2022-08-29 18:46:12
"Trauma within drama"
ኤልያስ ሽታኹን
(የልደት ዳር ጨዋታ)
~ ~ ~ ~ ~
* ሞት ይመስለኝ ነበር ክፉ ነገር:: ለካ አሟሟት ነው::
አባቴን በፀብ እንደተኳረፍን አረፈ::
አላሳደግኝም::
ግን አልጎድለብኝም አልልም::
እንኳን አባት ጎረቤትም ያጎድላል::
ከሌላ ለወለዳቸው ታላላቆቼ ሁሉን ሆኖላቸዋል:: ልክ ነው :: እናት አልነበራቸውምና::
ሰዎች ውበቱን የሚናገሩልት በብዛት የሚቆጠር ሱፍ የነበረው:: ደረባባ:: ቢናገር የሚሰማ:: ቢቆጣ የሚፈራ:: እርቅ በእጁ ሽማግሌ ነበር::
እቃ የሚበርከትለት እንዲያውም "ቴፑ" 39 አመት እንደሰማባት ሲያወራ ሰምቻለሁ:: ሽቅርቅር ነው::
ቤት ከሱ የወሰድነው ነገር ብዙ ነው:: ውስጡን ለቄስ ውጪ ውበት:: ሰው የሚድር የራሱን ትዳር ያላቆመ:: የተበላሸ የሰው ልጅ መካሪ የራስ ልጅ ላይ ስነፍ:: ለሰው መሬት ለመግዛት ዋስ ለቤቱ ሩብ ካሬ የሌለው::
ብቻ እንደተጣላን ሞተ:: ለሊቱን ሙሉ ሲያጣጥር አይቸዋለሁ:: አጥንቱ ሲገተር ጥርሱ መግጠም ሲከብደው አይቸዋለሁ::
ጀምበር መውጫ ንጋት ላይ ነፍሱ ተለየችው::
ብቻዬን ከአስክሬኑ ጋ አለቀስኩ::
በብዙ ስሜት መሐል አንባሁ:: እንቀጠቀጣለሁ:: " ይቅር ብዬሀለሁ" ለማለት አቅም አለነበረኝም::
ህመሜን ስላልነገርኩት ንደድኩ እንጂ:: ቅያሜዬን በውል ሳላስርዳው ሞተ:: እውነቱን ሳልያስረዳኝ ሄደ:: እንድልጅ ሳይሆን እንደእኩያ አለቅስኩ:: እሱ አብሮኝ አይሁን እንጂ ስልሱ የማስበው አብሮኝ ኖሯልና:: እሱ እናቴ ላይ አጠፋ የምለውን እኔ ዛሬ ስንት ሴቶች ላይ አርጌ አየሁት::
ወንዶች አባቶቻቸውን ይርግማሉ:: ግን እንደአባቶቻቸው ናቸው:: ነገ የልጄ እናት እና ልጆቼ የሚወቅሱኝ እውንታቸውን ሳስብ የረገምኩትን አባቴን አዘንኩለት::
ግን ለመታረቅም ለመጣላትም መኖር ነበርበት::
በጊዜ ሂደት
ታቦቴን የተነጥኩ መቅደስ ነፍሴን ይዤ እኳትናለሁ::
በምናገረው በምፅፈው ሁሉ ድሞ ምን አጣ ይሆን?ስል እረበሻለሁ::
እንማን ይቀብሉኛል?
እንማን ይርቁኛል?
"እኔ ቦታ የለኝም
የቆምኩበት አያውቀኝም" እንዳለ ኪሩቤል::
ራሴን ለሰዎች ኖሬያለሁ ብልም ውሸት ነው::
ለምወዳቸው በሚል ሰበብ ለራሴ አልነበርም ወይ የኖርኩት::
ግጥምን ከድኜ
ፂሜን ላጭቼ
ፀጉሬን አንስቼ
ድምፄን ዘግቼ
ንባቤን ቀድጄ
ስሜን አንስቼ ራሴን ሳየው
የት አለሁ?
በርግጥ ውሸት ብቻ አይደለንም:: እውነትም እንደዛው:: ቅልቅል መርዝ ነን:: ላንዱ መድኃኒት ላንዱ ገዳይ::
ተከታይ ካበጀን ወዲያ መልሰን የተከተለንን ጀሊል እንከተለዋለን:: እሱ ሚወደውን ለበሰን አውርተን አጊጠን እንታያለን:: የሚከተሉንን የመከተል ድራማ ላይ እንገባለን::
በ 14 አመቴ ይመለኛል:: እቤት ሽሮ በልተን ተኛሁ::
ወንድሜ ማታ አምሽቶ ሲመጣ ስጋ እጁ ላይ ነበር:: ሲጠበስ ሸተተኝ::
"ሁሉም በልተዋል"
እናቴ "አዎ አንተ ብላ"ትለዋለች
አቃተኝ:: እንደባነንኩ አስመሰልኩ:: ደነገጡ ::
"ምነው?"
"አባዬ ሲሞት አየሁ" እናቴ አማተበች::
ልተኛ ልመለሰ ወደትራስ መንገዴን ጀመርኩ::
"አቢ" ተጣራ ወንድሜ :: ጎሽ ብላ ሊሉኝ ነው::
"በል:: እንኳን ነቃህ ና ብላ"
ያኔ በስራሁት ያኔ ተሰራሁ::
ድራማዬን ሰርቼ ስጋዬን በልቼ ተኛሁ::
"አልወደውም" በምለው ሰው ስም እንዴት ታሪክ ሰራሁ:: እንዴት? በስሙ በላሁ?
በትንሹ ልቤ ሸረኛ ሆኜ ራሴን አየሁት::
የውነት ሞቷል ዛሬ:: ግን አልበላበትም::
ስሙንም አላነሳም:: ዛሬም አንስቼው ከሆነ አላውቅም....
845 views15:46