2022-08-31 08:43:24
*ሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ*
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም።
መላካም ንባብ!
ሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ በሥዕሉ ላይ አድሮ ቅዱሳን የሆኑ ባስልዮስንና ጎርጎርዮስን በመርዳት ከሃዲውን ንጉሥ ዑልያኖስን እንደቀሰፈው እኛንም ሀገራችን ኢትዮጵያንም ከክፉዎች ሁሉ ይታደገን።
መርቆሬዎስ ማለት የአብ ወዳጅ ማለት ነው፡፡ ዳግመኛም የኢየሱስ ክርስቶስ አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ወላጆቹ አስሊጥ ከምትባል ሀገር ቢሆኑም እርሱ ግን ተወልዶ ያደገው በሮሜ ከተማ ነው፡፡
በከሃዲው ንጉሥ በዑልያኖስ ዘመነ መንግሥት ሁለት ደጋግ የቂሳርያ ኤጲስ ቆጶሳት ነበሩ የአንዱ ስም ባስልዮስ የሁለተኛውም ስም ጎርጎርዮስ ነበር።
ከሃዲውብንጉሥ ዑልያኖስ ሁለቱን ኤጲስ ቆጶሳት ጠርቶ ለረከሱ ጣዖቶቹ እንዲሰግዱ አዘዛቸው። እነርሱም እግዚአብሔርን አንክድም ለሰይጣን አንደ ግድም አሉ።
ከዚህ በኋላ ንጉሡ ዑልያኖስ እኔ ወደ ጦር ግንባር እየወጣሁ ነው : ድል አድርጌ እስክመለስ ለአምላኬ ለአጵሎን ባትሰግዱ ታላቅ ቅጣትን እቀጣችኋለሁ አንገታችሁንም እቆርጠዋለሁ አላቸው።
ቅዱሳኑ ባስልዮስ እና ጎርጎርዮስም እኛስ ለጣዖት አንሰግድም ከጦርነቱ በ ሰላም ከመጣህ በእኛ ላይ የወደድከውን አድርግ አሉት።
በዚህ የተበሳጨው ንጉሥ ከውጊያ እስክመለስ ብሎ ሁለቱን ኤጲስ ቆጶሳት ወደ ወህኒ ወረወራቸው።
ቅዱስ ባስልዮስ እና ጎርጎርዮስ በታሰሩበት ወህኒ ቤት ውስጥ በእንጨት ላይ የተሰቀለ የሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕል ነበረ።
ኤጲስ ቆጶሳቱ በስዕሉ ፊት በጊዜ ቆመው እግዚአብሔር የመረጠህ ቅዱስ መርቆሬዎስ ሆይ ወደ አንተ ተማጽነናል፣ አትጣለን፣ አትናቀንም ጨካኙን ንጉሥ ዑልያኖስንም ወደ እኛ አትመልሰው ከስቃይ አድነን ፣ ከእጁም ታደገን ሥጋችን ደካማ ነውና ብለው ጸለዩ።
ከጸሎታቸው በኋላ ተኙ። የእኩለ ሌሊት ጸሎት ሊያደርሱ ከመኝታቸው ሲነሱ ቀን የተማጸኑት የቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕል በተሰቀለበት ቦታ ላይ አልነበረም: ቢፈልጉትም ሥዕሉን አጡት።
እጅግ እየተገረሙ የእኩለ ሌሊት ጸሎታቸውን ፈጽመው ተኙ። ደግሞ ለማለዳ ጸሎት ሲነሱ ግን የቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕል ቀድሞ በተሰቀለበት ቦታ ላይ ተመልሶ ተሰቅሎ አገኙት!
ኤጲስ ቆጶሳቱ ተደንቀው ወደ ሥዕሉ ቀርበው ቢመለከቱ ሥዕሉ ላይ ካለው የቅዱስ መርቆሬዎስ ጦር ጫፍ ላይ ትኩስ ደም ይንጠፈጠፍ ነበር፡፡ ኤጲስ ቆጶሳቱ በመገረም እንዲህ አሉ አሉ ቅዱስ መርቆሬዎስ ሆይ የት ጠፋህብን? የክርስቶስ ምስክር ጌታችን መርቆሬዎስ ሆይ የእውነት ፀር የሆነ ዑልያኖስን ገደልከውን? ከእጁም ታደግከንን? አሉት: : በዚያን ጊዜ ሥዕለ ቅዱስ መርቆሬዎስ አዎን እንደሚል ሁሉ እየተንቀሳቀስ አንገቱን ዘንበል አደረገ።
በነጋታው ከሃዲው ንጉሡ ዑልያኖስ መሞቱ እውን መሆኑ በሀገሩ ሁሉ ተነገረ። ኤጲስ ቆጶሳትም ቅዱስ መርቆሬዎስ ያደረገላቸውን ተአምር አደነቁ።
ዛሬ በባለ ጥቁር ፈረሱ የቅዱስ መርቆሬዎስ ስዕል ላይ ከጎኑ አብረው ተስለው የምናያቸው ሁለቱ ኤጲስ ቆጶሳት ባስልዮስ እና ጎርጎርዮስ ናቸው። ሥዕሉ ላይም በጦሩ ጫፍ የምናየው ደምም የዚህ ድንቅ ተአምር መዘከሪያ ነው።
ፍጡነ ረድኤት ሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ ሆይ እባክህን ቅዱስ ባስልዮስ እና ቅዱስ ጎርጎርዮስን እንዳዳንካቸው እኛንም ከክፉ ሁሉ አድነን። የቅድስት ሀገር የኢትዮጵያን እና የከበረች የተዋህዶ ጠላቶችን ዑልያኖስን በወጋህበት ጦርህ ውጋልን።
የቅዱስ መርቆሬዎስ በረከት በየቤታችን ይድረስ።
ብሩህ ቀን
1.2K views05:43