተደባለቀብኝ። የት እንዳለሁ ረሳሁኝ። ሰመመንም ሕልምም መሰለኝ። ግን ከፍተኛ ሕመም ስለሚሰማኝ የሆነ ነገር እንደሆንኩ አወኩ። እንደምንም ብዬ በዳበሳ ቀና ስል አንደኛው እንኳን ሰው አህያ የማይመታበት በሩን የምንቀረቅርበት ዘበጥ ያለ መቀርቀሪያ ዱላ ይዞ ሊደግመኝ ጎንበስ ብሎ ቆሟል። ያኔ በደንብ ታወቀኝ። ለካ ደህና አድርጎ በዛ መቀርቀሪያ አቅምሶኛል።

ፊት ለፊቴ ቆሞ "እንዴት አልሞትክም? እኔኮ ሞተሃል ብዬ ነበር የተውኩህ፣ መነሳትህን ባውቅማ እንዳትነሳ አድርጌ እዛው ጨርስህ አልነበረም" በማለት አጋንንቱ ዓይኑን አፍጥጦ፣ ጥርሱን አግጥጦ ሊደግመኝ ይዝትብኛል። ምንም አቅም አልነበረኝም። የሞት ሞቴን ጸሎተ ማርያም እየጸለይኩ እመቤታችንን እየተማጸንኩ፣ ቅዱስ ዑራኤል ድረስልኝ አልኩ።

ተማሙቼ ተነሳሁና ሳየው ዱላውን እንደያዘ ፊት ለፊቴ ቆማል። "በቅዱስ ዑራኤል ስም ስጠኝ ዱላውን" ስለው ያለማቅማማት ሰጠኝ። ተቀብዬው አስቀመጥኩና ልጁን አረጋጋሁት። እራሴንም ተመለከትኩት። ለካ በዱላው የመታኝ ግራ ጭንቅላቴን ነበር። አልተፈነከትኩም ግን ከፍተኛ እብጠት እና ሕመም ነበነው።

ልጁንም "ለምንድነው በበሩ መቀርቀሪያ የመታኸኝ" አልኩት። እሱም "በፍጹም እኔ አልመታሁህም አለኝ። ስለገባኝ ተውኩት። በጣም የሚገርማችሁ በበር መቀርቀሪያ ግራ ጭንቅላቴ መመታቱ ሳይሆን በ10 ቀጥር ሚስማር በኩል አለመመታቴ እና አናቴ አለመበሳቱ ነው።

በሰንሰለት ተሳስረን ከመተኛታችን በፊት ሌሊት እየወጡ ሲያስቸግሩኝ በሩን በቀላሉ እንዳይከፍቱት፣ ሊከፍቱ ሲሉ በሩን ሲታገሉ እንድነቃ ብዬ የመቀርቀሪያው ጫፍና ጫፉ ላይ 10 ቁጥር ሚስማር መትቼበት ነበር። በዚህም ለመክፈት ሲታገሉ ነቃለሁ።

ግን አንድ ቀን ከፍተው ሌሊት ቢወጡ አንድ ነገር ቢሆኑስ እነሱም እኔም ተረጋግተን ብንተኛስ ብዬ ነው ሰንሰለቱን የገዛሁት። እንደነገርኳችሁ የመቀርቀሪያው ጫፎች ላይ 10 ቀጥር ሚስማር ስለነበረ ቀስ ተብሎ አዟዙሮ ካልተከፈተ መቀርቀሪያው ከመሾገሪያው አይወጣም።

ለማንኛውም ሰኔ 22 የቅዱስ ዑራኤል እለት ከሞት የዳንኩበት ዕለት ነው። እንዲህ መመታቴን የሰሙ ወዳጆቼ "ደም ወደ ውጭ ስላልፈሰሰ ምናልባት ደምህ ወደ ውስጥ ወይም ወደ ጭንቅላትህ ፈሶ ሊሆን ስለሚችል የሆነ መሳሪያ አለ ሄደህ ሆስፒታል ታየው። ጥሩ አይደለም እንዲህ አይነት ችግር በሦስት ቀን ውስጥ ሊገድልህ ይችላል" አሉ።

ወቸው ጉድ ብሞትማ ያኔ ሞት ነበር ከዛ ዘግናኝ መቀርቀሪያ ያዳነኝ ከሞት የታደገኝ ቅዱስ ዑራኤል እንደፈለ ያድርገኝ ብዬ አልሄድም አልኩ። ግን ለአንድ ሳምንት ጭንቅላቴ የራሴ አይመስለኝም ነበር። የሆነ ነገር የተሸከምኩ እስኪመስለኝ ጭንቅላቴ ከብዶኝ ነበር።

የእመቤታችንን ጸበል እየጠጣሁ፣ የሸንኮራ የቅዱስ ዮሐንስን እምነት ጭንቅላቴን እየተቀባሁ፣ የቅዱስ ዑራኤልን መልክአ እየጸለይኩ ሁሉም ሰላም ሆነ፣ ሞቴ አለፈ ቀሲስም ተረፈ። ይሄ ነው እንግዲህ ከሞት የዳንኩበት ታሪኬ እና የቅዱስ ዑራኤል ተአምር።

ነብዩ ዳንኤል"አምላኬ መልአኩን ልኮ የአንበሶቹን አፍ ዘጋ፣ እነሱም አልጎዱኝም" እንዳለው ቅዱስ ዑራኤል ሊገድለኝ የነበረውን የዛን የመናጢ አፍ ዘጋልኝ። ከሞትም በተአምራት አዳነኝ። ት.ዳን 6፥22
2.5K views02:43
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 03:58:32
1.8K views00:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ
2023-06-30 03:58:23 #_የአገልግልት_ሰዓት_ማስተካከያ!

#_ጠዋት_3_ሰዓት_የተባለው_ጠዋት_9_AM_ለማለት_ነው!

#_ባፍሎ_ኒዮርክ_በሰላም_ገብቻለሁ!

ሼር በማድረግ ላላወቁ አሳውቁ!

ቀሲስ ሄኖክ ወልደ-ማርያም

ተወዳጆች ሆይ የካሊፎርኒያ አገልግሎቴን አጠናቅቄ ባፍሎ ኒዮርክ በሰላም ገብቻለሁ። ባለፈው የጥምቀት እና የቅብዓ ቅዱስ አገልግሎት የሚጀምረው "ጠዋት 3 ሰዓት" የሚለው በዚህ ሀገር ሰዓት አቆጣጠር ጠዋት 9 AM ለማለት ነው። ስለዚህ አገልግሎቱ የሚጀመረው ጠዋት 9 AM ነው።

አገልግሎቱም JUN 30, JULY 1,2,3 ማለትም አርብ፣ ቅዳሜ፣ እሑድ እና ሰኞ ሲሆን ከሦስት ቀን በኋላ ደግሞ JULY 7,8 እና 9 ማለትም አርብ፣ ቅዳሜ እና እሑድ ነው። የሁሉም ቀን አገልግሎቶች የሚጀምሩት ጠዋት 9 AM ነው!

ባፍሎ ኒዮርክ
JUN 29-2023
1.9K views00:58
ክፈት / አስተያየት ይስጡ